በጥበብ ኢስላማዊ ማህበር/ Betibeb Islamic Association

በጥበብ ኢስላማዊ ማህበር/ Betibeb Islamic Association ሁለነንተናዊ በሆኑ ሀገራዊ ማህበረሰባዊ የለውጥ የልማትና የትምህርት ስራዎች እንዲሁም በስነ ምግባር እና በእውቀት የታነጸ ትውልድ በመቅረጽ ላይ የተሰማራ ተቋም!

ጌታህም (እንዲህ ሲል) አዘዘ፦ እርሱን እንጂ ሌላን አትገዙ። በወላጆቻችሁም መልካምን ሥሩ። በአንተ ዘንድ ሆነው አንዳቸው ወይም ሁለታቸው እርጅናን ቢደርሱ «ኡፍ» አትበላቸው። አትገላምጣቸውም...
08/12/2025

ጌታህም (እንዲህ ሲል) አዘዘ፦ እርሱን እንጂ ሌላን አትገዙ። በወላጆቻችሁም መልካምን ሥሩ። በአንተ ዘንድ ሆነው አንዳቸው ወይም ሁለታቸው እርጅናን ቢደርሱ «ኡፍ» አትበላቸው። አትገላምጣቸውም። ለእነርሱም መልካምን (የአክብሮት) ቃልን ተናገራቸው።
ለእነርሱም ከእዝነትህ የመዋረድን ክንፍ ዝቅ አድርግላቸው። «ጌታዬ ሆይ! በሕፃንነቴ (በርኅራኄ) እንዳሳደጉኝ እዘንላቸውም» በል።

አላህ (ሱ.ወ) እርሱን በብቸኝነት የማምለክን ታላቅ ትዕዛዝ ካስቀመጠ በኋላ ወዲያውኑ ያስከተለው ትዕዛዝ ለወላጆች መልካም መሆንን ነው። ለወላጆች የምናደርገው እንክብካቤ በህይወት እያሉ ብቻ ሳይሆን፣ ከሞቱ በኋላም በዱዓ ልናስታውሳቸው እንደሚገባ ያስገነዝባል:: ይህንን ግዴታ መወጣት የአላህን ውዴታ ከምናገኝባቸው ታላላቅ መንገዶች አንዱ ነው።

አላህ ወላጆቻችንን እድሜያቸውን በኢማን፣ ጤናቸውን በአፊያ አጊጦ ያቆይልን።
በእዝነቱ ወደ እርሱ የወሰዳቸውንም፣ ቀብራቸውን የጀነት ጨፌ ፣ ማረፊያቸውን ጀነተል ፊርደውስ ያድርግልን።አሚን!✨

መልካም ሳምንት ይሁንላችሁ!
#ዱዐ
#ቁርዐን
https://t.me/beTibeb_In

የቀናት ድምቀት፣ የሳምንቱ ጸጋ... ጁምዓ!ጁምዐ የሰው ልጆች ሁሉ አባት የሆነው ነቢዩሏህ አደም(ዐ.ሰ) የተፈጠረበት፣ ጀነት የገባበት ፣ እንዲሁም ቂያማም የምትቆምበት ታላቅ ቀን ነው። ይህን...
05/12/2025

የቀናት ድምቀት፣ የሳምንቱ ጸጋ... ጁምዓ!

ጁምዐ የሰው ልጆች ሁሉ አባት የሆነው ነቢዩሏህ አደም(ዐ.ሰ) የተፈጠረበት፣ ጀነት የገባበት ፣ እንዲሁም ቂያማም የምትቆምበት ታላቅ ቀን ነው። ይህንን ውድ ቀን አላህ መርጦልናልና በዱዐ፣ በዚክርና በመልካም ስራዎች ወደርሱ እንቃረብ::

አላህ መልካሙን ሁሉ ይወፍቀን።
ጁምዓ ሙባረክ 🌙

اللهم صلِّ وسلم وبارك على سيدنا محمد وعلى آله وصحبه أجمعين.

#ጁምዐ
#ሰለዋት
https://t.me/beTibeb_In

 #ሒጃብበዚህ ውብ ርዕስ ዙሪያ የምንወያይበት፣ ልምዳችንን የምንካፈልበትና የምንማማርበት ልዩ ቆይታ ይኖረናል።ሐሙስ ህዳር 25, ከምሽቱ 2:30 ጀምሮ በበጥበብ ኢስላሚክ አሶሲዬሽን የቲክቶክ ...
03/12/2025

#ሒጃብ

በዚህ ውብ ርዕስ ዙሪያ የምንወያይበት፣ ልምዳችንን የምንካፈልበትና የምንማማርበት ልዩ ቆይታ ይኖረናል።

ሐሙስ ህዳር 25, ከምሽቱ 2:30 ጀምሮ በበጥበብ ኢስላሚክ አሶሲዬሽን የቲክቶክ ገጻችን ላይ በቀጥታ ሥርጭት ሁላችሁም ተጋብዛችሗል።✨

https://www.tiktok.com/?_r=1&_t=ZM-91fNAmVH7xz

ከአላህ(ሱ.ወ) ክብርና ልዕልና የሚመነጨው እውነተኛ እምነትና ፍራቻ ለዘላለም የመረጋጋትና የስኬት መንገድ ቁልፍ ነው:: መንገዱ ግን ቀላል አይሆንም፣ የነፍስያና የሸይጧን መሰናክሎች ጉዞውን ...
01/12/2025

ከአላህ(ሱ.ወ) ክብርና ልዕልና የሚመነጨው እውነተኛ እምነትና ፍራቻ ለዘላለም የመረጋጋትና የስኬት መንገድ ቁልፍ ነው:: መንገዱ ግን ቀላል አይሆንም፣ የነፍስያና የሸይጧን መሰናክሎች ጉዞውን ሊያከብዱብን ይታትራሉ:: መሰናክኖሎቹ ባጋጠሙንና የጌታችንን ትዕዛዝ ተላልፈን በወንጀል እንድንዘፈቅ በገፉን ቁጥር እርሱ ፊት የምንቆምበትን እለት እናስታውስ::

አላህም(ሱ.ወ) እርሱ ፊት መቆምን ፈርተው ከወንጀል ለሚታቀቡት ባሮቹ ታላቅ ምንዳ እንዳዘጋጀ ያበስረናል:: ከዚህ ታላቅ ምንዳ ተቋድሰን፣ ደግሞም ለሰፊው ፍቅሩና ወሰን ለሌለው እዝነቱ የተገባን ባሮቹ እንድንሆን ያድርገን:: አሚን::

ድንቅና ፍሬያማ ሳምንት እንዲሆንላችሁ ተመኘን!

#ቁርዐን
https://t.me/beTibeb_In

በዚያ ሰፊና ሁሉን አዋቂ በሆነው ዕውቀቱ ውስጥ፣ አላህ: ባሮቹ የሚሰሩትን፣ የሚያስቡትን፣ የሚደብቁትንና የሚገልጹትን ጠንቅቆ ያውቃል። ከእርሱ ምንም ነገር አይሰወርም::ለጌታችን ብለን በየዕለ...
28/11/2025

በዚያ ሰፊና ሁሉን አዋቂ በሆነው ዕውቀቱ ውስጥ፣ አላህ: ባሮቹ የሚሰሩትን፣ የሚያስቡትን፣ የሚደብቁትንና የሚገልጹትን ጠንቅቆ ያውቃል። ከእርሱ ምንም ነገር አይሰወርም::
ለጌታችን ብለን በየዕለቱ የምናደርጋት ሱጁድ፣ የሱን ውዴታ ተስፋ አድርገን የምናወጣው ሰደቃ፣ በጤንነትም ሆነ በህመም ላይ ሆነን የምናከናውናት እያንዳንዷ ተግባራችን አላህ ዘንድ በትክክል ትመዘገባለች። በዚያው ልክ ደግሞ፣ የምንሰራው ጥፋትም ሆነ የምንዘነጋው ሀቅ በርሱ እይታ ስር ናቸው::

አላህ አይዘነጋምና በስራዎቻችን አንዘናጋ::
በሰደቃና ሰለዋት የተዋበ ጁምዐ ይሁንላችሁ✨

اللهم صلِّ وسلم وبارك على سيدنا محمد وعلى آله وصحبه أجمعين.
#ጁምዐ
#ሰደቃ
#ሰለዋት
https://t.me/beTibeb_In

መመረጥ ከአላህ ነው:: በህይወታችን የምናልፈው እያንዳንዱ ቅፅበት፣ የምንረግጣቸው እርምጃዎች፣ የምናገኛቸው ሰዎች – ሁሉም የአላህ ምርጫ አካል ናቸው።አላህ በታላቅ ምሕረቱና ጥበቡ፣ ላጨን የ...
21/11/2025

መመረጥ ከአላህ ነው:: በህይወታችን የምናልፈው እያንዳንዱ ቅፅበት፣ የምንረግጣቸው እርምጃዎች፣ የምናገኛቸው ሰዎች – ሁሉም የአላህ ምርጫ አካል ናቸው።አላህ በታላቅ ምሕረቱና ጥበቡ፣ ላጨን የተመረጠ ትልቅ ስፍራ እየሞረደንና እያዘጋጀን ነው::

መልካም ብለን በደስታ የምንቀበለውና፣ መጥፎ ብለን በሀዘን የምናሳልፈው የህይወት ገፅ፣ በመንገዳችን ያጋጠመን በጎም ሆነ ፈታኝ አሻራ ያሳደረብን እያንዳንዱ ሰው፣ ለተመረጥንለት አላማ እያሰናዳን ነውና ቆም ብለን ለዚህ ፀጋ እናመስግን:: አላህ ለሚያመጣው ብርሃንና ታላቅ ድል ይጠቀምብን ዘንድ፣ ዝግጁነታችንን በኢባዳ፣ በሰብር፣ እና በትጋት እናሳይ። በሰለዋት የደመቀ ጁምዐ ይሁንላችሁ::

اللَّهُمَّ صَلِّ عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ كَمَا صَلَّيْتَ عَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ
اللَّهُمَّ بَارِكْ عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ كَمَا بَارَكْتَ عَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ.

#ጁምዐ
#ቁርዐን
#ሰለዋት
https://t.me/beTibeb_In

09/11/2025

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Mubarek Adem, Zeydan A. Yonis, Nurhussein Issa, Seya Hussen, Tofik Teku, Salim Ahmed, Múke Man, Mohammed Ahmed, Muhammed Ahmed, Shikur Yesuf, Betelhem Fekadu, Mohammed Awoll, Nebile Adugna Muhdin, Abdulfetah Seid, Nuru Hassen

በጥበብ ኢስላማዊ ማኅበር ያዘጋጀውን በፋይናንስ ዙሪያ ያጠነጠነ ስልጠና ለመካፈል የሚያስችለው የበይነመረብ ምዝገባ ተጠናቋል። የተመዘገባችሁ ወንድምና እህቶች በዕለቱ ሰአት አክብራችሁ በመገኘት...
09/11/2025

በጥበብ ኢስላማዊ ማኅበር ያዘጋጀውን በፋይናንስ ዙሪያ ያጠነጠነ ስልጠና ለመካፈል የሚያስችለው የበይነመረብ ምዝገባ ተጠናቋል። የተመዘገባችሁ ወንድምና እህቶች በዕለቱ ሰአት አክብራችሁ በመገኘት የስልጠናው ተካፋይ እንድትሆኑ እንጋብዛለን። እናመሠግናለን!

https://t.me/beTibeb_In

ልዩ እድል 💰__በኢኮኖሚክስ እና ኢስላሚክ ፋይናንስ ባለሙያው ኢብራሂም አብዱ ጋር ልዩ ቆይታ ይኖረናል !Title :- Financial Uncertainty and Economic Changeየፋይና...
30/10/2025

ልዩ እድል 💰
__
በኢኮኖሚክስ እና ኢስላሚክ ፋይናንስ ባለሙያው ኢብራሂም አብዱ ጋር ልዩ ቆይታ ይኖረናል !

Title :- Financial Uncertainty and Economic Change

የፋይናንስ ስርዓቱ ተለዋዋጭነት እና የኢኮኖሚ ለውጥ በሚል ዳሰሳ ይቀርብልናል

https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSfTeH93NySVVYQbgpjD0OCkRfDO9th9bI0OiyxDx97zX4wPvg/viewform?usp=header

ማስታወሻ :- ያለን ቦታ ውስን ስለሆነ ከላይ ባለው ጎግል ፎርም ቀድመው ይመዝገቡ !

ህዳር 03/2018
ከቀኑ 11:00 ጀምሮ
ቦታ በጥበብ ኢኒስቲቲዩት ቄራ ዴታሞ ህንፃ

አዘጋጅ በጥበብ ኢኒስቲትዩት

https://t.me/beTibeb_In

"እንዴት ሊሆን ነው? አንተንም በነዚህ ላይ መስካሪ ባደረግንህ ጊዜ።" በሚለው የሩቅ ሀገር ክስተት በሆነው  ተጠይቅ ወስጥ የኛ ስፍራ የት ይሆን? የርሳቸው እዝነት ከዱንያ የሚነሳ እስከ ወዲ...
07/04/2025

"እንዴት ሊሆን ነው? አንተንም በነዚህ ላይ መስካሪ ባደረግንህ ጊዜ።" በሚለው የሩቅ ሀገር ክስተት በሆነው ተጠይቅ ወስጥ የኛ ስፍራ የት ይሆን? የርሳቸው እዝነት ከዱንያ የሚነሳ እስከ ወዲያኛው ዓለምም የሚሻገር ነው። አይን ሳያይ በምናብ ብቻ የሚያስናፍቅ፤ ነገም ከአስፈሪው ቀን የሚያድን ምልጃ የተኖረበት ነው። አላህን(ሱ.ወ) እንለምነው። በዱንያ ውዴታቸውን፤ ነገም በአኼራ ሸፈዐቸውን እንዲገጥመን እንማፀነው።

ዕለቱንም በሰለዋት እናስውበው። ቀደምት ደጋጎች በተመነዱበት፣ ወደፊትም የማይቋረጥ ምንዳ በሚያስገኘው፣ ከጭንቅ መውጫ በሆነው ንግግር።

"የአላህ ሰላት አና ሠላም በመልዕክተኛው ሙሐመድ(ሠ.ዐ.ወ) ላይ ይውረድ፥ በብርቱ የሚያወሳ ባወሳቸው፣ የሚዘነጋም በዘነጋቸው፣ ጀንበር ለፍጡራን በተገለጠችም ባዘቀዘቀችም ቁጥር።"

اللَّهُــمَّ صَلِّ وَسَـــلِّمْ وَبَارِكْ على نَبِيِّنَـــا مُحمَّد ﷺ❤

https://t.me/beTibeb_In

"የአስተባባዮች፣ የዋሾዎች መጨረሻ እንዴት እንደሆነ ተመልከት።" በሚል የተገለፀው የማብቂያቸውን አስከፊነት አመላካች ነው። "ከእውነተኞቹም ጋር ሁኑ።" የሚለውን መርህ ይዘን በፈጣሪም በፍጡር...
04/04/2025

"የአስተባባዮች፣ የዋሾዎች መጨረሻ እንዴት እንደሆነ ተመልከት።" በሚል የተገለፀው የማብቂያቸውን አስከፊነት አመላካች ነው። "ከእውነተኞቹም ጋር ሁኑ።" የሚለውን መርህ ይዘን በፈጣሪም በፍጡርም ዘንድ ታምኖ የታመነ ለመሆን እንትጋ። አላህ(ሱ.ወ) ያግዘን።🤲
ጁሙአ ሙባረክ!

https://t.me/beTibeb_In

ለአሁን አብቅቷል። ለከርሞ "ያድርሰን" ከማለት ውጭ አንዳችም ዋስትና የለም። አይንን ከድኖ የመግለጥ ያክል ፈጣን የነበሩት ውስን ቀናት ግን ተገባደዋል። ያለለት አትርፎባቸው፤ እድለቢሱ ደግሞ...
30/03/2025

ለአሁን አብቅቷል። ለከርሞ "ያድርሰን" ከማለት ውጭ አንዳችም ዋስትና የለም። አይንን ከድኖ የመግለጥ ያክል ፈጣን የነበሩት ውስን ቀናት ግን ተገባደዋል። ያለለት አትርፎባቸው፤ እድለቢሱ ደግሞ በዋዛ ፈዛዛ አሳልፏቸው ነጉደዋል። በህይወት እስትንፋሳቸው ሁሉ ለቃሉ በጀ ያሉት አሁንም እንደተትረፈረፈ አዝመራ ሲያጭዱ ከርመዋል። የእኛስ ጎራ ከየትኞቹ ይሆን? ስንል መጠየቃችን አልቀረም። ከደጋጎች ጎራ እንዲያደርገን፣ የልባችንንም መሻት እንዲሞላልን ተመኝተናል። ዛሬያችንንም ነጋችንንም እንዲያበጀው ተማፅነናል። የግፉአንን ድልና የግፈኞችን መጨረሻ እንዲያቀርበው ከመመኘት አልዘነጋንም። የጠየቅነው ብዙ ነውና የሚበጀንን እንዲሰጠን ከአላህ(ሱ.ወ) እንከጅላለን። ከዚህ የደረስነው በርሱ እርዳታ ነውና፣ ብዙዎችም ለዚህ ሳይታደሉ ከቁጥር ጎድለዋልና ከምስጋና አናጓድልም። አልሀምዱሊላህ!
ደግሞም ከቀኞቹ ከደጋጎቹ እያዋለ፤ በእድሜም በፀጋውም እያቀማጠለ ለከርሞ እንዲያበቃን ከመመኘት አንመለስም።

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በተለይም የበጥበብ ኢስላማዊ ማህበር ቤተሰቦች እንኳን ለ1446ኛው አመተ ሂጅራ የኢድ አል ፊጥር በአል በሰላም አደረሳችሁ።

ኢድ ሙባረክ!
تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمال

https://t.me/beTibeb_In

Address

Addis Ababa

Telephone

+251904438888

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በጥበብ ኢስላማዊ ማህበር/ Betibeb Islamic Association posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to በጥበብ ኢስላማዊ ማህበር/ Betibeb Islamic Association:

Share