08/12/2025
ጌታህም (እንዲህ ሲል) አዘዘ፦ እርሱን እንጂ ሌላን አትገዙ። በወላጆቻችሁም መልካምን ሥሩ። በአንተ ዘንድ ሆነው አንዳቸው ወይም ሁለታቸው እርጅናን ቢደርሱ «ኡፍ» አትበላቸው። አትገላምጣቸውም። ለእነርሱም መልካምን (የአክብሮት) ቃልን ተናገራቸው።
ለእነርሱም ከእዝነትህ የመዋረድን ክንፍ ዝቅ አድርግላቸው። «ጌታዬ ሆይ! በሕፃንነቴ (በርኅራኄ) እንዳሳደጉኝ እዘንላቸውም» በል።
አላህ (ሱ.ወ) እርሱን በብቸኝነት የማምለክን ታላቅ ትዕዛዝ ካስቀመጠ በኋላ ወዲያውኑ ያስከተለው ትዕዛዝ ለወላጆች መልካም መሆንን ነው። ለወላጆች የምናደርገው እንክብካቤ በህይወት እያሉ ብቻ ሳይሆን፣ ከሞቱ በኋላም በዱዓ ልናስታውሳቸው እንደሚገባ ያስገነዝባል:: ይህንን ግዴታ መወጣት የአላህን ውዴታ ከምናገኝባቸው ታላላቅ መንገዶች አንዱ ነው።
አላህ ወላጆቻችንን እድሜያቸውን በኢማን፣ ጤናቸውን በአፊያ አጊጦ ያቆይልን።
በእዝነቱ ወደ እርሱ የወሰዳቸውንም፣ ቀብራቸውን የጀነት ጨፌ ፣ ማረፊያቸውን ጀነተል ፊርደውስ ያድርግልን።አሚን!✨
መልካም ሳምንት ይሁንላችሁ!
#ዱዐ
#ቁርዐን
https://t.me/beTibeb_In