05/03/2026
ወንድማችን፣ጓደኛችን እንታደገው!
/////////////////////////////////////////////////////
ዲያቆን እና ጠበቃ ፍቃድ አገኘው ይባላል።ትውልዱ በሰሜን ወሎ በድሮው መቄት ወረዳ 031 ቀበሌ በአሁኑ ጋዞ ወረዳ 015 ቀበሌ ዋሮ ቅ/ሚካኤል ደብር ሲሆን መደበኛ ትምህርቱን
# ከ1-2 ዋሮ ሻሪያው አንደኛ ደረጃ ት/ቤት
ከ 3ኛ -6ኛ ቦያ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት
ከ7ኛ - 10ኛ እስታይሽ አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት
ከ11ኛ -12ኛ ኮን ሁለተኛ ደረጃ መሰናዶ ት/ቤት
የተማረ ሲሆን የመጀመሪያ ድግሪውን በሕግ ከደብረ ማርቆስ ዩንቨርስቲ ተመርቋል።
ዩንቨርስቲ በነበረበት ወቅት ከህግ ትምህርቱ ጎን ለጎን በመንፈሳዊ ዘርፍም ተምሮ በድቁና ማእረግ ተመርቆ ወቷል። ከተመረቀ በሗላም መጀመሪያ ጎንደር ከዛም በሰሜን ወሎ ኮን ከተማ በአቃቢ ህግነት ለወገኑ ለፍትህ ሲከራከር፣በጎን እናት ቤተክርስቲያንን እያገለገለ፣ደካማ እናት አባቱንም እየደጎመ ከትምህርት በሗላ ያለውን የህይወት ምእራፍ ቀጠለ።
ፍቃድ ትልቅ ህልም የነበረው ወጣት ስለነበር ትዳር መሰረተ፣ የልጅ አባት ለመሆንም በቃ። ፍቃድ አገኘው እዚህ ደረጃ ከመድረሱ በፊት በተለይ ትምህርቱን እስከሚጨርስበት ድረስ ብዙ ውጣ ውረድ የገጠመው ቢሆንም ሁሉንም አሸንፎ በአለማዊም፣በመንፈሳዊም ተምሮ ሃገሩን እያገለገለ፣ቤተሰብ እየረዳ፣ ትዳር መስርቶ፣ልጅም ወልዶ ፈተናዎችንም አሸንፎ ጥሩ ኑሮ መኖር ጀምሮ ነበር።ህይወት አንዳንድ ጊዜ ወደ የት እንደምትመራን አይታወቅም እና ምክኒያቱ በውል ባልታወቀ ሁኔታ የጤና እክል ገጠመው።
ትናንት ለፍትህ ሲከራከር፣እናት ቤተ ክርስቲያንን ሲያገለግል፣ቤተሰቦቹን ሲረዳ የነበረው፣የልጅ አባት የነበረው ተስፈኛው ፍቃድ ስራ አቋረጠ፣ከሚወደው የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ተለየ፣ቤተሰብ ሲረዳ የነበረው ፍቃድ በግልባጩ ከሰው እርዳታ የሚጠብቅ ለመሆን በቃ። ያለፉትን አራት አመታት ቤተሰቦቹ እና የተወሰኑ የቅርብ ጓደኖቹ ብዙ ደከሙ፣ ነገር ግን ፈቃድ ሊሻለው አልቻለም። ይህን ሁኔታን የሰሙ የተወሰኑ የቀድሞ አብረውት የተማሩ ጓደኞቹ ወደ አዲስ አበባ እንድመጣ አድርገው ቤት ተከራይተው ያለበትን ሁኔታ ለመከታተል ተሞክሮ ነበር።
ፍቃድ አሁን ላይ ያለበት ሁኔታ የሚያሳየው ውስብስብ የሆነ የጤና እክል እንደገጠመው እና ይህንንም ለማስተካከል
# የሳይካትሪስት
# ሳይኮሎጅ
#-የህክምና ትሪትመንት እንደሚያስፈልገው ፣ ጊዜም ሊወስድ እንደሚችል እና በትንሹ ለጊዜው እስከ 200,000 ሽ ብር እንደሚያስፈልግ ስለተረዳን ይህ ደግሞ በተወሰኑ ጓደኞቹ ብቻ የሚሸፈን ባለመሆኑ፣ ጓደኛችን ወደ ነበረበት ሁኔታ ለመመለስ ዋናው ስራ የእግዚያብሄር ሆኖ ከእግዚያብሄር በታች የሚቻለውን ለመሞከር አሁን ጉዳዩን በቅርብ ከምንከታተለው ጓደኞቹ አቅም በላይ ሆኖ በመገኘቱ ጉዳዩን ወደ ህዝብ ለማውጣት ተገደናል።ስለሆነም ቀድሞ አብራችሁ የተማራችሁ የክፍል ጓደኞቹ፣የሃገሩ ልጆች፣ፍቃድን በአንድም በሌላም አጋጣሚ የምታውቁ እህት ወንድሞች እና ኢትዮጵያዊያን
#-ፍቃድን ማዳን በአንድ በኩል ፍቃድንእና የእሱን እርዳታ የሚፈልጉ ቤተሰቦቹን መታደግ በሌላ በኩል የሰውን ልጅ በህይወት እያለ መታደግ የሚሰጠውን የህሊና እረፍት ግምት ውስጥ በማስገባት የበኩላችሁን ድጋፍ እንድታደርጉልን በእግዚያብሄር ስም እንጠይቃለን።
ጓደኞቹ
Telegram link.
https://t.me/+ieYP37QBDC8yNzg0
#ለበለጠ መረጃ
ስልክ ቁጥሮች:
0980135413 ሃብትየ መከተ
0921919432 ያረጋል አለምሰው
0926100976 ፍቃዱ የማታው
0920224033 አብርሐም ሞገስ
Account No: 1000750998619
ፍቃዱ የማታው እና ወይም መንግስት አዋዬ