Ethiopia Reads/ኢትዮጵያ ሪድስ

Ethiopia Reads/ኢትዮጵያ ሪድስ Ethiopia Reads is a Non-profit organization to support children's literacy and enhance the reading c

ኢትዮጵያ ሪድስ ከሀዋሳ ዩንቨርስቲ የማህበረሰብ ሳይንስ ዲፓርትመንት ጋር በልጆች ንባብና ትምህርት ላይ አብሮ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ ኢትዮጵያ ሪድስ በሀዋሳ ከተማና አካባቢዋ ...
09/04/2026

ኢትዮጵያ ሪድስ ከሀዋሳ ዩንቨርስቲ የማህበረሰብ ሳይንስ ዲፓርትመንት ጋር በልጆች ንባብና ትምህርት ላይ አብሮ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ
ኢትዮጵያ ሪድስ በሀዋሳ ከተማና አካባቢዋ ያሉ ልጆች የትምህርትና የንባብ ችሎታ ለማሻሻል ከሀዋሳ ዩንቨርስቲ የሶሻል ሳይንስ ትምህርት ክፍል ጋር የትብብር ስምምነት አደረገ።
የተፈረመው ስምምነት በአካባቢው ህፃናት መካከል የንባብ ባህልን ማሻሻል ፣ ቤተ መፅሃፍትን ማስፋፋት ፣ የተለያዪ የስልጠና እና የምርምር ስራዎችን በጋራ መስራት ፣ እንዲሁም በንባብ እና ትምህርት ዙሪያ ህብረተሰቡን ማሳተፍ ፣ እና ሌሎች ዘርፈ ብዙ ጉዳዮችን ይመለከታል።

ይህ ትብብር በሀዋሳ ከተማና አካባቢዋ ያሉ ልጆች የንባብ ክህሎት እና ልምድ ለማጎልበት አስፈላጊ ሚና ይኖረዋል።


የሚያነብቡ ያብቡ!!
‎የልጆች የንባብ ባህልን ለማሳደግ ኑ በጋራ እንስራ!!
‎የኢትዮጵያ ሪድስ የ ዩቲዩብ ቻናል ሼር፣ላይክ እና ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ!!

Ethiopia Reads has signed a Memorandum of Understanding (MoU) with the Department of Social Sciences at Hawassa University to collaborate on children's reading and education.
has entered into a partnership agreement with the Social Sciences Department of Hawassa University to improve the educational and reading skills of children in Hawassa city and its surrounding areas.
‎The signed agreement focuses on enhancing reading culture among children in the community, expanding libraries, jointly conducting various training and research activities, as well as engaging the community in reading and education initiatives, along with other multidisciplinary efforts.
‎This collaboration will play a significant role in strengthening the reading skills and habits of children in Hawassa and nearby areas.

‎*****************************************

‎Those who Read Bloom!!
‎Let’s work Together for Enhancing Children Reading Culture!!
Share, like and subscribe Ethiopia Read’s You Tube Channel and be a Family.

ኢትዮጵያ  ሪድስ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና ከአዲስ አበባ ሴቶች ፣ሕፃናት እና ማኀበራዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ Van Leer Foundation እና ፈረንሳይ ኤምባሲ ጋር በመተባበ...
23/03/2026

ኢትዮጵያ ሪድስ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና ከአዲስ አበባ ሴቶች ፣ሕፃናት እና ማኀበራዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ Van Leer Foundation እና ፈረንሳይ ኤምባሲ ጋር በመተባበር አቧሬ በሚገኘው የልጆች መጫወቻ ፓርክ የንባብ ፌስቲቫል አካሂዷል።
‎በቦታው ልጆች ከወላጆቻቸው ጋር የተገኙ ሲሆን ልዩ
‎ልዩ አዝናኝና አስተማሪ ትርኢቶችን በመመልከት፣በጨዋታ ፣ በንባብ ፣ ተረት በማድመጥ እና ሥዕል በመሣል ጊዜያቸውን አሳልፈዋል።
‎ተረት በማንበብ ውድድር ያደረጉ ወላጆችና ልጆችም ከኢትዮጵያ ሪድስ የሐገር ውስጥ ተጠሪ ወ/ሪ የምስራች ወርቁ እጅ የመጽሐፍ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።


‎………………………………………..
‎የሚያነብቡ ያብቡ!!
‎የልጆች የንባብ ባህልን ለማሳደግ ኑ በጋራ እንስራ!!
‎የኢትዮጵያ ሪድስ የ ዩቲዩብ ቻናል ሼር፣ላይክ እና ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ!!

Ethiopia Reads in collaboration with A.A city admnistration , A.A woman and children affair office, Van L‎eer foundation, and French Embassy have organized a children reading event in one of the playgrounds of Addis Ababa. Children attended the event together with their parents and spent their time enjoying various fun and educational activities. These included watching performances, playing games, reading, listening to stories, and drawing.
‎Parents and children who participated in the storytelling reading competition were awarded books by Ms. Yemisirach Worku, the Country Director of Ethiopia Reads.

‎*****************************************

‎Those who Read Bloom!!
‎Let’s work Together for Enhancing Children Reading Culture!! Share, like and subscribe Ethiopia Read’s You Tube Channel and be a Family.

"6 ኛው የልጆች ንባብ ጉባኤ እየተካሄደ ነው"‎‎ኢትዮጵያ ሪድስ በየአመቱ የሚያካሂደው የልጆች ንባብ ጉባኤ "የንባብን ችግኝ በቀዳማዊ ልጅነት መትከል " በሚል መሪ ቃል ካሳንችስ በሚገኘው ኢ...
18/03/2026

"6 ኛው የልጆች ንባብ ጉባኤ እየተካሄደ ነው"

‎ኢትዮጵያ ሪድስ በየአመቱ የሚያካሂደው የልጆች ንባብ ጉባኤ "የንባብን ችግኝ በቀዳማዊ ልጅነት መትከል " በሚል መሪ ቃል ካሳንችስ በሚገኘው ኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል መጋቢት 8ቀን 2018 ዓ.ም አካሂዷል።

‎የዘንድሮውን ንባብ ጉባኤ ኢትዮጵያ ሪድስ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስትራጄክ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጽፈት ቤት (SPMO)፣ ከትምህርት ሚኒስቴር እና ቫን ሊር ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር ነው ያዘጋጀው ።

‎በመድረኩ በሁለት ቋንቋዎች ማለትም በአማርኛና በአፋን ኦሮሞ የተዘጋጁ ከ0 እስከ 3 ዓመት እና 4 እስከ6 ዓመት ዕድሜ ላላቸው ሕፃናት የሚሆኑ 20 ሺህ መፅሐፍት አስመርቋል።

‎በጉባኤው ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የስራ ሐላፊዎች በልጆችና ሕፃናት ላይ የሚሰሩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ተወካዮች፣ ከአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ሐላፊዎችና ሌሎች ባለ ድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን በሕፃናት የንባብ ልምድ ላይ ያተኮሩ ጥናታዊ ጽሑፎች ላይ ውይይቶች እና የልምድ ልውውጥ አድርገዋል ። መርሐ ግብሩ በዛሬው ዕለትም ቀጥሎ ውሏል።


‎………………………………………..
‎የሚያነብቡ ያብቡ!!
‎የልጆች የንባብ ባህልን ለማሳደግ ኑ በጋራ እንስራ!!
‎የኢትዮጵያ ሪድስ የ ዩቲዩብ ቻናል ሼር፣ላይክ እና ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ!!









09/03/2026
የልጆች ንባብ ፌስቲቫል በድሬድዋ!ኢትዮጵያ ሪድስ ከፈረንሳይ ኤምባሲና ከአሊያንስ ኢትዮ- ፍራንሲስ ጋር በመተባበር እንደ ከ ዚህ በፊቱ  የልጆች ንባብ ፌስቲቫል በድሬደዋ ከተማ አካሄደ ፡፡"የ...
25/11/2025

የልጆች ንባብ ፌስቲቫል በድሬድዋ!

ኢትዮጵያ ሪድስ ከፈረንሳይ ኤምባሲና ከአሊያንስ ኢትዮ- ፍራንሲስ ጋር በመተባበር እንደ ከ ዚህ በፊቱ የልጆች ንባብ ፌስቲቫል በድሬደዋ ከተማ አካሄደ ፡፡

"የልጆች ንባብ ላይ እና ሁለንተናዊ ዕድገት ላይ በማተኮር የተሻለ ትውልድ እንፍጠር " በሚል መሪ ቃል ለሁለት ተከታታይ ቀናት አሊያንስ-ኢትዮ ፍራንሲስ ድሬደዋ ግቢ ዉስጥ የተካሄደው የልጆች ንባብ ፌስቲቫል በልዩ ልዩ ሁነቶች የደመቀ ሲሆን ልጆች በታዋቂዋ አለም ጸሃይ ወዳጆ የተጻፈዉን ጣይቱ ብጡል የተሰኘውን መጽሃፍ ጨምሮ ሌሎች የተለያዩ መጥሃፍትን በማንበብ ፣ ያነበቡትን መልሶ በመተረክ እና በመወያየት፣ሥዕል በመሳል ፣ ተረት እን የተለያዩ ታሪኮችን በማድመጥ ፣ ግጥም በማንበብ ፣ የጥያቄ እና መልስ ውድድር በማድረግ . እና በተለያዩ ንባብን በሚያበረታቱ እና በሚያዝናኑ ክንዋኔዎች አሳልፈዋል፡፡አሸናፊ ተማሪዎች የተለያዩ መጽሃፍቶችን በአሊያንስ ድሬዳዋ እና በኢተዮጵያ ሪድስ ተሸልመዋል፡፡
በቦታው ከ10 የመንግሥት ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ተማሪዎች የተገኙ ሲሆን በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የልጆች ካራክተር የሰራው ታዋቂው ኮሜዲያን አስረስ በቀለ ልጆችን እንዲያነቡ የሚመክር እና የሚያዝናኑ ልዩ ልዩ ዝግጅቶችን አቅርቧል፡፡



‎………………………………………..
‎የሚያነብቡ ያብቡ!!
‎የልጆች የንባብ ባህልን ለማሳደግ ኑ በጋራ እንስራ!!
Ethiopia Reads, in collaboration with the French Embassy and Alliance Ethio-Française, proudly hosted a vibrant Children’s Reading Festival in Dire Dawa City!
The two-day festival, held at the Alliance Ethio-Française Dire Dawa campus, celebrated children’s reading and holistic development under the theme:“Let’s create a better generation by focusing on children’s reading and holistic development.”
Children enjoyed a wide range of enriching and fun activities—reading diverse books including Taytu Bitul by the legendary Alem Tshehai Wedajo, retelling and discussing stories, drawing, listening to folk tales, reciting poems, engaging in Q&A competitions, and participating in many creative, literacy-boosting games.
Outstanding participants were recognized with book prizes from Alliance Dire Dawa and Ethiopia Reads. Students from 10 government schools took part, making the festival lively.We were also honored to have the renowned comedian Asres Bekele, creator of Ethiopia’s first children’s character, who energized the event with entertaining programs that inspired children to read more.
A heartfelt thank you to everyone who made this festival a joyful celebration of books, creativity, and learning!
Agegnehu

Those Who reads Bloom !

‹አንባቢ ህፃን የወደፊት ህይወቱ ብሩህ ነው፡፡› በማለት የሚመክረው የኢትዮጵያ ሪድስ/ Ethiopia Reads የዛሬው የክረምት መረሃ ግብር ተጋባዥ እንግዳ ደራሲ፣ ተርጓሚና የአዲስ አበባ ዩ...
18/09/2025

‹አንባቢ ህፃን የወደፊት ህይወቱ ብሩህ ነው፡፡› በማለት የሚመክረው የኢትዮጵያ ሪድስ/ Ethiopia Reads የዛሬው የክረምት መረሃ ግብር ተጋባዥ እንግዳ ደራሲ፣ ተርጓሚና የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የቀድሞ መምህር ዓለም እሸቱ ነው ፡፡
በዩኒቨርስቲ መምህሩ ትእዛዝ ‹በቀለና አዲሶቹ ቡቹሎች› በሚል ርዕስ ሀ ብሎ የጀመረው የልጆች ታሪክ ጹሁፍ ስራ ተወዳጅነት በማትረፉ ዛሬ ላይ ከ120 በላይ ታሪኮችን ሊያበረክትልን ችሏል፡፡
ከሚኖርበት ሐገር በቅርቡ ለእረፍት ወደ ሀገሩ የተመለሰው ደራሲ ዓለም እሸቱ "ገበታ" የልጆች ቤተ -መጽሐፍት በመገኘት ለልጆች ተረት በማንበብ ፣የንባብ ልምዱን በማካፈልና የተረት መጽሐፉን ለልጆች በመሸለም አስደሳች ጊዜ አሳልፏል፡፡


‎*******
‎የሚያነብቡ ያብቡ!!
‎የልጆች የንባብ ባህልን ለማሳደግ ኑ በጋራ እንስራ!!
‎የኢትዮጵያ ሪድስ የ ዩቲዩብ ቻናል ሼር፣ላይክ እና ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ!!


“A child who reads is a child with a bright future.”
Ethiopia Reads’ guest speaker for this year's summer program was Alem Eshetu; a writer, translator, and former Addis Ababa University teacher. His journey into children’s literature began with the story “Bekele and the New Puppies”, written at the request of one of his university instructors. Since then, his work has flourished, and he has authored over 120 stories that continue to inspire young readers.
Currently visiting Ethiopia for vacation, Alem Eshetu spent a delightful day at the “Gebeta” Children’s Library, where he read stories aloud, shared his personal reading experiences, and gifted his storybook to children as a special award.


***************************
Those who Reads Bloom !
Let's work together to cultivate children's reading!
Please share,like and subscribe Ethiopia Read's YOUTUBE channel

‹አንባቢ ህፃን የወደፊት ህይወቱ ብሩህ ነው፡፡› በማለት የሚመክረው የኢትዮጵያ ሪድስ/ Ethiopia Reads የዛሬው የክረምት መረሃ ግብር ተጋባዥ እንግዳ ደራሲ፣ ተርጓሚና የአዲስ አበባ ዩኒቨርስ...

 🎉🎉🎉  🎉🎉🎉Ethiopia Reads/ኢትዮጵያ ሪድስ
11/09/2025

🎉🎉🎉
🎉🎉🎉
Ethiopia Reads/ኢትዮጵያ ሪድስ

‎120 በላይ ልጆች የተሳተፉበት የ"ገበታ" የልጆች ቤተ -መጽሐፍት የክረምት መረሃ ግብር ቅዳሜ ነሐሴ24 ቀን 2017 ዓ.ም የመዝጊያ መርሃ ግብር አካሂደዋል ።‎በቦታው ጥሪ የተደረገላቸው እ...
02/09/2025

‎120 በላይ ልጆች የተሳተፉበት የ"ገበታ" የልጆች ቤተ -መጽሐፍት የክረምት መረሃ ግብር ቅዳሜ ነሐሴ24 ቀን 2017 ዓ.ም የመዝጊያ መርሃ ግብር አካሂደዋል ።

‎በቦታው ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ የአካባቢው ነዋሪዎችና የክረምት መርሃ ግብር ተሳታፊ ልጆች ወላጆች የተገኙ ሲሆን ልጆችም ግጥም፣ መዝሙር ፣ የቃላት ጨዋታና ቴአትር አቅርበዋል።

‎ልጆቹ በነበራቸው ቆይታ ለቀጣይ ዓመት መደበኛ ትምህርታቸው ድጋፍ እንዲሆናቸው በበጎ ፈቃደኛ ወጣቶች የሂሳብ፣ የቋንቋና የሌሎችም ትምህርት ዓይነቶች ጥናት እንዲያደርጉ ድጋፍ ሲደረግላቸው ቆይተዋል።

‎በቦታው የተገኙ ወላጆች ልጆቻቸው የእረፍት ጊዜያቸውን በዚህ መልኩ ማሳለፋቸው እንዳስደሰታቸው የገለጹ ሲሆን፣ ልጆቹም በቤተ-መጽሐፍቱ በማሳለፋቸው በራስ የመተማመን አቅማቸው የጎለበተና በትምህርታቸውም ለውጥ ማምጣታቸውን ተናግረዋል።


‎*******
‎የሚያነብቡ ያብቡ!!
‎የልጆች የንባብ ባህልን ለማሳደግ ኑ በጋራ እንስራ!!
‎የኢትዮጵያ ሪድስ የ ዩቲዩብ ቻናል ሼር፣ላይክ እና ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ!!

‎በግብርናና አካባቢ ጥበቃ ላይ ትኩረቱን አድርጎ የሚንቀሳቀሰው     አባላት  አትዮጵያ ሪድስ "ገበታ" ቤተ መጽሐፍት ረቡዕ 21 ቀን 2017 ዓ.ም  በመገኘት ለክረምት መርሃ ግብር  ተጠቃሚ...
29/08/2025

‎በግብርናና አካባቢ ጥበቃ ላይ ትኩረቱን አድርጎ የሚንቀሳቀሰው አባላት አትዮጵያ ሪድስ "ገበታ" ቤተ መጽሐፍት ረቡዕ 21 ቀን 2017 ዓ.ም በመገኘት ለክረምት መርሃ ግብር ተጠቃሚ ልጆች ስለ ንብ ማነብና ማር ጠቀሜታ በማስተማር አሳልፈዋል ።
‎ልጆች ከልጅነታቸው ጀምሮ አካባቢያቸውን፣ ተፈጥሮን እንዲያቁና ግንኙነት እዲኖራቸው፤ በተለይም ትልቅ ጠቀሜታ ያለው ነገር ግን በሀገራችን ብዙም ትኩረት ተሰጦበት እየተሰራበት ስላልሆነው የንብ ማነብ ስራ እና የማር ጠቀሜታን በተመለከተ መሰረታዊ ትምህርት ወስደዋል።
‎በመጨረሻም ከልጆቹ ጋር "የላሊበለዋ ንብ አርቢ" የተሰኘ የተረት መጽሐፍ በማንበብ አስደሳች ጊዜ አሳልፈዋል።
‎ /ኢትዮጵያ_ ሪድስ

‎🌱🌱🎍🎍🌴🌴🌵🌵🌾🌼🌸🌺🌷🌧🍓🍍🌱🌱🎍🎍🌴🌴🌵🌵🌾🌼🌸🌺🌷🌧🍓🍍

‎***
‎የሚያነብቡ ያብቡ!!
‎የልጆች የንባብ ባህልን ለማሳደግ ኑ በጋራ እንስራ!!
‎የኢትዮጵያ ሪድስ የ ዩቲዩብ ቻናል ሼር፣ላይክ እና ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ!!

‎የ"ቡሄ" ሥዕል አውደ ርዕይ በህፃናት!‎ኢትዮጵያ ሪድስ ሀዋሳ ንባብ ማዕከል እና አዲስ አበባ ቀበና በሚገኘው "ገበታ"  የልጆች ቤተ- መጽሐፍት  የክረምት መርሃ ግብር  ተሳታፊ  ልጆች በቆ...
22/08/2025

‎የ"ቡሄ" ሥዕል አውደ ርዕይ በህፃናት!
‎ኢትዮጵያ ሪድስ ሀዋሳ ንባብ ማዕከል እና አዲስ አበባ ቀበና በሚገኘው "ገበታ" የልጆች ቤተ- መጽሐፍት የክረምት መርሃ ግብር ተሳታፊ ልጆች በቆይታቸው የሰራቸውን ሥዕሎች የቡሄ በአል ሲያከብሩ ለዕይታ አቅርበዋል።

‎**********************************
‎የሚያነብቡ ያብቡ!!
‎የልጆች የንባብ ባህልን ለማሳደግ ኑ በጋራ እንስራ!! የኢትዮጵያ ሪድስ የ ዩቲዩብ ቻናል ሼር፣ላይክ እና ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ!!

"ቡሄ" በገበታ ቤተ_መጽሐፍት!‎ ‎ኢትዮጵያ ሪድስ በየዓመቱ እንደሚያደርገው በ2017ዓ.ም ለገበታ የቤተ -መጽሐፍት ተጠቃሚ ህፃናትን የእረፍት ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙበት  የክረምት መ...
20/08/2025

"ቡሄ" በገበታ ቤተ_መጽሐፍት!

‎ኢትዮጵያ ሪድስ በየዓመቱ እንደሚያደርገው በ2017ዓ.ም ለገበታ የቤተ -መጽሐፍት ተጠቃሚ ህፃናትን የእረፍት ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙበት የክረምት መርሃ ግብር አዘጋጅቷል፡፡
ህፃናቱ በባለሙያዎችና በበጎ ፈቃደኛ ወጣቶች እየታገዙ በንባብ ፣ ቋንቋ፣ የስዕልና የተለያዩ የትምህርት ዓይነቶችን ብቃታቸውን በማዳበር ለቀጣዩ ዓመት ትምህርት ዘመን እየተዘጋጁ ይገኛሉ፡፡
‎ነሐሴ 13 የሚከበረውን የደብረ ታቦር (ቡሄ) በአልን የገበታ ቤተ -መጽሐፍት ተጠቃሚ ህፃናት በዚህ መልኩ አክብረውታል።
‎**********************************
‎የሚያነብቡ ያብቡ!!
‎የልጆች የንባብ ባህልን ለማሳደግ ኑ በጋራ እንስራ!! የኢትዮጵያ ሪድስ የ ዩቲዩብ ቻናል ሼር፣ላይክ እና ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ!!

Ethiopia Reads once again hosted its annual Summer Camp Program in 2025 at the Gebeta Library, creating a meaningful space for children to spend their free time in a productive and enjoyable way.
With guidance from dedicated professionals and enthusiastic youth volunteers, the children took part in reading, language activities, art, and a variety of educational exercises designed to strengthen their skills and prepare them for the upcoming school year.
On August 18, during the celebration of Debre Tabor (Buhe) holiday, the Gebeta Library children marked the occasion with joy and creativity.
Those Who Read, Bloom!

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopia Reads/ኢትዮጵያ ሪድስ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Ethiopia Reads/ኢትዮጵያ ሪድስ:

Share