30/07/2025
ፕሮ ደቨሎፕመንት ኔትዎርክ ከ አየርላንድ ኤምባሲ ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ አማካኝነት ከኢትዮጵያ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ጋር በጋራ በመሆን ትናንት ማለትም ሃምሌ 22 ቀን 2017 ዓ/ም የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አዋጅ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ላይ የምክክር መድረክ አዘጋጅቷል፡፡
በመድረኩም የተለያዩ ድርጅቶች ተወካዮች፣ በዘርፉ የተሰማሩ ባለሙያዎችና ከተለያዩ ክልሎች ማለትም ከአማራ ክልል፤አፋር ክልል፤ ቤንሻንጉልጉሙዝ፤ ሶማሌ ክልል እንድሁም ትግራይ ክልል የመጡ የሲቪል ማህበረሰብ ተዎካዮች ተሳትፈዋል፡፡
በውይይቱ መጀመሪያ ማሻሻያ የተደረገባቸው ድንጋጌዎች በባለሙያ የቀረቡ ሲሆን ከዚያ በመቀጠል በረቂቅ አዋጁ ዙሪያ የተለያዩ ጥያቄዎችና ገንቢ ሃሳቦች ተነስተዋል፡፡ ከተነሱ ጥያቄና ሃሳቦች መካከል፣ ረቂቅ አዋጁ ለትርጉም የተጋለጡ አንቀዖችን አካቷል አላካተተም? በረቂቅ አዋጁ ዙሪያ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ድርሻው ምን ይመስላል? በዚህ ዙሪያ የሁሉም የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ድርሻ ምን መሆን አለበት? ማሻሻያው ጥናትን መሰረት ያደረገ ነው ወይስ? እንድሁም የዚህ አዋጅ መጽደቅና ስራ ላይ መዋል በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ላይ የሚፈጥረው ተጽእኖስ ምን ይመስላል? የሚሉና የመሳሰሉ ሃሳቦች ተነስተዋል፡፡
With financial support obtained from Ireland Embassy, Pro Development Network, in collaboration with the Ethiopian Civil Society Organizations council organized a consultation workshop on July 29, 2025 on the draft amendment to CSO proclamation No. 1113/2019.
Different participants from different organizations, professionals with expertise in the field, and Civil Society representatives from different regions, namely, Amhara, Afar, Beninshangul gumuz, Somalia & Tigray regional states, attended the workshop.
At the beginning of the discussion, an expert presented the amendments made to the proclamation and then participants raised various questions and constructive ideas regarding the draft proclamation. Among the issues raised were, are the amended provisions of the proclamation open for interpretation? What was the role of the civil society organizations council in the process of the amendment? What should be the role of all civil society organizations in this regard? Is the amendment research based or not? Moreover, there were reflections on the impact of the ratification and implementation of the proclamation on civil society organization.
July 29,2025
Aya Hotel
Addis Ababa, Ethiopia