Kemer development & Charity organization

Kemer development & Charity organization ቀመር የበጎ አድራጎት ድርጅት በኢትዮጵያ ሲቪል ማሀበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ህጋዊ እዉቅና ያለው ተቋም ነዉ

14/09/2025

📌 !

▸ በሌሎች ለመወደድ ያለህን ፍላጎት አስወግድ፦ ምንም ሰራህ ምን ሁሌም ድርጊትህን የሚቃወሙ ሰዎች መኖራቸው አይቀርም።

▸ መርዘኛ ባህሪ ያላቸው ሰዎችን አስወግድ፦ መልካም አመለካከት የሌላቸውን ሰዎች በዙሪያ ይዞ ስኬታማ መሆን አይቻልም።

▸ ሁሉንም ነገር ለመቆጣጠር ያለህን ፍላጎት አስወግድ፦ የተወሰኑ ነገሮች ለኛ አብዛኞቹ ደሞ ለኛ እንዳልሆኑ መረዳት ።

▸ ሁሌም ፍፁም ለመሆን ያለህን ፍላጎት አስወግድ፦ ፍፁም ለመሆን ማሰብ ባንተ ላይ ከፍተኛ ግፊት ያሳድራል ስለሆነም በተግባርህ ጥሩ ከሆንክ ይበቃል።

▸ በፍጥነት ስኬት ላይ ለመድረስ ያለህን እምነት አስወግድ (Overnight Success)፦ ስቲቭ ጆንስን ጨምሮ ማንም በአንዴ ስኬታማ የሆነ የለም።

▸ ትንንሽ ህልሞችን አስወግድ፦ ራዕይህ ትልቅ ካልሆነ መቼም ትልቅ ነገር አታሳካም።

▸ ጤናማ ያልሆኑ የህይወት መንገዶችን አስወግድ፦ አካልህ ቤትህ ነው ስለሆነም ስኬትህ ላይ ለመድረስ ጤናማ መሆን አለብህ።

Kemer development & Charity Organization
01/06/2025

Kemer development & Charity Organization

25/04/2025

ድርጅት አቋቁሙ
~
ለመስጂድ ማሰሪያ፣ የተቸገሩን ለመርዳት ከበጎ ፈቃደኞች ገንዘብ መሰብሰብና ማስተባበር በቁርኣንና በሐዲሥ መሰረት ያለው ትልቅ ኸይር ነው። ይሄ በተቋም ደረጃም ይፈፀም፣ በግለሰብ ደረጃም ይፈፀም የሚደነቅ እንጂ የሚወገዝ ተግባር አይደለም። እንዲያውም ቁርኣን ውስጥ ደካሞችን በማገዝ ላይ አላማነሳሳት ነው የከሃዲዎች ተግባር እንደሆነ ተወግዞ የምናገኘው። አላህ እንዲህ ይላል፦
{ أَرَءَیۡتَ ٱلَّذِی یُكَذِّبُ بِٱلدِّینِ (1) فَذَ ٰ⁠لِكَ ٱلَّذِی یَدُعُّ ٱلۡیَتِیمَ (2) وَلَا یَحُضُّ عَلَىٰ طَعَامِ ٱلۡمِسۡكِینِ (3) }
"ያንን በምርመራው የሚያስተባብለውን አየህን? (ዐወቅከውን?) ይህም ያ የቲምን በኀይል የሚገፈትረው፤ ድሃንም በማብላት ላይ የማያግባባው ሰው ነው።" [አልማዑን፡ 1-3]

ነብያችንም ﷺ በተደጋጋሚ ሰዎችን ለሶደቃ አነሳስተዋል። በዒድ ቀን ሴቶችን ለሶደቃ ቀስቅሰዋል። መስጂድ ላይ ከሙዶር ጎሳ ለሆኑ ችግረኞች እርዳታ ሰብስበዋል።

ስለዚህ በዚህ ተግባር ላይ የተሰማሩ አካላትን ልመና ላይ ተሰማርተዋል እያሉ ማንቋሸሽ በማንም ቢነሳ ተቀባይነት የሌለው ትችት ነው። "ረቢዕ እንዲህ ብለዋል"፣ "ሙቅቢል እንዲህ ብለዋል"፣ "ሙሐመድ ብኑ ሃዲ እንዲህ ብለዋል" እያዩ የተንጓለሉ ጥቅሶችን ማራገብ አጉል ጭፍን ተከታይነት ነው።
1ኛ፦ የነሱን ንግግር ባልተገባ መልኩ ከኸይር ስራ ማሰናከያ እያደረጉ መመንዘር አይገባም።
2ኛ፦ ከከልካዮቹ በዒልምም በብዛትም የሚልቁ ዓሊሞች ፈተዋዎች እጅግ ብዙ ናቸው።
3ኛ፦ ከምንም በላይ የቁርኣንና የሐዲሥ ማስረጃ ያለው ከሚፈቅዱት ጋር ነው። ለኸይር ስራ እርዳታ ማሰባሰብን የሚነቅፍ አንድም መረጃ የለም።
አለኝ የሚል ካለ በአደብ ማቅረብ ይችላል። ከነጥብ ከወጣ፣ ከአደብ ካፈነገጠ አስወግዳለሁ።

ተግባሩ ላይ የተሰማሩት እምነት የማይጣልባቸው መሆናቸው ከተረጋገጠ ያኔ ለይተን እንናገራለን። ሂደቱ ላይ ስህተት ከታየም እንዲሁ ነጥሎ ስህተቱን ብቻ ለማረም መሞከር ነው። እንጂ በደፈናው እያወገዙ ደካሞች የሚታገዙበትን ስራ ማሰናከል የተሳሳተ አካሄድ ነው።

የሚገርመው እንዲህ አይነቱን ተግባር ልመና እያሉ የሚያጣጥሉ አካላት ራሳቸው የተቸገረን ለመርዳት፣ መስጂድ ለመገንባት፣ የራሳቸውን ቡድናዊ ተግባር ለመፈፀም ሲሆን ልመና ላይ የሚሰማሩ መሆናቸው ነው። ለምን? የሚወገዘው ተግባሩ ሳይሆን አተገባበሩ ከሆነ በጅምላ እያወገዝክ የተዛባ መልእክት አታስተላልፍ። የሚወገዘው ተግባሩ ሳይሆን እንደ ፈፃሚዎቹ ማንነት ሑክሙ የሚለያይ ከሆነ ይሄ ዲን ሳይሆን ቡድንተኝነት ነው።

ለማንኛውም ፕሮጀክት መቅረፅ፣ ፈንድ ማሰባሰብ የምትችሉ አቅሙ ያላችሁ ወገኖች ድርጅት እየከፈታችሁ አካባቢያችሁን አግዙ። ወገናችሁን እርዱ። መስጂዶችን ስሩ። መሻይኾችን አቋቁሙ። የቲሞችን አልብሱ። ትምህርት ቤት፣ ሃኪም ቤት ስሩ። ውሃ አውጡ። በጦርነት ወይም በሌላ ምክንያት ህይወታቸው የተመሰቃቀለባቸውን ወገኖች በምትችሉት ከጎናቸው ቁሙ። እነዚን ስራዎች እየሰሩ ነው እምነት የሚያስቀይሩ ሚሺነሪዎች ወገኖቻችን ላይ እየዘመቱ ያሉት።
ኮፒ

ስልጣኔ የሚፈርስባቸው ሶስት መንገዶች~ ~ ~ ~ ~ ~~~~ ~ ~ ~ ~ ~ ~~~ጥንታውያኑ ቻይናውያን በሰላም መኖር ቢያምራቸው ታላቁን የቻይና ግንብ ገነቡ። ቁመቱ ክፍ ያለ ከመሆኑ የተነሳ ...
08/10/2024

ስልጣኔ የሚፈርስባቸው ሶስት መንገዶች
~ ~ ~ ~ ~ ~~~~ ~ ~ ~ ~ ~ ~~~
ጥንታውያኑ ቻይናውያን በሰላም መኖር ቢያምራቸው ታላቁን የቻይና ግንብ ገነቡ። ቁመቱ ክፍ ያለ ከመሆኑ የተነሳ ማንም አይወጣበትም፣ ማንም አይደርስብንም ብለው አምነዋል። ነገር ግን...
ግንቡ በተገነባ የመጀመሪያው መቶ አመት ውስጥ ብቻ ቻይና ሶስት ጊዜ ለጠላት ወረራ ተጋለጠች። በያንዳንዱ ወረራ ጊዜ ግዙፉ ወራሪ ሀይል ታላቁን የቻይና ግንብ መስበርም መንጠላጠልም አላስፈለገውም ነበር። እናስ? ሰተት ብለው ነበር በበሩ የሚገቡት። እንዴት አድርገው? ቀላል ነበር። ለግንቡ በረኞች፣ ለዘበኞቹ ጉቦ ይሰጣሉ። ከዚያ ነገሩ ሁሉ ያልቃል።
ቻይናውያን በዙሪያቸው ግዙፍ ግንብ በመገንባት ሲጠመዱ ዘበኛ መገንባት ግን ዘንግተዋል። ስብእናን መገንባት ሌሎች ነገሮችን ከመገንባት የሚቀድም ነገር ነው። ይሄ ጉዳይ ትኩረት ሊቸረው የሚገባ ጉዳይ ነው። አንዱ የምስራቁን ዓለም ታሪክና ትውፊት የሚያጠና ተመራማሪ (ኦሬንታሊስት) እንዲህ ይላል፡-

“የአንድን ህዝብ ስልጣኔ ማፈራረስ ከፈልግክ ሶስት መንገዶች አሉልህ፡-
1. ቤተሰብን ማፍረስ፣
2. የትምህርት ስርአቱን ማፍረስ እና
3. መልካም ምሳሌና አርኣያ የሆኑ ሰዎችን ስብእና ማጠልሸት።

* ቤተሰብን ለማፍረስ እናት ሚናዋን እንዳትወጣ አድርጋት። “የቤት እመቤት” በመባሏ እንድታፍር አድርጋት።
* የትምህርት ስርኣቱን ለማፍረስ አስተማሪው ላይ አነጣጥር። ህብረተሰቡ ጋር ያለውን ቦታ አሳጣው። ተማሪዎቹ ይንቁት ዘንድ ደረጃውን አውርደው።
* አርአያዎችን ለማፍረስ ዓሊሞች ላይ አነጣጥር። አንቋሻቸው። ዋጋ አሳጣቸው። ማንነታቸውን ሰዎች እንዲጠራጠሩ አድርግ። ያኔ ሰዎች አይሰሟቸውም። ምሳሌም አያደርጓቸውም።

• አስተዋይ እናት ከጠፋች፣
• ከልቡ የሚሰራ አስተማሪ ከጠፋ፣
• ምሳሌ ሊሆኑ የሚችሉ ሰዎች ዋጋ ካጡ፣
ማነው ትውልዱን በመልካም ስነ-ምግባር የሚያንፀው?
=====
ከዐረብኛ የተመለሰ
ኢብኑ ሙነወር
የቴሌግራም አድራሻ፦

08/10/2024
11/11/2023

በህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የፋርማሲ ት/ቤት ለተማሪዎቹ ሞዴል የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ሰጠ።
***************************
ግንቦት 8/2015 ዓ.ም
በሀዋሳ ዩኒቨርሰቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ለአምስተኛ አመት የፋርማሲ ትምህርት ክፍል ተማሪዎች ሞዴል የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና (Exit Exam) መስጠት ተጀምሯል::

የፋርማሲ ት/ቤት ኃላፊው አቶ ሕዝቅኤል ኤንጊሶ ስለፈተናው አላማ ሲያብራሩ ተማሪዎቻችን በእስካሁኑ ዝግጅታቸው ምን አይነት ደረጃ ላይ እንደሚገኙ ራሳቸውን እንዲገመግሙና የትምህርት ክፍሉም በቀጣይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ያለበትን ስራ ለማወቅ መሆኑን ገልጸዋል። ኃላፊው አክለውም ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ይሰጣል ከተባለበት ጊዜ አንስቶ በአጠቃላይ በኮሌጁ ደረጃ ብሎም እንደ ፋርማሲ ትምህርት ቤት በርካታ የስነ-ልቦና ዝግጅትና በፈተናው ይዘቶች ላይ ለተማሪዎች ገለጻና የማጠንከሪያ ትምህርት ሲሰጥ መቆየቱን አስታውሰው በአሁኑ ወቅት የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተናው ሊሰጥ የሁለት ወራት ጊዜ ያህል ብቻ የቀረው በመሆኑ ይህን ሞዴል ፈተና ለማዘጋጀት መወሰኑን ተናግረዋል።

የፋርማሲ ትምህርት ክፍል አስተባባሪው አቶ ሙሉቀን አልታዬ በበኩላቸው በትምህርት ክፍሉ የተዘጋጀው ሞዴል ፈተና ዋናው የመውጫ ፈተና የሚያተኩርባቸውን ኮርሶች በመለየት የተዘጋጀ የመለማመጃ ፈተና በመሆኑ ተማሪዎች በዚህ ፈተና የሚያስመዘግቡትን ውጤት በመመልከት ምን ያህል ዝግጅት ማድረጋቸውን መገምገም ይቻላል ብለዋል።
አቶ ሙሉቀን ጨምረውም ፈተናው በኦንላየን መሰጠቱ ቀደም ሲል በዩኒቨርሲቲው በነበራቸው ቆይታ ከለመዱት የወረቀት የፈተና አሰጣጥ በአቀራረቡ የተለየ ቢመስልም በይዘት ግን ልዩነት የሌለው መሆኑን ተማሪዎች በመገንዘብ ከአላስፈላጊ ጭንቀት ራሳቸውን መጠበቅ እንደሚገባቸውና በዚህኛው ዙር የሞዴል ፈተና ራሳቸውን አይተው እንደ ፋርማሲ ትምህርት ቤት በሚዘጋጀው ሁለተኛ የሞዴል ፈተና በደንብ ተዘጋጅተው ለመቅረብ እንዲሰሩ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

Address

Addis Ababa

Telephone

+251942586080

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kemer development & Charity organization posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share