Public Information Noble PIN

Public Information Noble PIN ''Building a better Ethiopia through access to information" "Unlocking the PIN to information access

05/03/2026

እወቅ
Be informed...✍️

30/12/2025

መረጃ በሚከለክሉ የመንግሥት ኃላፊዎች ላይ የተቀመጠው
ቅጣት ወደ 150 ሺ ብር ከፍ እንዲል ተጠየቀ

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኀን ምክር ቤት፣ የመረጃ ነጻነት ረቂቅ አዋጅ መረጃ በሚከለክሉ የመንግሥት ኃላፊዎች ላይ ያስቀመጠው የቅጣት መጠን ከ20 ሺሕ ወደ 150 ሺሕ ብር ከፍ እንዲል ትናንት በጉዳዩ ዙሪያ አዲስ አበባ ውስጥ ባካሄደው ውይይት ላይ ጠየቀ።

ምክር ቤቱ፣ የመንግሥት ሃላፊዎች የሰነድ መረጃ መስጠት ባልቻሉ ጊዜ በቃለ መጠይቅ ተጨማሪ መረጃ እንዲሠጡ የሚያስገድድ አንቀጽ በመረጃ ነጻነት ረቂቅ አዋጁ ውስጥ እንዲካተት ምክረ ሃሳብ አቅርቧል።

ረቂቅ አዋጁ የመንግሥት ሃላፊዎች በ48 ሰዓት ውስጥ ለመረጃ ጥያቄ ምላሽ እንዲሠጡ ያስገድዳል።

ምክር ቤቱ በበኩሉ፤ ለአስቸኳይ ኹኔታዎች ከ48 ሰዓት ባነሰ ጊዜ ውስጥ የተቋማት ሃላፊዎች ለመረጃ ፈላጊዎች መረጃ መስጠት አለባቸው የሚል አንቀጽ ጭምር ይካተት በማለት አሳስቧል ስትል ዋዜማ ዘግባለች፡፡

የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
AdissAdmas
Public Information Noble PIN

Access to information
30/12/2025

Access to information

30/12/2025

Tomorrow on Youth Network Ethiopia – Join Us!

መረጃ የማግኘት መብት እና የሕግ ግንዛቤ ‼️
Access to Information & Legal Awareness ‼️

🗓 Date: December 31, 2025

This session will empower young people to understand their right to access information, strengthen legal awareness, and become informed, responsible citizens.

🔗 Join us on Telegram:
https://t.me/YNE123

👥 Invite your friends and networks
📲 Be part of the conversation!





27/10/2025
01/09/2025

Corruption in Ethiopia remains a deep wound draining public resources, silencing justice, and holding back progress. We must demand transparency, accountability, and integrity at every level.

23/04/2025

የግል ዳታ ጥበቃ በኢትዮጵያ ህግ
#መግቢያ
በዚህ ባለንበት ዘመን በፍጥነት እያደገ የሚገኘው የዲጂታል ግንኙነት ቴክኖሎጂ ዘርፈ ብዙ እድሎችና ጠቀሜታዎችን እያስገኘ የሚገኝ የፈጠራ እድገት መሆኑ ይታወቃል። በመሆኑም መረጃዎች ቀድሞ ከነበሩበት እጅግ በላቀ ፍጥት እና ጥራት በቀላሉ ለመላው የዓለም ህዝብ ተደራሽ እየሆኑ የሚገኙበት የማይተነበይ የዲጂታል ዘመን ላይ እንገኛለን። ከዚህ በመነሳት ሀገራት ይህ ፈጣን የመረጃ ልውውጥ በዜጎች የግል ህይወትና በአገራዊ ደህንነት ላይ የሚያመጣውን አሉታዊ ተጽዕኖ ለመቆጣጠር ልዩ ልዩ የቁጥጥር ስርዓቶችን ተግባር ላይ ያውላሉ። እንደምሳሌ፣ በጋና የዳታ ጥበቃ ኮሚሽን (Data Protection Commission) የሚባል ተቋም በህግ የተቋቋመ ሲሆን አጠቃላይ የዳታ ምዝገባ፤ ማቀናበር፣ የማስተላለፍ ሂደትን መቆጣጠርና ከጥሰት ጋር የተያያዙ ልዩ ልዩ እርምጃዎችን የሚወስድ ተቋም ነው።

ከዚህ አንፃር በእኛም ሀገር በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ-መንግስት በግልጽ ሰፍሮ እንደምናገኘው ዜጎች በአካላቸው ላይ እንዲሁም፣ በግል ባለቤትነት፣ አመንጭነት ወይም በተለየ መንገድ ግላዊ ይዘት ያላቸው መረጃዎችና ግንኙነቶች በህግ ጥበቃ ያላቸው የነፃነት መብቶች መሆናቸው ተመላክቷል። በአንፃሩ እነዚህ ጥብቅ ጥንቃቄ የሚሹ የግልና አገራዊ መረጃዎች በአልተገባ መንገድ በቀላሉ በሶስተኛ ወገን እጅ እየገቡ ብሎም የሚዲያ ፍጆታ ሆነው ሰፊ ፖለቲካዊና ማህበረሰባዊ ጉዳት ሲያስከትሉ ማየት ውሎ አድሯል።

በአገራችን እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ይህንን የመብት ክፍል ለመጠበቅ የወጣ የተለየ ህግም ሆነ የተቋቋመ መስሪያ ቤት አልነበረም። ከዚህ ይልቅ እዚም አዛም ተበታትነው በሚገኙ ድንጋጌዎች፣ ወጥነት በሌለው የአሰራር ሂደትና በየተቋማቱ በሚወሰዱ ልዩ ልዩ እርምጃዎች ሲተዳደር ኖሯል። ይሁን እንጂ በ2016 ዓ.ም ይህንን ችግር ሊቀርፍ የሚችል“የግል ዳታ ጥበቃ አዋጅ” ‘’አዋጅ ቁጥር 1321/2016’’ የተሰኘ ህግ ጸድቆ በስራ ላይ ይገኛል። በዚህ ጽሁፍም በዚህ ህግ የተሸፈኑ ዋና ዋና ጉዳዮች ማለትም፣ ስለ ግል ዳታ ምንነት፣ የጥበቃ ስርዓቱ፣ የሚተላለፍበት መንገድና ዝርዝር ግዴታዎችን መተላለፍ የሚያስከትለውን ህጋዊ ተጠያቂነት ለመዳሰስ ተሞክሯል። በመጨረሻም “ዳታ” የሚለው ቃል በአማርኛ መረጃ በተለይም የግል መረጃ የሚለውን አገላለጽ የሚተካ ቢሆንም በአዋጁ ጥቅም ላይ የዋለው የእንግሊዝኛው የግል ዳታ (Personal data) የሚለው ስለሆነ ለተሻለ ግልጽነት በዚህ ጽሁፍም ይኸው ቃል ጥቅም ላይ ውሏል።

ዳታና የግል ዳታ ምንነት
በአገራችን ያለው የዳታ ጥበቃ ስርዓት ገና በጅማሮ ላይ የሚገኝ ከመሆኑ የተነሳ የዳበረ ስርዓት ያለቸው አገራት ለጉዳዩ የሰጡትን ትርጉም መመልከት ተገቢ ይሆናል። በዚህም ለምሳሌ የኖርዋይ መንግስት ዳታ ጥበቃ ባለስልጣን የግል ዳታን ሲተረጉም፣ “Personal data is any kind of information that can be related to an identifiable person…. that may include information on name, address, e-mail address, personal identification number, registration number, photo, fingerprints, diagnostics, biological material, when it is possible to identify a person from the data or in combination with other data.” በማለት ይገልጸዋል። ይህም አባባል በአጭሩ “የግል ዳታ ማለት ከአንድ የታወቀ ግልሰብ ጋር የተቆራኙ ግላዊ መረጃዎችን የሚያመለክት ሆኖ እንደ ስም፣ አድራሻ፣ መለያ ቁጥር፣ የአሻራ መለያ፣ የምዝገባ ቁጥር፣ የጤና ምርመራ ውጤት፣ ፎቶ፣ ኢሜል፣ እና ስነ-ህይወታዊ መረጃዎችን (እንደ DNA) ሊይዝ ይችላል። ይህም መረጃ አስፈላጊ በሆነበት ጊዜ ሁሉ በራሱ ካልሆነም ከሌላ መሰል መረጃ ጋር በማነፃጸር የሰውየውን ማንነት ለመለየት ያገለግላል ማለት ነው።

በዚህ መነሻነት ወደ እኛ ህግ ስንመጣ የግል ዳታ ጥበቃን ለመደንገግ በወጣው አዋጅ ቁጥር 1321/2016 ዓ.ም አንቀጽ 2(1) ላይ አስቀድሞ “ዳታ” ለሚለው ቃል እንደሚከተለው ራሱን የቻለ ፍች ሰጥቶታል። በዚህም ዳታ ማለት፣
ሀ) ለታቀደ ዓላማ አስቀድሞ በተሰጠው ትእዛዝ መሰረት ራስ አዘዝ በሆነ መሳሪያ በመቀናበር ሂደት ላይ ያለ፤ “ራስ አዘዝ መሳሪያን እንግሊዝኛው (Operating Automatically) ይለዋል።
ለ) በፊደል ተራ (ሀ) በተጠቀሰው መሳሪያ እንዲቀናበር ታሰቦ የተሰበሰበ፤
ሐ) በአንድ የመዝገብ ሥርዓት አካል እንዲሆን ወይም የመዝገብ ሥርዓቱ የተወሰነ ክፍልን ለማሟላት ታቅዶ የተመዘገበ፤ ወይም
መ) በፊደል ተራ (ሀ)፣ (ለ) እና (ሐ) ሥር የማይወድቅ ነገር ግን ሌላ ለሕዝብ ተደራሽና የመዝገብ አካል የሆነ፤ መረጃ ነው በሚል ተርጉሞታል። በሌላ በኩል ለግል ዳታ የሰጠውን ትርጉም ስንመለከት፣-
የግል ዳታ የሚለውን አገላለጽ በሚመለከት ከሞላ ጎደል ከላይ ከሰፈረው ትርጉም ጋር ተቀራራቢ የሆነ ትርጉም በአንቀጽ 2(2) ላይ እንደሚከተለው ሰፍሮ እናገኛለን፣ “የግል ዳታ” ማለት በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ በተለይም ስምን፣ መለያ ቁጥር ፣ የስልክ ቁጥርን ፣ የኢንተርኔት መለያ አድራሻን ፣ የቦታ ዳታን ፣ የኦንላይን መለያን ወይም ከአንድ በላይ ከሆኑና ከአንድ የተፈጥሮ ሰው ጋር ተያያዥ ከሆኑ የአካላዊ ፣ የፊዚዎሎጂ ፣ የዘረ-መል፣ የአዕምሮ፣ የኢኮኖሚ፣ የባህል ወይም የማህበራዊ ሁኔታዎች ጋር ተያያዥ የሆኑ መለያዎችን በመጠቀም ተለይቶ ከሚታወቅ ወይም ተለይቶ ሊታወቅ ከሚችል የተፈጥሮ ሰው ጋር የተገናኘ ማንኛውም መረጃ ነው ሲል ያስቀምጣል።

እዚህ ላይ ከላይ ከተመለከትነው ትርጉም የሚለየው አዋጁ ጥበቃ የሰጠው በተፈጥሮ ሰው የተያዘ የግል ዳታ ብቻ መሆኑ ነው። ከዚህ ጋር በተያያዘ በአንቀጽ 2(9) የግል ዳታ ባለቤት-” ማለት በግል ዳታ ላይ ባለቤት የሆነ የተፈጥሮ ሰው ነው፤ የሚል ግልጽ ድንጋጌም ይገኛል። ይህ አገላለጽ የህግ ሰውነት ባላቸው ተቋማት የተያዙ ዳታዎችን በተለይም ከንግድ፣ ከውል፣ ከምዝገባና መሰል ጉዳዮች ጋር በተያያዘ ሊኖሩ የሚችሉ ዳታዎችን ጥበቃ የሚያሳጣ ቢሆንም በሌላ በኩል በተለይም አርቲፊሻል ኢንተሊጀንት (AI)ን ጨምሮ በቴክኖሎጂ ቅንብር የሚፈጠሩ መረጃዎችን ከመከላከል አኳያ አስፈላጊ መሆኑ ይታመናል።

አዋጁ ከዚህም በተጨማሪ በአንቀጽ 2(5) መሰረት ጥንቃቄ የሚፈልግ የግል ዳታ ምን ምን እንደሚያካትት ዘርዝሮ አስቀምጧል፣ በዚህም፣ የአንድ የተፈጥሮ ሰው ዘርን ወይም ብሔርን፣ የዘረ-መል ወይም የማንነት አካላዊ ዳታን፣ የአካላዊ ወይም የአዕምሯዊ ጤንነት ወይም ሁኔታን፣ የፖለቲካ አመለካከትን፣ የሙያ ማኅበር አባልነትን፣ ሃይማኖትን ወይም ሌላ ሃይማኖት ነክ አስተሳሰብን፣ የተፈጸመ ወይም ተፈጸመ የተባለ ወንጀልን፤ የተፈጸመ ወይም ተፈጸመ የተባለ ወንጀልን አስመልክቶ የተካሄዱ ሂደቶችን፣ እነዚህ ሂደቶች የተጠናቀቁበት መደምደሚያን ወይም በሂደቶቹ ዙሪያ ፍርድ ቤቶች የሰጡት የቅጣት ውሳኔን፣ ይዘትንና ሜታ ዳታን ወይም ገላጭ ዳታን ጨምሮ ያሉ የመልዕክት ልውውጥ ዳታ ፣ወይም ባለሥልጣኑ ከጊዜ ወደ ጊዜ ጥንቃቄ የሚፈልግ የግል ዳታ ነው በማለት የሚወስነው ሌላ የግል ዳታን የተመለከተ መረጃ ነው በማለት ያስቀምጣል። ይህ ጥንቃቄ የሚጠይቅ የዳታ ክፍል በአዋጁ አንቀጽ 10(1) መሰረት ሚኒስቴሩ በሚያወጣው ደንብ ሌሎችንም ሊያካትት ይችላል።

የአዋጁ ተፈፃሚነት ወሰን
አዋጁ በአንቀጽ 3 ስር በግልፅ እንዳስቀመጠው “በሙሉ ወይም በከፊል ራስ አዘዝ በሆነ መሳሪያ፣ እንደዚሁም የመዝገብ ሥርዓት አካል የሆነ ወይም የመዝገብ ሥርዓት አካል እንዲሆን የታሰበና ራስ አዘዝ ባልሆነ መሳሪያ በሌላ መንገድ በሚደረግ የግል ዳታ ማቀናበር ላይ፣ ተፈፃሚ ይሆናል። ከቦታ አንፃር ስንመለከተው የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮችን ጨምሮ በፌደራልና ክልል መንግስታት ውስጥ የግል ዳታ የማቀናበር ኃላፊነትና ተግባር ባላቸው የግል እና የመንግስት ተቋሞች ላይ ተፈጻሚነት ይኖረዋል። ይህም ማለት የትኛውም በዚህ አዋጅ መሰረት ፈቃድ ወስዶ የዳታ ማቀናበር ስራ የሚሰራ ድርጅትም ይሁን ከዚሁ ጋር በተያያዘ ስልጣን ያለው የመንግስት መስሪያ ቤት በህጉ የተካተቱ ዝርዝር ክልከላዎችን የማክብር ግዴታ ይኖርበታል ማለት ነው።

በሌላ በኩል አንድ ግለሰብ ለግሉ ወይም ለቤተሰቡ ግልጋሎት ለመስጠት በሚደረጉ፤ በመንግስት ተቋማት መካከል አንድን ጉዳይ ለማጣራት በሚደረጉ የመረጃ ልውውጦች ላይ የሚያተኩሩ፤ በዚህ አዋጅ ድንጋጌዎች ተፈጻሚነት ላይ የተጣሉ ገደቦች ተብለው በተለዩ፣ እና ከውጭ አገራት በመነጩ እንዲሁም በኢትዮጵያ አልፈው ወደ ሶስተኛ አገራት የሚሻገሩ የግል ዳታ ማቀናበሮች ላይ ይህ አዋጅ ተፈፃሚ አይሆንም። አንቀጽ 3(2)

የግል ዳታ ጥበቃና የጥበቃ ጊዜ ርዝማኔ
አዋጁ ዝርዝር የግል ዳታ ጥበቃ ሂደቶችን ማለትም፣ ህጋዊና ህገ-ወጥ ዳታ ማቀናበርን፣ ከማስተላለፍ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች እና መሰል ይዘቶችን አካቷል። ከዚህ አንፃር የሚከተሉትን ዋናዋና መብቶች ማንሳት ይቻላል፣
ሀ) መረጃ የማግኘት መብት፣ ማንኛውም የዳታ ተቆጣጣሪ ወይም አቀናባሪ የዳታ ባለቤቱን ማሳወቅና በግልጽ ካልተከለከለ በቀር ሙሉ ፈቃድ ማግኘት አለበት፣ አንቀጽ 24፣ 2(14)
ለ) የመረጃ ተደራሽነት መብት፣ ተቃራኒ ክልከላ ከሌለ በስተቀር የዳታው ባለቤት በራሱ ስም የተያዙ ዳታዎችን አስመልክቶ መረጃ እንዲሰጠው ሲጠይቅ ይህንኑ የማግኘት መብት አለው።
ሐ) ዳታን የመደምሰስ መብት፣ የዳታው ባለቤት ዳታው ከአላማው አንፃር አስፈላጊ ካልሆነ፣ ዳታ እንዲቀናበር የሰጠው ፈቃድ ከተነሳ፣ ዳታ የተቀናበረበትን መሠረት ከተቃወመ እና ለማቀናበር ከፍ ያሉ ሕጋዊ ምክንያቶች የሌሉ ከሆነ፤ ወይም የግል ዳታ የተቀናበረው ሕጋዊ መሠረት ሳይኖረው ከሆነ የግል ዳታው ያለ ምንም ክፍያና ያላግባብ መዘግየት እንዲደመሰስ የማድረግ መብት አለው።
መ) የመቃወም መብት፣ የዳታ ተቆጣጣሪው ከዳታ ባለቤቱ ፍላጎቶች፣ መብቶች እና ነፃነቶች ከፍ ያሉ ወይም ሕጋዊ መብቱን ለማቋቋም፣ ለመተግበር ወይም ለመከላከል የሚያስችሉ ሕጋዊ ምክንያቶችን በጽሑፍ ዘርዝሮ ካላቀረበ በስተቀር፤ የዳታ ባለቤቱ የግል ዳታው እንዳይቀናበር በማንኛውም ጊዜ በጽሑፍ የመቃወም መብት አለው። (አንቀጽ 29)
ሰ) የማስተካከል መብት፣ የዳታ ባለቤት የግል ዳታው ትክክለኛ ያልሆነ ፣ ያልተሟላ ፣ አሳሳች፣ ወቅታዊ ያልሆነ፣ ወይም የሚቀናበረው ከዚህ አዋጅ በተቃራኒ ነው ብሎ በሚያምንበት ጊዜ፣ የዳታው ባለቤት ዳታው ያለምንም ክፍያና ያላግባብ መዘግየት የዳታ ተቆጣጣሪው እንዲያስተካክል የማድረግ መብት አለው። (አንቀጽ 27)
ረ) ማቀናበርን የመገደብ መብት፣ የዳታ ባለቤቱ በዳታው ትክክለኛነት ላይ ተቃውሞ ያቀረበና የዳታ ተቆጣጣሪው የዳታውን ትክክለኛነት ለማረጋገጥ እንዲችል ጊዜ የተሰጠው፣ የዳታ ተቆጣጣሪው ለማቀናበር የማይፈልገው፣ ነገር ግን የዳታው ባለቤት ሕጋዊ መብቱን ለማረጋገጥ፣ ለመተግበር ወይም ለመከላከል የሚፈልገው የግል ዳታ፣ የዳታ ማቀናበሩ ሕጋዊ መሠረት የሌለው፣ እና የዳታው ባለቤት የግል ዳታው እንዳይደመሰስ ተቃውሞ ያቀረበና በምትኩ ማቀናበሩ እንዲገደብ የሚል ጥያቄ ያቀረበ፣ ወይም ማቀናበሩ እንዲቆም ተቃውሞ አቅርቦ ከሆነና ዳታ ተቆጣጣሪው ያለው ሕጋዊ ምክንያቶች የዳታ ባለቤቱ ካለው መብት ከፍ ያሉ መሆኑን በማጣራት ሂደት ላይ ያለ ከሆነ የግል ዳታ ማቀናበር እንዲገደብ የመጠየቅ መብት አለው። (አንቀጽ 30)
ከዚህ በተጨማሪ በአዋጁ አንቀጽ 23 ስር የጥበቃ ጊዜን በተመለከተ የሚከተሉትን ተጨማሪ ጉዳዮች እናገኛለን፣
• የዳታ ባለቤት የግላዊነት መብት ከግለሰቡ የሕይወት ዘመን በኋላ ቀጣይነት ያለው መብት ነው፣ (Right of post-mortem protection) የምንለው ማለት ነው።
• የግላዊነት መብት የዳታ ባለቤቱ ከሞተ በኋላ ባሉ አስር ዓመታት ጭምር የጸኑ ናቸው።
• የዳታ ባለቤቱ ሕጋዊ ወራሽ የዳታ ባለቤቱ ከሞተ በኋላ ባሉ አሥር ዓመታት ውስጥ በማንኛውም ጊዜ መብቶቹን ማስከበር ይችላል።

ህጋዊ የዳታ ማስተላለፍ
የግል ዳታ በዋነኝነት በሶስት ዋና ዋና መንገዶች ሊተላለፍ ይችላል፣ የመጀመሪያው የዳታው ባለቤት ዳታው እንዲተላለፍ በጽሁፍ፣ በቃል ወይም በሌላ አውንታዊ ዘዴ ፈቃደኝነቱን ሲገልጽ ነው፣ አንቀጽ 2(14) ፣ አዋጁ በግልጽ የግል ዳታ እንዲቀናበር ወደ ሦስተኛ ወገን የሥልጣን ክልል የሚተላለፈው በዚህ አዋጅ ድንጋጌዎች መሠረት እና ዳታው የሚተላለፍለት የሥልጣን ክልል ተገቢ የሆነ ጥበቃ የሚያደርግ መሆኑን በማረጋገጥ ነው የሚል መርህን አስቀምጧል። በአዋጁ መሰረት የምዝገባ ፈቃድ ለሌላቸው የዳታ አቀናባሪ ድርጅቶች ማስተላለፍ አይቻልም።

በተለይም ወደሌላ ሶስተኛ የስልጣን ክልል (Jurisdiction) በሚተላለፍበት ጊዜ ተመሳሳይ ጥበቃ መኖሩን ማረጋገጥ ያስፈልጋል። ሁለተኛው የዳታ መተላለፊያ መንገድ በዳታ ባለቤቱ የህይወት እልፈት ወቅት በህግ የወራሽነት ስልጣን ለተሰጣቸው አካላት የሚተላለፍ ይሆናል። ይህም ዳታ በህግ አግባብ የሚተላለፍበት (Transfer by law) ሁኔታ እንዳለ የሚያሳይ ነው።

በሌላ በኩል በአንዳንድ ልዩ ሁኔታዎች የዳታው ባለቤት ፈቃድ ሳያስፈልግ ዳታው ወደ ሶስተኛ ወገን ሊተላለፍ የሚችልበት ሁኔታም አለ። ለምሳሌ በአንቀጽ 19(2) እንደተመላከተው ባለሥልጣኑ ተገቢ የዳታ ጥበቃ ደረጃ በሌለበት ሁኔታ የተወሰነ ዳታ ማስተላለፍ ተገቢ ነው ብሎ ሲያምን የዳታ ባለቤቱን መብት በሚገድብ መልኩ ዳታ ማስተላለፉን ሊፈቅድ ይችላል፣ በተያያዘም ጥንቃቄ የሚፈልግ የግል ዳታ ከአገር ውጭ ለማስወጣት ሲያስፈልግ በቅድሚያ የባለሥልጣኑን ፈቃድ ማግኘት እንዳለበት በአንቀጽ 22(3) ተመላክቷል። (ጥንቃቄ የሚፈልግ የግል ዳታን በሚመለከት በአንቀፅ 2(5) ላይ ዝርዝር ትርጓሜ ተሰጥቶታል)። በተጨማሪም የግል ዳታ ለታሪካዊ፣ ለስታስቲክስ ወይም ለሳይንሳዊ ምርምሮች ዓላማ ለማሳካት የባለቤቱ ፈቃድ ላይ ገደብ ሊጣልበት ይችላል።

አዋጁን የማስፈጸም ስልጣን ስለተሰጣቸው አካላት፣
ይህንን አዋጅ የማስፈጸም ስልጣን በዋነኝነት ለኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ባለስልጣን ተሰጥቷል። ይህ ባለስልጣን መስሪያ ቤት በኢ.ፌ.ዲ.ሪ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ስር ያለና ቀደም ብሎ በአዋጅ ቁጥር 1148/2011 መሠረት የተቋቋመው ባለሥልጣን መስሪያ ቤት ነው። ባለሥልጣኑ በዋነኝነት የሚከተሉት ሥልጣንና ተግባራት ተሰጥተውታል፤
 የዚህን አዋጅ ተፈጻሚነት ያረጋግጣል፤
 ኃላፊነቱን ለመወጣት የሚያስችል አስፈላጊውን አስተዳደራዊ መዋቅር ይፈጥራል፣ የግል ዳታ ማቀናበር፣
 ማስተላለፍ ስራዎች በህጉ መሰረት መከናዎናቸውን ያረጋግጣል፣ በተለይም ጥንቃቄ የሚሹ የግል ዳታዎች በተገቢወው መንገድ ጥቅም ላይ መዋላቸውን ይከታተላል፣ እንዲሁም
 ይህንን አዋጅ በሚጥሱ አካላት ላይ ተገቢ አስተዳደራዊ እርምጃዎችን ይወስዳል። በተጨማሪም በሀጉ አንቀጽ 5 ተለይተው የተሰጡትን ሌሎች ዝርዝር ኋላፊነቶችን ይፈጽማል።

የአዋጁ ጥሰትና የሚያስከትለው የህግ ተጠያቂነት

አስተዳደራዊ እርምጃዎች
ባለሥልጣኑ የዚህን አዋጅ ድንጋጌዎች እና በዚህ አዋጅ መሠረት የወጡ ደንቦችና መመሪያዎችን በመጣስ የግል ዳታ የሚያቀናብሩ ሰዎች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ የመውሰድ ሥልጣን አለው፡፡ በተለይም ጥሰቱ የተፈጸመው
(ሀ) በተቋም ከሆነ፤
(ለ) ጥንቃቄ በሚፈልግ የግል ዳታ ዙሪያ የተፈጸመ ከሆነ፤ ወይም
(ሐ) ለአካለ መጠን ያልደረሰ ልጅ የግል ዳታን የሚመለከት ከሆነ በጉዳዩ ላይ አቤቱታ ከተመሰረተበት ዓመት በፊት ባለው የሥራ ዘመን ተቋሙ ከሚያካሂደው የንግድ ሥራው ካገኘው ጠቅላላ ሽያጭ እስከ አራት ፐርሰንት(4%) ያህል መቀጮ ይቀጣል፡፡ በድርጊቱ የተገኘ ፍሬ ለመንግሥት ገቢ ይሆናል።
ይሁን እንጂ አዋጁ አስተዳደራዊ እርምጃ የሚያስወስዱ ዝርዝር ድርጊቶች የትኞቹ እንደሆኑ በደንብ ይወጣል በማለት ቢያስቀምጥም ይህ ጽሁፍ እስከተዘጋጀበት ጊዜ ድረስ የተባለው ደንብ አልወጣም። በአዋጁ በግልጽ የተቀመጠ የአቤቱታ ማቅረቢያ የጊዜ ገደብም እንዲሁ አልተካተተም።

የወንጀል ተጠያቂነት
ማንኛውም ሰው ከዚህ በታች ወንጀል ተብለው የተዘረዘሩትን ድርጊቶች ፈጽሞ የተገኘ እንደሆነ የተቀመጡት የእስርና የገንዘብ መቀጮዎች ይፈጸሙበታል፣
ሀ) የግል ዳታ ጥሰትን ካላሳወቀ፣
ለ) የግል ዳታ ጥሰት ተፈጽሞ ሲገኝ ተገቢውን የቴክኒክና ተቋማዊ እርምጃዎች ካልወሰደ የግል ዳታ በአዋጁ ከተደነገጉት የማቀናበር መርሆዎች ውጪ ካቀናበረ፤ ከአንድ ዓመት እስከ ሦስት ዓመት በሚደርስ ቀላል እስራ ወይም ከብር ከ50000 (ሃምሳ ሽ) እስከ 100000 (መቶ ሽ) በሚደርስ መቀጮ ወይም በሁለቱም ይቀጣል።
፪/ ማንኛውም ሰው በዚህ አዋጅ የተደነገጉና የግል ዳታ ባለቤት የግል ዳታው
ሀ) እንዲደመሰስ የማድረግ፣
ለ) እንዳይቀናበር የመቃወም፣
ሐ) ማቀናበር እንዲገደብ የመጠየቅ፣
መ) ራስ አዘዝ በሆኑ መሳሪያዎች በሚሰጡ ውሳኔዎች ላይ ያለውን መብቱን ካላከበረ ከሶስት እስከ አምስት ዓመት በሚደርስ እስራት እና ከብር 100000 (መቶ ሽ) እስከ 200000 (ሁለት መቶ ሺ) በሚደርስ መቀጮ ወይም በሁለቱም ይቀጣል።
፫/ ማንኛውም ሰው
ሀ) የግል ዳታ ባለቤቱ ተለይቶ እንዳይታወቅ የተደረገን የግል ዳታ ተለይቶ እንዲታወቅ ካደረገ፤
ለ) ተለይቶ የታወቀውን የግል ዳታ ካቀናበረ፤
ሐ) የግል ዳታን ከሸጠ ወይም ለሽያጭ ካቀረበ፤ ወይም ለሽያጭ ካቀረበ፤ ወይም
መ) የግል ዳታን በአዋጁ ከተደነገገው ውጪ ከአገር ውጪ ካስተላለፈ አምስት ዓመት አስር ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እና ከብር 200000 (ሁለት መቶ ሽ) እስከ 600000 (ስድስት መቶ ሽ) በሚደርስ መቀጮ የሚቀጣ ይሆናል።
ከዚህ ባለፈ እነዚህ ድርጊቶች ከፍ ያለ ኢኮኖሚያዊ ወይም የሞራል ጉዳት አስከትለው እንደሆነ ድርጊት ፈፃሚው ተገቢ ካሳ የመክፈል ፍትሀብሄራዊ ሃላፊነት ይወድቅበታል።

ማጠቃለያ
በዚህ አጭር ጽሁፍ ዋና ዋና የግል ዳታ ጥበቃ መርሆዎች፣ እውቅና የተሰጣቸው መብቶቸን፣ ዝርዝር የማስፈጸም ስልጣን የተሰጣቸውን ተቋማትን ከአዲሱ የግል ዳታ ጥበቃ አንጻር ለመዳሰስ ጥረት ተደርጓል። ይሁንና የግል ዳታ ጥበቃ ጉዳይ በአንድ አዋጅ ተጠቃሎ የማያልቅ አይሆንም። በዚህም ምክንያት ውጤታማ ጥበቃ ይኖር ዘንድ በርካታ ዘርፎችን የሚገዙ ህግጋትን መሰረት ያደረገ ጠንካራ ተቋም መገንባት ይጠይቃል። ለምሳሌ በዚህ ጽሁፍ ከተዳሰሰው አዋጅ በተጨማሪ የፍትሃብሄር ህጉ፣ የኤሌክትሮኒክ ትራንዛክሽን አዋጁ፣ የወንጀል ህጉ፣ የኤሌክትሮኒክ ፊርማ አዋጅ፣ የሰነድ ምዝገባና ማረጋገጥ አዋጅ፣ የካፒታል ማርኬት አዋጅና የመሳሰሉት ህጎች ሁሉ የግል ዳታን በሚመለከት ልዩ ልዩ ይዘቶችን አካተዋል። በዚህም ምክንያት የግል ዳታ ጥበቃ በአገራችን በጅማሮ ላይ ያለና አሁንም ድረስ በተቋም ደረጃ ብዙ የሚቀሩት ዘርፍ ቢሆንም ያለንበት ወቅት ዘርፉን በልዩ ትኩረት ማየት የሚጠይቅ ነው።

በንቃተ ህግ፣ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ
ፍትህ ሚኒስቴር

ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com

07/04/2025

ሁሉም ነገር በአውሎ ነፋስ ፍጥነት በሚጓዝበት ዓለም ውስጥ መረጃ ጉልበት ነው:: መረጃ ኃይል ነው:: መረጃ አቅም ነው:: ግን ግን መረጃ ኃይል እና ጉልበት እንዲሁም Game-Changer ፍኖት የሚሆነው በትክክለኛው ሰዓት እና ቦታ አንተ ወይም አንቺ ጋር ከደረሰ ብቻ ነው::
Melat Nigussie

የመረጃ ነፃነት፣ መረጃ የማግኘት መብት እና መረጃን ተደራሽ የማድረግ ግዴታመግቢያሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ዓለም አቀፋዊ መብት ሲሆን ኢትዮጵያ ተቀብላ ባጸደቀችው የሰብዓዊ መብቶች ሁሉ...
31/01/2025

የመረጃ ነፃነት፣ መረጃ የማግኘት መብት እና መረጃን ተደራሽ የማድረግ ግዴታ

መግቢያ
ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ዓለም አቀፋዊ መብት ሲሆን ኢትዮጵያ ተቀብላ ባጸደቀችው የሰብዓዊ መብቶች ሁሉ አቀፍ መግለጫ (UDHR፣1948) አንቀፅ 19 ላይ እንደተቀመጠው ማንኛውም ሰው ሀሳቡን በነፃነት የመግለጽና የመሰለውን አስተያየት የመስጠት መብት አለው። ይህ መብት ያለምንም ተፅዕኖ እና ጣልቃ ገብነት በማናቸውም ዓይነት መገናኛ መረጃዎችና ሀሳቦችን የመፈለግ፣ የመቀበልና የማስተላለፍ ነፃነትን እንደሚጨምር በድንጋጌው ላይ ሰፍሮ ይገኛል። በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ መንግስት አንቀፅ 29 (4) ላይ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎች ሀሳቦችና አመለካከቶች በነፃ መንሸራሸራቸውን ለማረጋገጥ ሲባል የመገናኛ ብዙኃን በተቋምነታቸው የአሰራር ነፃነትና የተለያዩ አስተያየቶች የማስተናገድ ችሎታ እንዲኖራቸው የሕግ ጥበቃ ይደረግላቸዋል።

የመገናኛ ብዙኃን መሰረታዊ ተግባር መረጃን ከአንድ ወገን ወደ ሌላው ማሰራጨት እንደመሆኑ መጠን ይህን መረጃ የማሰራጨት ተግባራቸውን በአግባቡ መወጣት እንዲችሉ መረጃዎቹን በነፃነት ማግኘት መብት አላቸው። በዚህ አጭር የንቃተ ሕግ ጽሁፍ ስለ መረጃ ነፃነት፣ መረጃ የማግኘት መብትና መረጃን ለሚዲያዎች ተደራሽ ከማድረግ አኳያ ስለሚኖር ግዴታና ግዴታውን አለመወጣት የሚያስከትለውን ተጠያቂነት ለመዳሰስ እንሞክራለን፡፡

የመረጃ ነፃነት ምንነት
የመረጃ ነፃነት የሚለውን ሐረግ ምንነት ከማየታችን በፊት መረጃ የተባለው ወሳኝ ቃል ምንድን ነው የሚለውን ማየቱ ጠቃሚ ይሆናል። የመገናኛ ብዙኃንና የመረጃ ነፃነት አዋጅ ቁጥር 590/2000 አንቀፅ 2(6) ላይ “መረጃ ማለት በማንኛውም ዓይነት ቅርፅ የተቀናበረ ማንኛውም ዓይነት ሰነድ ነው” ሲል ትርጉም ሰጥቶታል። በዚህም መሰረት መረጃ ማንኛውም ቅጂ፣ ምልልስ፣ ጥሬ ሀቅ፣ የግል አስተያየት፣ ምክር፣ የውስጥ ማስታወሻ፣ ዳታ፣ ስታቲስቲክስ፣ መፅሐፍ፣ ሥዕል፣ ዕቅድ፣ ካርታ፣ ዲያግራም፣ ፎቶግራፍ፣ የድምፅ ወይም የምስል ቅጅ፣ ወይም ማንኛውም ሊጨበጥ የሚችልና የማይጨበጥ ቁስ ሊያጠቃልል ይችላል (አማኑኤል አብርሀም “የመረጃ ነፃነት በኢትዮጵያ” ከተሰኘው መፅሐፍ)።

የመረጃ ነፃነት ሲባል ደግሞ የሰዎች የመናገር ወይም ሀሳብን የመግለፅ፣ መረጃ የመፈለግ፣ የማግኘትና የማስተላለፍ መብትን ያካተተ ሰፊ ፅንሰ ሀሳብ ነው። የመረጃ ነፃነት መኖር ዜጎች የሀገራቸውን ጉዳይ እንዲረዱና በተገቢው ሁኔታ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ከማስቻሉም በላይ፤ መብትና ግዴታቸውን ተረድተው ስለመብታቸው እንዲጠይቁና ሀገራዊ ግዴታቸውን እንዲወጡ ያስችላቸዋል።

መረጃ የማግኘት መብት
መረጃ የማግኘት መብትን በሕገ-መንግስት አንቀፅ 29(2) እንደተመለከተው ማንኛውም ሰው ያለማንም ጣልቃ ገብነት ሀሳቡን የመግለፅ ነፃነት ያለው ሲሆን ይህ ነፃነት በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ ወሰን ሳይደረግበት በቃልም ሆነ በፅሁፍ ወይም በህትመት፣ በሥነ ጥበብ መልክ ወይም በመረጠው ማንኛውም የማሰራጫ ዘዴ፣ ማንኛውንም አይነት መረጃና ሀሳብ የመሰብሰብ፣ የመቀበልና የማሰራጨት ነፃነትን የሚያካትት እንደሆነ በግልፅ ተቀምጦ እናገኘዋለን (አዋጅ ቁጥር 1238/13 አንቀፅ 48ን ይመለከታል)።

ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት በኢትዮጵያ ሕገ-መንግስት መሰረት ዴሞክራሲያዊ መብት በመሆኑ ይህ መብት ሊገደብ የሚችልበት ሁኔታ አለ። በሕገ-መንግስቱ አንቀፅ 29(6) እንደተመለከተው የወጣቶችን ደህንነት፣ የሰውን ክብርና መልካም ስም ለመጠበቅ ሲባል ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ላይ ሕግን መሰረት ያደረገ ገደብ ሊደረግ ይችላል። ሌላው ጦርነትን የሚቀሰቅሱ እንዲሁም ሰብዓዊ ክብርን የሚነኩ የአደባባይ መግለጫዎች ከላይ በተጠቀሰው አንቀፅ መሰረት በሕግ የተከለከሉ እንደሆነ ተመላክቷል። ዜጎች ወይም ማንኛውም ህጋዊ የሚዲያ አካል መረጃን በተቻለ መጠን በፍጥነትና በዝቅተኛ ወጭ የማግኘት መብት አላቸው።
የመረጃ ጥያቄ በፍጥነትና ፍትሐዊ በሆነ መንገድ መስተናገድ አለበት። ይህን ሊፈታ የሚችል የመረጃ ጥያቄ አቀረራብና ቅሬታ አሰማም ሥርዓት ያስፈልገዋል። መረጃን የማግኘት መብት በመረጃ ፈላጊው አካል ሲጠይቅ እና ሳይጠየቅ የሚፈፀም መብት ሲሆን መረጃ ሳይጠየቅ መረጃ የማግኘት መብት የሚተገበረው መረጃው በመንግስት አካል ሲገለፅ ነው። የመንግስት አሰራር ለሕዝብ ግልፅ በሆነ መንገድ እና በተጠያቂነት መርህ መከናወን እንዳለበት በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ-መንግስት አንቀፅ 12 ላይ ተደንግጎ ይገኛል። የመንግስት አካላት በግልፅነትና በተጠያቂነት መንፈስ ስራቸውን ማከናወን ያለባቸው በመሆኑ ለህዝብ መገለፅ ያለባቸውን ጉዳዮች በተለያዩ መረጃ ማሰራጫ መንገዶች የማሳወቅ ግዴታ አለባቸው።

በጠቅላላው መረጃን የማግኘት መብትን በአዋጅ ቁጥር 590/2000 አንቀፅ 12 ላይ እንደሚከተለው ተደንግጓል፡-
 ማንኛውም ሰው ከማንኛውም መንግስታዊ አካል መረጃን የመጠየቅ፣ የማግኘትና የማስተላለፍ መብት አለው፤
 በመንግስት ተቋም የሚገኝን መረጃ የመመልከት፣ ማስታወሻ የመያዝና ግልባጭ የመውሰድ መብት አለው።

መረጃን ለሚድያ ተደራሽ የማድረግ ግዴታ
መገናኛ ብዙሃን የሚያሰራጩት መረጃ የመንግስትን የአሰራር ግልፅነት፤ ተጠያቂነትና ውጤታማነት በመመዘን የመንግስት አሰራርንና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ከመቅረፍ አኳያ ከፍተኛ ሚና አላቸው። በመሆኑም የመንግስት አካላት መረጃን ለመገናኛ ብዙኃን ተደራሽ የማድረግ ግዴታ አለባቸው። በመረጃ ነፃነት ሕጉ መረጃ የማግኘት መብትና መረጃን የመስጠት ግዴታን አስመልክቶ የሚከተሉትን ዓላማዎች ለማሳካት ሊተገበሩ እንደሚገባቸው በአንቀፅ 10 ስር ደንግጓል። እነዚህም፡- ሕግን መሰረት ያደረጉ ገደቦች እንደተጠበቁ ሆነው ማንኛውም መንግስታዊ አካል ዜጎች መረጃን ለመጠየቅ፣ ለማግኘትና ለማስተላለፍ ያላቸውን መብት ተፈፃሚ የማድረግ፤ መረጃ ፈላጊዎች መረጃዎችን በተቻለ ፍጥነትና በዝቅተኛ ወጪ ሳይደክሙ የሚያገኙበትን አሰራርና ስነ-ስርዓት በመመስረት መብቱን ተፈፃሚ የማድረግ እና የሕዝብ ተሳትፎን የስልጣን ባለቤትነትን የማረጋገጥና እንዲሁም የአሰራር ግልፅነት፣ ተጠያቂነትና ውጤታማነት የሰፈነበት የመንግስት አሰራርንና መልካም አስተዳደርን የማጠናከር ዓላማን መሰረት አድርጎ የሚተገበር ይሆናል።

መረጃን ለሚድያ ተደራሽ አለማድረግ የሚያስከትለው ተጠያቂነት
መረጃን ተደራሽ የማድረግ ጉዳይ በግዴታነት መቀመጡ ብቻ በቂ አይሆንም። ግዴታው በአግባቡ ተግባር ላይ እንዲውልና እንዲፈፀም አስገዳጅ ሕግ ሊቀመጥለት ይገባል። ሰዎች በሕግ የተጣለባቸውን ግዴታ እንዲወጡ ከሚያስችሉት መንገዶች ዋነኛው ሕጉን በሚጥሱት ላይ ተመጣጣኝ ቅጣት መጣል ነው። በያዝነው ርዕሰ ጉዳይ ላይም የመረጃ ነፃነት አዋጁ መረጃን ተደራሽ የማድረግ ግዴታቸውን በማይወጡት ላይ የሚከተለውን ቅጣት አስቀምጧል። በዚህም መሰረት ማንም ሰው መረጃ የማግኘት መብትን ለመጣስ በማሰብ ማንኛውንም ሰነድ ያጠፋ፣ ያበላሸ፣ የቀየረ፣ የሰረዘ፣ የደበቀ፣ በተንኮል የከለከለ፣ ያፋለሰ ወይም ሀሰተኛ ሰነድ የሰራ በገንዘብ መቀጮ ወይም ከሁለት ዓመት በማይበልጥ እስራት እንደሚቀጣ ተደንግጓል (አንቀፅ 39(5))።

ማጠቃለያ
በጠቅላላው ማንኛውም ሰው በተለይም የመገናኛ ብዙኃን ከማንኛውም አካል በዋናነት ከመንግስት አካላት መረጃን የማግኘት እና የማሰራጨት ሕገ-መንግስታዊ መብታቸው መሆኑንና የመንግስት አካላትም መረጃዎችን ለሕዝብ በተለይም ለመገናኛ ብዙኃን በፍጥነት፣ በዝቅተኛ ወጪ ተደራሽ የማድረግ ግዴታ ያለባቸው መሆኑ በመረጃ ነፃነት አዋጁ ሰፍሯል። አዋጁ በዚህ ብቻ ሳይወሰን ሕጉን በሚተላለፉት ላይ ተመጣጣኝ ቅጣት የጣለ ስለሆነ የመንግስት አካላት ይህንን ተገንዝበው በሕግ እገዳ ከተጣለባቸው መረጃዎች ውጪ ያሉትን በሙሉ ለመገናኛ ብዙኃንና ለሕዝብ በተገቢው መንገድ ተደራሽ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።
በንቃተ ህግ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ

ፍትህ ሚኒስቴር

የመረጃ ነፃነት፣ መረጃ የማግኘት መብት እና መረጃን ተደራሽ የማድረግ ግዴታ

መግቢያ
ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ዓለም አቀፋዊ መብት ሲሆን ኢትዮጵያ ተቀብላ ባጸደቀችው የሰብዓዊ መብቶች ሁሉ አቀፍ መግለጫ (UDHR፣1948) አንቀፅ 19 ላይ እንደተቀመጠው ማንኛውም ሰው ሀሳቡን በነፃነት የመግለጽና የመሰለውን አስተያየት የመስጠት መብት አለው። ይህ መብት ያለምንም ተፅዕኖ እና ጣልቃ ገብነት በማናቸውም ዓይነት መገናኛ መረጃዎችና ሀሳቦችን የመፈለግ፣ የመቀበልና የማስተላለፍ ነፃነትን እንደሚጨምር በድንጋጌው ላይ ሰፍሮ ይገኛል። በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ መንግስት አንቀፅ 29 (4) ላይ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎች ሀሳቦችና አመለካከቶች በነፃ መንሸራሸራቸውን ለማረጋገጥ ሲባል የመገናኛ ብዙኃን በተቋምነታቸው የአሰራር ነፃነትና የተለያዩ አስተያየቶች የማስተናገድ ችሎታ እንዲኖራቸው የሕግ ጥበቃ ይደረግላቸዋል።

የመገናኛ ብዙኃን መሰረታዊ ተግባር መረጃን ከአንድ ወገን ወደ ሌላው ማሰራጨት እንደመሆኑ መጠን ይህን መረጃ የማሰራጨት ተግባራቸውን በአግባቡ መወጣት እንዲችሉ መረጃዎቹን በነፃነት ማግኘት መብት አላቸው። በዚህ አጭር የንቃተ ሕግ ጽሁፍ ስለ መረጃ ነፃነት፣ መረጃ የማግኘት መብትና መረጃን ለሚዲያዎች ተደራሽ ከማድረግ አኳያ ስለሚኖር ግዴታና ግዴታውን አለመወጣት የሚያስከትለውን ተጠያቂነት ለመዳሰስ እንሞክራለን፡፡

የመረጃ ነፃነት ምንነት
የመረጃ ነፃነት የሚለውን ሐረግ ምንነት ከማየታችን በፊት መረጃ የተባለው ወሳኝ ቃል ምንድን ነው የሚለውን ማየቱ ጠቃሚ ይሆናል። የመገናኛ ብዙኃንና የመረጃ ነፃነት አዋጅ ቁጥር 590/2000 አንቀፅ 2(6) ላይ “መረጃ ማለት በማንኛውም ዓይነት ቅርፅ የተቀናበረ ማንኛውም ዓይነት ሰነድ ነው” ሲል ትርጉም ሰጥቶታል። በዚህም መሰረት መረጃ ማንኛውም ቅጂ፣ ምልልስ፣ ጥሬ ሀቅ፣ የግል አስተያየት፣ ምክር፣ የውስጥ ማስታወሻ፣ ዳታ፣ ስታቲስቲክስ፣ መፅሐፍ፣ ሥዕል፣ ዕቅድ፣ ካርታ፣ ዲያግራም፣ ፎቶግራፍ፣ የድምፅ ወይም የምስል ቅጅ፣ ወይም ማንኛውም ሊጨበጥ የሚችልና የማይጨበጥ ቁስ ሊያጠቃልል ይችላል (አማኑኤል አብርሀም “የመረጃ ነፃነት በኢትዮጵያ” ከተሰኘው መፅሐፍ)።

የመረጃ ነፃነት ሲባል ደግሞ የሰዎች የመናገር ወይም ሀሳብን የመግለፅ፣ መረጃ የመፈለግ፣ የማግኘትና የማስተላለፍ መብትን ያካተተ ሰፊ ፅንሰ ሀሳብ ነው። የመረጃ ነፃነት መኖር ዜጎች የሀገራቸውን ጉዳይ እንዲረዱና በተገቢው ሁኔታ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ከማስቻሉም በላይ፤ መብትና ግዴታቸውን ተረድተው ስለመብታቸው እንዲጠይቁና ሀገራዊ ግዴታቸውን እንዲወጡ ያስችላቸዋል።

መረጃ የማግኘት መብት
መረጃ የማግኘት መብትን በሕገ-መንግስት አንቀፅ 29(2) እንደተመለከተው ማንኛውም ሰው ያለማንም ጣልቃ ገብነት ሀሳቡን የመግለፅ ነፃነት ያለው ሲሆን ይህ ነፃነት በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ ወሰን ሳይደረግበት በቃልም ሆነ በፅሁፍ ወይም በህትመት፣ በሥነ ጥበብ መልክ ወይም በመረጠው ማንኛውም የማሰራጫ ዘዴ፣ ማንኛውንም አይነት መረጃና ሀሳብ የመሰብሰብ፣ የመቀበልና የማሰራጨት ነፃነትን የሚያካትት እንደሆነ በግልፅ ተቀምጦ እናገኘዋለን (አዋጅ ቁጥር 1238/13 አንቀፅ 48ን ይመለከታል)።

ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት በኢትዮጵያ ሕገ-መንግስት መሰረት ዴሞክራሲያዊ መብት በመሆኑ ይህ መብት ሊገደብ የሚችልበት ሁኔታ አለ። በሕገ-መንግስቱ አንቀፅ 29(6) እንደተመለከተው የወጣቶችን ደህንነት፣ የሰውን ክብርና መልካም ስም ለመጠበቅ ሲባል ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ላይ ሕግን መሰረት ያደረገ ገደብ ሊደረግ ይችላል። ሌላው ጦርነትን የሚቀሰቅሱ እንዲሁም ሰብዓዊ ክብርን የሚነኩ የአደባባይ መግለጫዎች ከላይ በተጠቀሰው አንቀፅ መሰረት በሕግ የተከለከሉ እንደሆነ ተመላክቷል። ዜጎች ወይም ማንኛውም ህጋዊ የሚዲያ አካል መረጃን በተቻለ መጠን በፍጥነትና በዝቅተኛ ወጭ የማግኘት መብት አላቸው።
የመረጃ ጥያቄ በፍጥነትና ፍትሐዊ በሆነ መንገድ መስተናገድ አለበት። ይህን ሊፈታ የሚችል የመረጃ ጥያቄ አቀረራብና ቅሬታ አሰማም ሥርዓት ያስፈልገዋል። መረጃን የማግኘት መብት በመረጃ ፈላጊው አካል ሲጠይቅ እና ሳይጠየቅ የሚፈፀም መብት ሲሆን መረጃ ሳይጠየቅ መረጃ የማግኘት መብት የሚተገበረው መረጃው በመንግስት አካል ሲገለፅ ነው። የመንግስት አሰራር ለሕዝብ ግልፅ በሆነ መንገድ እና በተጠያቂነት መርህ መከናወን እንዳለበት በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ-መንግስት አንቀፅ 12 ላይ ተደንግጎ ይገኛል። የመንግስት አካላት በግልፅነትና በተጠያቂነት መንፈስ ስራቸውን ማከናወን ያለባቸው በመሆኑ ለህዝብ መገለፅ ያለባቸውን ጉዳዮች በተለያዩ መረጃ ማሰራጫ መንገዶች የማሳወቅ ግዴታ አለባቸው።

በጠቅላላው መረጃን የማግኘት መብትን በአዋጅ ቁጥር 590/2000 አንቀፅ 12 ላይ እንደሚከተለው ተደንግጓል፡-
 ማንኛውም ሰው ከማንኛውም መንግስታዊ አካል መረጃን የመጠየቅ፣ የማግኘትና የማስተላለፍ መብት አለው፤
 በመንግስት ተቋም የሚገኝን መረጃ የመመልከት፣ ማስታወሻ የመያዝና ግልባጭ የመውሰድ መብት አለው።

መረጃን ለሚድያ ተደራሽ የማድረግ ግዴታ
መገናኛ ብዙሃን የሚያሰራጩት መረጃ የመንግስትን የአሰራር ግልፅነት፤ ተጠያቂነትና ውጤታማነት በመመዘን የመንግስት አሰራርንና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ከመቅረፍ አኳያ ከፍተኛ ሚና አላቸው። በመሆኑም የመንግስት አካላት መረጃን ለመገናኛ ብዙኃን ተደራሽ የማድረግ ግዴታ አለባቸው። በመረጃ ነፃነት ሕጉ መረጃ የማግኘት መብትና መረጃን የመስጠት ግዴታን አስመልክቶ የሚከተሉትን ዓላማዎች ለማሳካት ሊተገበሩ እንደሚገባቸው በአንቀፅ 10 ስር ደንግጓል። እነዚህም፡- ሕግን መሰረት ያደረጉ ገደቦች እንደተጠበቁ ሆነው ማንኛውም መንግስታዊ አካል ዜጎች መረጃን ለመጠየቅ፣ ለማግኘትና ለማስተላለፍ ያላቸውን መብት ተፈፃሚ የማድረግ፤ መረጃ ፈላጊዎች መረጃዎችን በተቻለ ፍጥነትና በዝቅተኛ ወጪ ሳይደክሙ የሚያገኙበትን አሰራርና ስነ-ስርዓት በመመስረት መብቱን ተፈፃሚ የማድረግ እና የሕዝብ ተሳትፎን የስልጣን ባለቤትነትን የማረጋገጥና እንዲሁም የአሰራር ግልፅነት፣ ተጠያቂነትና ውጤታማነት የሰፈነበት የመንግስት አሰራርንና መልካም አስተዳደርን የማጠናከር ዓላማን መሰረት አድርጎ የሚተገበር ይሆናል።

መረጃን ለሚድያ ተደራሽ አለማድረግ የሚያስከትለው ተጠያቂነት
መረጃን ተደራሽ የማድረግ ጉዳይ በግዴታነት መቀመጡ ብቻ በቂ አይሆንም። ግዴታው በአግባቡ ተግባር ላይ እንዲውልና እንዲፈፀም አስገዳጅ ሕግ ሊቀመጥለት ይገባል። ሰዎች በሕግ የተጣለባቸውን ግዴታ እንዲወጡ ከሚያስችሉት መንገዶች ዋነኛው ሕጉን በሚጥሱት ላይ ተመጣጣኝ ቅጣት መጣል ነው። በያዝነው ርዕሰ ጉዳይ ላይም የመረጃ ነፃነት አዋጁ መረጃን ተደራሽ የማድረግ ግዴታቸውን በማይወጡት ላይ የሚከተለውን ቅጣት አስቀምጧል። በዚህም መሰረት ማንም ሰው መረጃ የማግኘት መብትን ለመጣስ በማሰብ ማንኛውንም ሰነድ ያጠፋ፣ ያበላሸ፣ የቀየረ፣ የሰረዘ፣ የደበቀ፣ በተንኮል የከለከለ፣ ያፋለሰ ወይም ሀሰተኛ ሰነድ የሰራ በገንዘብ መቀጮ ወይም ከሁለት ዓመት በማይበልጥ እስራት እንደሚቀጣ ተደንግጓል (አንቀፅ 39(5))።

ማጠቃለያ
በጠቅላላው ማንኛውም ሰው በተለይም የመገናኛ ብዙኃን ከማንኛውም አካል በዋናነት ከመንግስት አካላት መረጃን የማግኘት እና የማሰራጨት ሕገ-መንግስታዊ መብታቸው መሆኑንና የመንግስት አካላትም መረጃዎችን ለሕዝብ በተለይም ለመገናኛ ብዙኃን በፍጥነት፣ በዝቅተኛ ወጪ ተደራሽ የማድረግ ግዴታ ያለባቸው መሆኑ በመረጃ ነፃነት አዋጁ ሰፍሯል። አዋጁ በዚህ ብቻ ሳይወሰን ሕጉን በሚተላለፉት ላይ ተመጣጣኝ ቅጣት የጣለ ስለሆነ የመንግስት አካላት ይህንን ተገንዝበው በሕግ እገዳ ከተጣለባቸው መረጃዎች ውጪ ያሉትን በሙሉ ለመገናኛ ብዙኃንና ለሕዝብ በተገቢው መንገድ ተደራሽ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።

በንቃተ ህግ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ

የፍትህ ሚኒስቴርን የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገፆችን ይቀላቀሉ
Facebook
https://www.facebook.com/MOJEthiopia/
(x) Twitter
https://x.com/MOJEthiopia
YouTube channel
https://youtube.com/...3701...
Telegram
https://t.me/fdreattorneyGeneral_external

15/12/2024

በብሮክራሲ (Bureaucracy) እስርቤት የሚገኙ የምንግስት ተቋማትን እንዴት ነፃ እናውጣቸው⁉️???

15/12/2024

access to information

Address

Dropped Pinhttps://maps. App. Goo. Gl/hDT7pUHMWMUkHgFB 7
Addis Ababa
1000

Website

https://t.me/PublicInformationNoble

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Public Information Noble PIN posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share