Basketo Intellectuals Association-BIA

Basketo Intellectuals Association-BIA Basketo Intellectual's Association is a non governmental civic society which concern all about the Basket community members.

It works on professional commitment and linking the bridge among professional intellectuals and stakeholder.

Here we Go!👏የተከበሩ ፍቃዱ ጋውሻሎ ነገ ማክሰኞ ግንቦት 18/2018 ዓ.ም  ከጠዋት 2:30 ላይ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩንቨርስቲ የሦስተኛ ድግሪ መመረቂያ ፅሁፋቸውን ያቀርባሉ።ይ...
25/05/2026

Here we Go!
👏

የተከበሩ ፍቃዱ ጋውሻሎ ነገ ማክሰኞ ግንቦት 18/2018 ዓ.ም ከጠዋት 2:30 ላይ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩንቨርስቲ የሦስተኛ ድግሪ መመረቂያ ፅሁፋቸውን ያቀርባሉ።

ይህንን ፕሮግራም ለመታደም የምትፈልጉ በሙሉ አዲስ አበባ ቦሌ ክ/ከተማ CMC አካባቢ በሚገኘው ዩንቨርስቲው ግቢ በመገኘት ከከተማችን ህዝብ ተወካይ ከሆኑት ከዕጩ ዶ/ር ፍቃዱ ጋውሻሎ ጎን እንድትገኙ እናስታውሳችኋለን።

እንኳን ደስ አልዎት የተከበሩ ዶክተር ፍቃዱ ጋውሻሎ!
👏🤝

ኢዜማ ባስኬቶበሻንካ ጋምጋይላ ቀበሌ⚖️ኢዜማ ባስኬቶ በሁሉም የዞኑ ቀበሌያት ሀሳቡን ለመራጩ አቅርቦ የመራጩን ጥያቄ እና የህዝቡን የጋራ አጀንዳ በማንገብ የዜግነት ፖለቲካን በመከተል መዳረሻው...
25/05/2026

ኢዜማ ባስኬቶ

በሻንካ ጋምጋይላ ቀበሌ

⚖️

ኢዜማ ባስኬቶ በሁሉም የዞኑ ቀበሌያት ሀሳቡን ለመራጩ አቅርቦ የመራጩን ጥያቄ እና የህዝቡን የጋራ አጀንዳ በማንገብ የዜግነት ፖለቲካን በመከተል መዳረሻውን ማህበራዊ ፍትህ ለማድረግ በብርቱ ጥረት እየሰራ ይገኛል።

የተሻለች ኢትዮጵያ እስክትመጣ ኢዜማ ትግሉን ከኢትዮጵያ አርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ጋር ያደርጋል!
⚖️
ኢዜማን ይምረጡ!
⚖️

እንኳን ለዓለምአቀፉ የእግር ኳስ መታሰቢያ ቀን በሰላም አደረሳችሁ!⚽ ⚖️ ⚽ ⚖️በየዓመቱ መጋቢት 17 ወይም May 25 የተባበሩት መንግስታት ቀን በዓለምአቀፍ ደረጃ የእግር ኳስ ቀንን ያከብ...
25/05/2026

እንኳን ለዓለምአቀፉ የእግር ኳስ መታሰቢያ ቀን በሰላም አደረሳችሁ!
⚽ ⚖️ ⚽ ⚖️

በየዓመቱ መጋቢት 17 ወይም May 25 የተባበሩት መንግስታት ቀን በዓለምአቀፍ ደረጃ የእግር ኳስ ቀንን ያከብራል። የመንግስታቱ ድርጅት የእግር ኳስ ሀይልን በማመን በመላው ዓለም ለሚገኙ የእግር ኳስ ተጫዋቾች: አስተዳደሮችና ደጋፊዎች የዓለምን አንድነት ለማስከበር ባላቸው ሚና የተነሳ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላልፋል።

እኛ የእግር ኳስ አፍቃሪዎች ተከታታይ የኢዜማ አባላትና ደጋፊዎች በዞናችን ላሉ ሁሉም የእግር ኳስ ተጫዋቾች: አመራሮችና ደጋፊዎች በሙሉ እንኳን አደረሳችሁ ለማለት እንወዳለን።

እግር ኳስ የሰው ልጆችን በሙሉ ዘር ቀለም ሳይለይ አንድ የሚያደርግና የማህበራዊ ፍትህ እንዲሰፍን በዘርፉ ከፍተኛ ድጋፍ እንደሚያደርግ አካል እንኳን አደረሳችሁ ለማለት ይወዳል።

በዛሬው ዕለትም ለመላው የባስኬት ቡና እግር ኳስ ክለብ ተጫዋቾች: አመራሮችና ደጋፊዎች በሙሉ እንኳን አደረሳችሁ ለማለት ይወዳል!
⚖️
በድጋሚ እንኳን ለዓለምአቀፉ የእግር ኳስ ቀን በሰላም አደረሳችሁ!

ኢዜማ ባስኬቶበሣሳ ማኬሣ ቀበሌኢዜማ በትናንትናው ዕለት በሣሳ ማኬሣ ቀበሌ የአደባባይ ላይ ቅስቀሳ አድርጓል። የምርጫ ቅስቀሳው በኢዜማ የመሬት ፖሊሲ እና ሌሎች ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ያደረገ ሲሆ...
25/05/2026

ኢዜማ ባስኬቶ

በሣሳ ማኬሣ ቀበሌ

ኢዜማ በትናንትናው ዕለት በሣሳ ማኬሣ ቀበሌ የአደባባይ ላይ ቅስቀሳ አድርጓል። የምርጫ ቅስቀሳው በኢዜማ የመሬት ፖሊሲ እና ሌሎች ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ያደረገ ሲሆን የአካባቢው ነዋሪም ከምንጊዜው በላይ ለውጥ ናፋቂ እና አዲስ ነገር ለማየት ካደረበት ጉጉት የተነሳ በላስካ ዙሪያ ወረዳ በሣሳ ማኬሣ ቀበሌ በመገኘት ሰፊ ንቅናቄ ፈጥሯል።
⚖️
ኢዜማን ይምረጡ!
⚖️
የምርጫ ምልክታችን ሚዛን ነው!
⚖️

ኢዜማ ባስኬቶበዛባ አካባቢ የምርጫ ቅስቀሳ አደረገ። የላስካ 02 ቀበሌ ነዋሪዎችን ተደራሽ ያደረገ የመሠረተ ልማት እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ላይ የማህበረሰቡን ፍላጎት ያማከለ የግንዛቤ ...
24/05/2026

ኢዜማ ባስኬቶ

በዛባ አካባቢ የምርጫ ቅስቀሳ አደረገ። የላስካ 02 ቀበሌ ነዋሪዎችን ተደራሽ ያደረገ የመሠረተ ልማት እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ላይ የማህበረሰቡን ፍላጎት ያማከለ የግንዛቤ ማስጨበጫ አድርጓል።

ኢዜማ በዛባ እና አካባቢው ቀበሌያት ነዋሪዎች በቀጣይ የምርጫ ሳምንት ውስጥ የኢዜማ የምርጫ ምልክትና የፓርቲውን ፖሊሲዎች የኢዜማ ላስካ መደበኛ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዕጩዎች ተገኝተዋል።

የዛባ እና አካባቢው ነዋሪ ምርጫ ኢዜማ እንደሆነ አረጋግጧል!
⚖️
ባለሚዛን ምልክቱን ኢዜማን ይምረጡ!

ኪነ ጥበባዊ ይዘት ያለው ቅስቀሳ በቦላ ጋባላ ቀበሌ⚖️ኢዜማ ባስኬቶ በላስካ ዙሪያ ወረዳ ቦላ ጋባላ ቀበሌ የአካባቢው ነዋሪዎች በቀበሌው ያለውን የመሠረተ ልማት እጥረት እና የመንግስት የጤና ...
24/05/2026

ኪነ ጥበባዊ ይዘት ያለው ቅስቀሳ በቦላ ጋባላ ቀበሌ
⚖️
ኢዜማ ባስኬቶ በላስካ ዙሪያ ወረዳ ቦላ ጋባላ ቀበሌ የአካባቢው ነዋሪዎች በቀበሌው ያለውን የመሠረተ ልማት እጥረት እና የመንግስት የጤና ጣቢያ ጥራት አለመኖር በታካሚዎች ላይ ያደረሰውን ጫና በኪነ ጥበባዊ ድራማ ተውነው ስሜታቸውን ገልፀዋል።

የኢዜማ ባስኬቶ ልዩ ዕጩዎች በስፍራው ተገኝተው የህዝባችን የመሠረተ ልማት ጥያቄ ትኩረት እስኪያገኝ ድረስ ኢዜማ ትግል እንደሚያደርግ ቃል ገብቷል።

⚖️

የቀበሌው ነዋሪ በነቂስ ወጥቶ ኢዜማን እንደሚመርጥ አረጋግጧል።
⚖️

ኢዜማ ባስኬቶበአውራ ሦስታ ቀበሌየኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ በባስኬቶ ልዩ ምርጫ ክልል በላስካ ዙሪያ ወረዳ በቀጣይ የምርጫ ዝግጅት ላይ ከአካባቢው ነዋሪ ጋር ውይይት አድርጓል።አ...
24/05/2026

ኢዜማ ባስኬቶ

በአውራ ሦስታ ቀበሌ

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ በባስኬቶ ልዩ ምርጫ ክልል በላስካ ዙሪያ ወረዳ በቀጣይ የምርጫ ዝግጅት ላይ ከአካባቢው ነዋሪ ጋር ውይይት አድርጓል።

አውራ ሦስታ ኢዜማን መርጧል!
⚖️

በሀቅ አደባባይእውነት ጎልቶ እንዲታይበፖለቲካ ውጣ ውረድ ውስጥ እንደአንድ ህዝብ እንደማህበረሰብ በጋራ ቆመን በአብሮነት መወሰን እስካልቻልን ድረስ ወደ መግባባት አንመጣም። ለዓመታት በጋራ ጉ...
24/05/2026

በሀቅ አደባባይ

እውነት ጎልቶ እንዲታይ

በፖለቲካ ውጣ ውረድ ውስጥ እንደአንድ ህዝብ እንደማህበረሰብ በጋራ ቆመን በአብሮነት መወሰን እስካልቻልን ድረስ ወደ መግባባት አንመጣም። ለዓመታት በጋራ ጉዳያችን ላይ ውሳኔ የሰጡ ግለሰቦች በውሳኔዎቻቸው ማፈርና መሸማቀቅ ሲገባቸው ወደኋላ ለቀረንበት ውሳኔያቸው ተጠያቂ አካል በመፍጠር ጊዜያቸውን ማራዘም ይሻሉ።

በሀቅ አደባባይ ላይ በእውነት ሚዛን መስራት ሲገባን በጥቃቅን ፍላጎቶቻችን ከማህበረሰባችን የወጡ አካላትን እያገለልን ስናርቃቸው ከርመናል። አሁን የህዝቡን ክቡር ሀሳብ የምንቀበልበት ወቅት ላይ እንገኛለን። የግል ጥፋቶቻችን ለመሸፋፈን የምናደርጋቸው ተጨማሪ ልፍያዎች ከታሪክ ተጠያቂነት እስከ ወንጀለኛነት ያስወስናሉ።

ገዢዎቻችን በኛ ጉዳይ የሰጡን ውሳኔ በሙሉ ዛሬ ላለንበት አዘቅት መነሻ ሆኗል። ከገባንበት ውጥንቅጥ የምንወጣው በእናንተው ስሁት ውሳኔ ሳይሆን በህዝባችን ቀጥተኛ ፍላጎት ነው።

አስፈፃሚዎቻችን ለዘመናት አቅልለው በወሰኑብን አንድ ትውልድ ወደኋላ እንዲቀር አድርገዋል። ለዚህም ተግባራቸው ተጠያቂነታቸው ሊረጋገጥ ይገባል!
🤝

የመድፈኞቹ ወዳጆች⚖️ደስታችሁ ደስታችን ነው!⚖️እንኳን ደስ አላችሁ!
23/05/2026

የመድፈኞቹ ወዳጆች
⚖️

ደስታችሁ ደስታችን ነው!
⚖️
እንኳን ደስ አላችሁ!

ኢዜማ ባስኬቶበጌዜ ኣይማ ቀበሌ⚖️የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ-ኢዜማ ባስኬቶ በላስካ ዙሪያ ወረዳ ጌዜ ኣይማ ቀበሌ ከነዋሪዎች ጋር በመሠረተ ልማት ጉዳይ ተወያይተዋል። የገዢው መን...
22/05/2026

ኢዜማ ባስኬቶ

በጌዜ ኣይማ ቀበሌ
⚖️

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ-ኢዜማ ባስኬቶ በላስካ ዙሪያ ወረዳ ጌዜ ኣይማ ቀበሌ ከነዋሪዎች ጋር በመሠረተ ልማት ጉዳይ ተወያይተዋል። የገዢው መንግስት አርሶ አደሩን በየሦስት ሳምንቱ በየመኖሪያ ቤቱ እየዞረ መዋጮ የሚሰበስበው አካል ለአካባቢው መደበኛ የማብራት አገልግሎት ባለማስገባቱ የህብረተሰቡን ጥያቄ እያወቀ መመለስ አለመፈለጉን አንስተዋል።

ከላስካ 02 ቀበሌ ጋር የሚዋሰነው የዛባ እና ጌዜ ኣይማ ቀበሌ ነዋሪዎች መንግስት የነዋሪዎችን የመሠረተ ልማት ፍላጎት መመለስ ተስኖት አካባቢው ከመብራት አገልግሎት መገለሉን አውስተዋል።

ኢዜማ የመንግስት መሠረተ ልማቶች ለዜጎች በፍትሃዊነት እንዲሰራጭ ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍል እንዲመጣ እየታገለ እንደሚገኝ ማብራሪያ ተሰጥቷል።

ኢዜማ ባስኬቶ ልዩ የምርጫ ካርድ የወሰዱ ዜጎች ባለሚዛን ምልክቱን ኢዜማን እንዲመርጡ ጥሪ ቀርቧል።
⚖️
ኢዜማን ይምረጡ!
⚖️
ሚዛን ነው ምልክታችሁ!

ኢዜማ በላስካ ዙሪያ ወረዳበጌዜ ኣይማ ቀበሌከማህበረሰቡ ጋር ውይይት እያደረገ ነው።
22/05/2026

ኢዜማ በላስካ ዙሪያ ወረዳ

በጌዜ ኣይማ ቀበሌ

ከማህበረሰቡ ጋር ውይይት እያደረገ ነው።

Address

Basketo Laska
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Basketo Intellectuals Association-BIA posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Basketo Intellectuals Association-BIA:

Share