Basketo Intellectuals Association-BIA

Basketo Intellectuals Association-BIA Basketo Intellectual's Association is a non governmental civic society which concern all about the Basket community members.

It works on professional commitment and linking the bridge among professional intellectuals and stakeholder.

26/08/2026

ዛሬ በተደረገው ምርጫ:
✍️

ምንታምር ምልኪያስ- የወጣቶች ም/ቤት ፕረዚዳንት

አንድነት ዮሀንስ- የወጣቶች ፌዴሬሽን ፕረዚዳንት

ሀብተነህ እንዳለ- የወጣቶች ማህበር ፕረዚዳንት

ሆናችሁ በመመረጣችሁ እንኳን ደስ አላችሁ!
🙏
መልካም የሥራ ዘመን ይሁንላችሁ!

የዲን ዐብይ ጌታሁን ህክምና ብዝዎቻችንን አስጨንቆአል። ኦፕሬሽኑ በጭንቅላቱ ውስጥ የታየ እና በየቀኑ እያደገ ያለ እብጠት ነበር። በዚህ ምክንያት አስጊ የሆነ ሁኔታ ከመፈጠሩም በላይ እጆቹና ...
24/08/2026

የዲን ዐብይ ጌታሁን ህክምና ብዝዎቻችንን አስጨንቆአል።

ኦፕሬሽኑ በጭንቅላቱ ውስጥ የታየ እና በየቀኑ እያደገ ያለ እብጠት ነበር። በዚህ ምክንያት አስጊ የሆነ ሁኔታ ከመፈጠሩም በላይ እጆቹና እግሮቹ እንዳይንቀሳቀሱ አድርጒቸዋል።

በመሆኑም ይህንን ነገር ለማስወገድና በሽታውንና መንስኤውን ለመለየትና በዘላቂነት ለማከም 5 ሠዓታትን እንደሚወስድ ቅድመ ግምት በሀኪሞቹ ተደርጎ ዛሬ ከቀኑ5 ሰዓት ላይ የተጀመረ ሲሆን በአምላክ መሀሪነት በእናቱ አማላጅነት በሀኪሞቹ ላይ በፀጋ ባደረው መንፈስ ቅዱስ መሪነት በ3ሰዓት ጭንቅላቱ ውስጥ የነበረው በሽታ ተነቅሎ ሊወጣ ችሎአል። ናሙናውም ወደከፍተኛ ላቦራቶሪ እንደሚላክ ይጠበቃል።

እንግዲህ ቅድመ ኦፕሬሽን ወንድማችን በህመም ስቃይ ፡ ጊዜ ኦፕሬሽን ይተርፍ ይሆን አይሆን የሚል የቤተሰብ ሰቀቀንና የጒደኞች ስጋት እንዲሁም መታመሙ ይፋ ከተደረገ ጀምሮ የእናንተ የኢትዮጲያውያን ርብርብና ፀሎት በኋላ ድህረ ኦፕሬሽን በተሰማው ዜና ደስ እንድንሰኝ ሆነናል።

ይህንን ያደረገ እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን።
ይሄ ጉዳይ ለሦስት ተከታታይ ቀናት ክፉ ሀሳብ እየመጣ ከእንቅልፍ አጣልቶኛል። ዛሬ አንድ ሸክም ከላዬ ወድቆአል። እናም ፈጣሪን አመስግኜ ንቃት ዐልባ እንቅልፍ ለሽ ልል ነው። ደህና እደሩ።

መምህር አንዷለም ሀይለማርያም

ደማስቆ በኛ ቀለም ❤🙏
21/08/2026

ደማስቆ

በኛ ቀለም ❤🙏

የታምራት ስጦታ ለሀዋሪያው ታምራት❤ከሰሞኑን የወጣቶች መንፈሳዊ ጉባኤዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። የተወሰኑት በሀዋሳ የመልካም ወጣት ሲሳተፉ ታምራትና ጓደኞቹ ደግሞ በአዲስ አበባ የCJ Inter...
16/08/2026

የታምራት ስጦታ ለሀዋሪያው ታምራት


ከሰሞኑን የወጣቶች መንፈሳዊ ጉባኤዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። የተወሰኑት በሀዋሳ የመልካም ወጣት ሲሳተፉ ታምራትና ጓደኞቹ ደግሞ በአዲስ አበባ የCJ International Church የወጣቶች ኮንፍራንስ እየታደሙ ይገኛሉ።

ታምራት ለሀዋሪያው ስጦታ እንዳመጣለት ሲነግረኝ አላመንኩትም ነበር። ጊዜው ሲደርስ ስጦታውን ሰጠ ለምዕመኑም ስለመጣበት የባስኬት ማህበረሰብ ተናገራቸው። አካባቢዉንም አስተዋወቀልን።

እናመሰግናለን!🙏በዞን አስተዳደርበከተማ አስተዳደርና በዙሪያ ወረዳ አስተዳደሮች የህዝብ ምክር ቤት በተደረጉ ወቅቱን የጠበቁ የዓመታዊ ሪፖርቶች: እና የቀጣይ ዓመት ዕቅዶች ላይ በመነጋገር በን...
13/08/2026

እናመሰግናለን!
🙏

በዞን አስተዳደር
በከተማ አስተዳደርና
በዙሪያ ወረዳ አስተዳደሮች የህዝብ ምክር ቤት በተደረጉ ወቅቱን የጠበቁ የዓመታዊ ሪፖርቶች: እና የቀጣይ ዓመት ዕቅዶች ላይ በመነጋገር በንቃት መገምገማቸው ለቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎቻችን እንድንለይ መነሻ ይሆኑናል። ይህን ተከትሎ በየምክር ቤቶቹ አገልግሎት ሰጥተው ላገለገሉን አመራሮች በሙሉ ልባዊ ምስጋናችን ይድረሳችሁ!

በሌላ በኩል

በተለያዩ የአስተዳደር መዋቅሮች የህዝብን ጥያቄ ለመመለስና በተሻለ ታሪካዊ አፈፃፀም ለመስራት ሀላፊነት ለተረከባችሁ የየመዋቅሮቹ አስተባባሪ ኮሚቴዎችና የካቢኔ አባላት መልካም የሥራ ዘመን እንዲሆንላችሁ እንመኛለን!

በዞን አስባባሪነት የተመደባችሁ

እንጂነር በዛብህ ገበየሁ
ዶ/ር ሰላምነሽ ጌታቸው
ክንፉ ሻቦ
ፍሬው አረጋ
በሀይሉ ባባሮ

በከተማ አስተዳዳር አስተባባሪነት የተመደባችሁ

እንጂነር በሃይሉ አጎናፍር
ለማ መንገሻ
ጳውሎስ ሀይሌ
አምባዬ ፀደቀ
እንጂነር ዝናሽ አግዘው

በዙሪያ ወረዳ አስተባባሪነት የተመደባችሁ

ከፈለው በለጠ
ኤቤኔዘር መሰለ
ወራፎ አወቀ
አሙለ ጋረደው
አጎናፍር ሙላት

በፍፁም ልባዊ ቅንነት ህዝባችን ለማገልገል በወሰዳችሁት ሃላፊነት: በሰጣችሁን ተስፋ እና በምታሳዩን ቅንነት እንደምታገለግሉን በመተማመን መልካም የትጋት ዘመን እንዲሆንላችሁ ልባዊ ምኞታችን እንገልፃለን!
🤝

የምክክሩ ሂደትና የባስኬቶ ተሳትፎ✍️በዚህ ትውልድ ታላቅ ገድል ሆኖ የተመዘገበው የሀገራዊ ምክክር ከተለያዩ መዋቅሮች የተሳተፉ 4,000 ሰዎች እየተመካከሩ መሆኑ ይታወቃል። ከደቡብ ክልል የተ...
01/08/2026

የምክክሩ ሂደትና የባስኬቶ ተሳትፎ
✍️

በዚህ ትውልድ ታላቅ ገድል ሆኖ የተመዘገበው የሀገራዊ ምክክር ከተለያዩ መዋቅሮች የተሳተፉ 4,000 ሰዎች እየተመካከሩ መሆኑ ይታወቃል። ከደቡብ ክልል የተወከሉ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ከ450 በላይ እንደሆኑ ሲገመት 12 ባስኬተኛ ተናጋሪዎች በንቃት እየተሳተፉበት ይገኛል።

በእያንዳንዱ ቡድን የባስኬቶን ህዝብ ጥያቄ ከግንዛቤ በማስገባት እየተወያዩ ሲሆን በዋናነት 500 ሰዎች ውሳኔ በሚሰጡበት የ500 ሰዎች አጀንዳ አዘገጃጀት ውስጥ በፀሐፊነት የሚሳተፉ የኛ ተሳታፊዎች ቁጥር ሦስት መሆኑን አረጋግጠናል።

ከዋና ዋና ለውሳኔ የሚቀርቡ አጀንዳዎችን ከሚፅፉበት

አጀንዳ 2 ውስጥ የመንግስት አደረጃጀት እና ቅርፅ
አጀንዳ 6 ውስጥ የማህበራዊ ጉዳይና የአርብቶ አደር አካባቢዎች
አጀንዳ 3 ውስጥ የፌዴራል ከተሞች
አጀንዳ 5 ውስጥ የተቋማት ግንባታ: የህግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች
አጀንዳ 7 ውስጥ ሙስና እና መልካም አስተዳደር

በእነዚህ ቡድኖች ውስጥ የባስኬቶ ተወካዮች ከባለ10 ቡድን እስከ 500 ተመካካሪዎች ያለውን የፀሐፊነት ሚና በተግባር እየተወጡ እንደሆነ ልናሳውቃችሁ እንወዳለን። የባስኬቶ ህዝብ አጀንዳ እንደየርዕሰ ጉዳዩ በየሁኔታዎች በምሳሌነት ተጠቃሽ እየሆነ እንደሆነ ለማሳወቅ እንወዳለን።

ከዚህ ጋር ተያይዞ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የምክክር ተሳታፊዎች ውስጥ በዚህ ታሪካዊ ሂደት ውስጥ የህዝባችን ጥቅም ለማስከበር በእልህ አስጨራሽ ትግል ከህዝባችን ጎን ለቆሙ 12ቱ ተሳታፊዎቻችን ምስጋናችን ለማቅረብ እንወዳለን። ያለአንዳች ልዩነት ከታችኛው መዋቅር ጀምሮ ለዚህ ታሪካዊው ሀገር አቀፍ ምክክር የህዝባችን ጥያቄ ለማንፀባረቅ ዕድሉን ለሰጠን የባስኬቶ ህዝብ ምስጋናችን ላቅ ያለ ነው።

መልካም የስራ ዘመን ይሁንላችሁ!✍️የባስኬቶ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ከሰሞኑን ባደረገው አስቸኳይ ጉባኤው በክልሉ ገዢ ፓርቲ አቅራቢነት የዞን አስተዳደሩ አስተባባሪ ኮሚቴ ሆናችሁ ሃላፊነት ለተቀ...
25/07/2026

መልካም የስራ ዘመን ይሁንላችሁ!
✍️

የባስኬቶ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ከሰሞኑን ባደረገው አስቸኳይ ጉባኤው በክልሉ ገዢ ፓርቲ አቅራቢነት የዞን አስተዳደሩ አስተባባሪ ኮሚቴ ሆናችሁ ሃላፊነት ለተቀበላችሁ በሙሉ መልካም የስራ ዘመን ይሁንላችሁ!

ክቡር ኢንጅነር በዛብህ ገበየሁ የባስኬቶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ
ክብርት ዶ/ር ሰላምነሽ ጌታቸው የባስኬቶ ዞን ም/አስተዳዳሪ

እና

ሌሎች በባስኬቶ ዞን ህዝብ ምክር ቤት የመንግስት ተጠሪዎች

በድጋሚ መልካም የአገልጋይነት ዘመን ይሁንላችሁ!

እናመሰግናለን 🙏የቀድሞ የባስኬቶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር ሳሙኤል ደሳለኝ እና የቀድሞ የባስኬቶ ዞን ህዝብ ምክር ቤት የመንግስት ዋና እና ረዳት ተጠሪዎች በህዝብ ምክር ቤቱ ውስጥ ላደረጋች...
23/07/2026

እናመሰግናለን 🙏

የቀድሞ የባስኬቶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር ሳሙኤል ደሳለኝ እና የቀድሞ የባስኬቶ ዞን ህዝብ ምክር ቤት የመንግስት ዋና እና ረዳት ተጠሪዎች በህዝብ ምክር ቤቱ ውስጥ ላደረጋችሁልን ሁሉ እናመሰግናለን!

ትናንትን አብረን ከጎናችን እንደሆናችሁ ሁሉ ነገም እንደማትለዩን ባለሙሉ ተስፋ ነን!
🙏
በባስኬቶ ህዝብ ስም በምክር ቤቱ ለነበራችሁ የመንግስት ተጠሪነት ምስጋናችን ከልብ ነው!

"ለተሻለ ነገ እመክራለሁ!"ኤደን ከሰሜን አሪ ወረዳ ገሊላ ከተማ
13/07/2026

"ለተሻለ ነገ እመክራለሁ!"

ኤደን ከሰሜን አሪ ወረዳ ገሊላ ከተማ

አምባሳደር መላው ጌታቸው ቢረጋ💪በአሁኑ ሰዓት በፓኪስታን ሀገር የኢትዮጵያ ኢምባሲን እየመራ የሚገኙው የባስኬቶው ጀግና መላው ጌታቸው ቢረጋ ነው።ፓኪስታን በእሲያ ከሚገኙ የኑክሌር ባለቤት ሀገ...
11/07/2026

አምባሳደር መላው ጌታቸው ቢረጋ
💪

በአሁኑ ሰዓት በፓኪስታን ሀገር የኢትዮጵያ ኢምባሲን እየመራ የሚገኙው የባስኬቶው ጀግና መላው ጌታቸው ቢረጋ ነው።

ፓኪስታን በእሲያ ከሚገኙ የኑክሌር ባለቤት ሀገራት ውስጥ አንዷ ነች።

ለዚህ ታላቅ ሀገራዊ ተልዕኮ የተመደበውን ወንድማችን መላውን መልካም የስራ ዘመን በሉልን!
🤝

Address

Basketo Laska
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Basketo Intellectuals Association-BIA posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Basketo Intellectuals Association-BIA:

Shortcuts

Share