Editors Guild of Ethiopia

Editors Guild of Ethiopia The Editors Guild of Ethiopia is a professional association for editors in Ethiopia working at print, broadcast and online media companies.

ውድ የኢትዮጵያ አርታኢያን ማህበር አባላት እና የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች…የኢትዮጵያ አርታኢያን ማህበር International Home of Journalists (IHJ) አባል እንደመሆኑ ፣ ከዚህ በ...
07/04/2026

ውድ የኢትዮጵያ አርታኢያን ማህበር አባላት እና የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች…
የኢትዮጵያ አርታኢያን ማህበር International Home of Journalists (IHJ) አባል እንደመሆኑ ፣ ከዚህ በታች ከተዘረዘሩት ሦስት ዕድሎች ውስጥ በመረጡት አምድ እንዲሳተፉ ይጋብዛል። የሚያሳዩት ትዕይንት ፣ የሚያጋሩት ክስተት/ገጠመኘ ፣ ወይም የሚያቀርቡት ዕይታ ካለዎት ፣ መላው ዓለም ከእርስዎ መስማት ይፈልጋል።
1. OnSene - ገጠመኝዎን ያጋሩ https://www.facebook.com/permalink.php?story_fbid=pfbid02aXu8zXo3nmkV1qa1Qr6NiPiXGkBexsS9fqZ1QHweHmyWjJ3kSHKJWuEhvNVRVcxJl&id=61571348563575
አንድ የዜና ታሪክ ሲከሰት በፎቶ ወይም በቪዲዮ ከያዙ ፤ ወይም ከሪፖርትዎ ጀርባ ያለውን ገጠመኝ በዓለም ዙሪያ ላሉ ጋዜጠኞች ማካፈል ከፈለጉ።
• ገጠመኙን የሚያሳይ አጭር ቪዲዮ/ፎቶ
• ዘገባዎትን እና አስፈላጊነቱን የሚያብራራ መግለጫ (እስክ 200 ቃላት)
• የእርስዎ ስም ፣ የሚሰሩበት የሚዲያ ተቋም እና ክልል
2. HomeofJournalists - የድርጅትዎን እንቅስቃሴ ያካፍሉ https://www.facebook.com/permalink.php?story_fbid=pfbid02JnFMtFKctQvvfDMUZJrCxpZR6XopzpueQKQMxisagdvRXrTNm35hZZKqSAsX2Hkbl&id=61571348563575
ጋዜጠኛ ከሆኑ እና በጋዜጠኛ ማህበራት ወይም በሚዲያ ተቋማት ውስጥ ንቁ ተሳትፎ የሚያደርጉ ከሆነ ፤ በተጨማሪም የጋዜጠኞችን መብት ለማስጠበቅ ፣ የሙያ ክህሎትን ለማጠናከር ፣ የጋራ እሴቶችን ለማክበር እና በሙያው ውስጥ ያለዎትን የክብር እና የስነ-ምግባር ደረጃ ለማዳበር የሚተጉ ከሆኑ።
• ይህን በአግባቡ የሚያሳዩ በአንድ ፕሮግራም ላይ የተያዙ ፎቶዎች/አጫጭር ቪዲዮዎች
• ቢበዛ 200 ቃላት ፡ ያደረጉት አስተዋፅኦ
• የእርስዎ ስም ፣ ድርጅት እና አካባቢ
3. LeadingVoices - እይታዎን ያጋሩ https://www.facebook.com/permalink.php?story_fbid=pfbid02PjucC5HzDQDiVHWWRQ3mtrLeuqZtRtQ31ux2goq8pKkmy6MAyPftV1gb3xZxrXJTl&id=61571348563575
ዛሬ በፍጥነት እየተለዋወጠ ባለው ዓለም ውስጥ ጋዜጠኝነት ማለት ምን ማለት ነው? እና ምንስ መስዋዕትነት ይጠይቃል?
• በዚህ ዙርያ ያለዎትን አጭር አስተያየት (100-150 ቃላት)
• አንድ የእርስዎን ፎቶ
• የእርስዎ ስም ፣ የስራ ቦታ እና ክልል
ፍላጎቱ አለዎት? ማጋራት የሚፈልጉትን ወይም ጥያቄዎችዎን በቀጥታ ለኢትዮጵያ አርታኢያን ማህበር ቀጥሎ ባለው የኢሜይል አድራሻ መላክ ይችላሉ፡፡ በሂደቱም ላይ ማህበራችን እገዛ ያደርግልዎታል [email protected]
Dear EGE Members and Journalists in Ethiopia,
As a member of the International Home of Journalists (IHJ), Editors' Guild of Ethiopia invites you to take part in three global columns. Whether you have a scene to show, an event to share, or a perspective to offer, we want to hear from you.
1. OnScene – Share your moment from the field https://www.facebook.com/permalink.php?story_fbid=pfbid02aXu8zXo3nmkV1qa1Qr6NiPiXGkBexsS9fqZ1QHweHmyWjJ3kSHKJWuEhvNVRVcxJl&id=61571348563575
If you have witnessed a news story unfold right before your eyes and want to share the moments behind your reporting with journalists around the world.
• Short video/photo of you working on a story
• Max 200 words: what you covered and why it matters
• Your name, media affiliation, and location
2. HomeofJournalists – Share your organization's activity https://www.facebook.com/permalink.php?story_fbid=pfbid02JnFMtFKctQvvfDMUZJrCxpZR6XopzpueQKQMxisagdvRXrTNm35hZZKqSAsX2Hkbl&id=61571348563575
If you are a journalist who is also active in a journalists' association or media organization, and dedicated to protecting journalists' rights, strengthening professional skills, upholding shared values, and fostering a stronger sense of honor and belonging within the profession.
• Photos/short videos from an event or initiative
• Max 200 words: what you did and your reflections
• Your name, organization, and location
3. LeadingVoices – Share your perspective https://www.facebook.com/permalink.php?story_fbid=pfbid02PjucC5HzDQDiVHWWRQ3mtrLeuqZtRtQ31ux2goq8pKkmy6MAyPftV1gb3xZxrXJTl&id=61571348563575
What does it mean to be a journalist in today's rapidly changing world? And what does it take?
• A short comment (100–150 words) on journalism today
• One portrait photo
• Your name, affiliation, and location
Interested? Reach out to EGE directly with your content or questions, and we will guide your submission: [email protected]
Let's share with the world Ethiopian journalism – from the field, from our organizations, and from our leading voices!

EGE extends its warmest congratulations to Meron Aragaw! This is a well-deserved recognition and a powerful inspiration ...
03/04/2026

EGE extends its warmest congratulations to Meron Aragaw! This is a well-deserved recognition and a powerful inspiration for fellow women lawyers from Ethiopia.

ሜሮን አራጋው ከአፍሪካ 100 ተጽእኖ ፈጣሪ ሴት የሕግ ባለሙያዎች አንዷ ሆነው ተመረጡ

ኮርትሩም ሜይል 100 (Courtroom Mail 100) የተሰኘ ተቀማጭነቱ በናይጄሪያ የሆነ ከፍተኛ ልምድ ያላቸው እና በሰብ ሳህራ አፍሪካ እና በሌሎች የአፍሪካ አገራት ያሉ የሕግ ባለሙያዎች ኘላትፎርም (Panel of Experts) ባካሄደው ምርጫ ከተሰማሩበት፣ የሕግ፣ የጥብቅና፣ የአድቮከሲ...ስራዎች በተጨማሪ በማኀበረሰቡና በፖሊሲ አውጪዎች ዘንድ በጎ ተጽእኖ ያሳረፈ ስራ ያከናወኑ ሴት የህግ ባለሙያዎችን በጥንቃቄ በመምረጥ በየዓመቱ የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን ተመስርቶ እውቅና ይሰጣል። ከዚህ ቀደም ከኢትዮጵያ ብርቱካን ሚደቅሳ እውቅናውን አግኝተዋል።

በድርጅቱ የ2026 ምርጫ መሰረት ከኢትዮጵያ ሜሮን አራጋው በብቸኝነት ተመርጠው እውቅናውን አግኝተዋል።

ሜሮን አራጋው የስርአተ-ፆታ፣ የወጣቶች እና የማህበራዊ ጉዳዮች ማካተት ጉዳይ በአለምአቀፍ ድርጅት ከፍተኛ አማካሪ ሲሆኑ ከዚህ ቀደም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሴቶች፣ ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ምክትል ኃላፊና የሴቶች ዘርፍ ኃላፊ ሆነው አገልግለዋል። የኢትዮጵያ የህግ ባለሙያ ሴቶች ማህበር የስራ አስፈጻሚ ዳይሬክተርነት መርተዋል። በተጨማሪም የተለያዩ ተቋማት በማማከር፣ በጥናትና ምርምር እንዲሁም በሴቶችና በህፃናት የመብት ጉዳዮች ተሟጋችነትም ይታወቃሉ።
#ድሬቲዩብ

25/03/2026
 #ፍትህአወቅ የወንድወሰን (የሙያ ታሪክ)በተወዳጅ ሚድያ (ዕዝራ እጅጉ )የተዘጋጀ #ጋዜጠኝነት የሚድያ ሰው ፍትህአወቅ የወንድወሰን የምስራቅ አፍሪካ አርታዒያን ሶሳይቲ (EAES) ፕሬዝዳንት ...
03/03/2026

#ፍትህአወቅ የወንድወሰን (የሙያ ታሪክ)

በተወዳጅ ሚድያ (ዕዝራ እጅጉ )የተዘጋጀ

#ጋዜጠኝነት የሚድያ ሰው ፍትህአወቅ የወንድወሰን የምስራቅ አፍሪካ አርታዒያን ሶሳይቲ (EAES) ፕሬዝዳንት ሆኖ ተመርጧል።

በምስራቅ አፍሪካ የሚዲያ ዘርፍ ላይ ኢትዮጵያ ያላትን ተሰሚነት የሚያጎላ አዲስ ምዕራፍ ተመዝግቧል። እ.ኤ.አ. የካቲት 28 ቀን 2026 በናይሮቢ በተካሄደው የአፍሪካ ሚዲያ ፌስቲቫል ማጠናቀቂያ ላይ፣ ፍትህአወቅ የወንድወሰን የሶሳይቲው ፕሬዝዳንት በመሆን በከፍተኛ ድምፅ ተመርጧል።
* ምክትል ፕሬዝዳንት፦ ወ/ሮ ዙቤይዳ ካኑ (ከኬንያ አርታዒያን ማህበር)

"ይህ ምርጫ ለኢትዮጵያ አርታዒያን ብቻ ሳይሆን፣ በቀጠናው ለሚገኙ ሁሉም የሙያ ባልደረቦች የጋራ እድገት ትልቅ ፋይዳ አለው።"

#ስለ ምስራቅ አፍሪካ አርታዒያን ሶሳይቲ (EAES)

የምስራቅ አፍሪካ አርታዒያን ሶሳይቲ (EAES) የአምስት ሀገራት የሚዲያ ማህበራት ጥምረት ሲሆን፣ አባላቱም ኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ታንዛኒያ፣ ዩጋንዳ እና ደቡብ ሱዳን ናቸው። ሶሳይቲው በዋናነት በፕሬስ ነፃነት፣ በሙያ ስነ-ምግባር እና በጋራ ልማት ላይ ትኩረት አድርጎ ይሠራል።

ተወዳጅ ሚድያም የጋዜጠኞችን ታሪክ በዲጂታል ሚድያ እና በመፅሐፍ የሚሰንድ ሲሆን በዚህ መሠረት የፍትህ አወቅ ሙያዊ አስተዋፅኦ በተወዳጅ ሚድያ የመዝገበ አእምሮ ቦርድ የሚመጥ ሆኖ በመገኘቱ ታሪኩን ሰንደነዋል። ዕዝራ እጅጉ ታሪኩን እንደሚከተለው ያቀርበዋል።

፨፨፨፨፨፨፨፨ ፨፨፨፨፨ ፨፨፨፨፨፨

አባቱ አቶ የወንድወሰን ወደ ንባቡ አለም እንዲሳብ መሠረት ሆነውታል። እርሳቸው ጋዜጣና መፅሔት የማንበብ ልምዱ ስለነበራቸው ፍትህ ገና በታዳጊነት ህትመቶቹን እየተቀበለ ያነብ ነበር። ይህ ንባቡ ዛሬ ለያዘው ዕውቀት መነሻ ሆኖታል። ፍትህ በደንብ ማንበቡን የተረዱት አባቱ ፊልድ ደርሰው ሲመለሱ ምን አዲስ ክስተት አለ? ብለው የሚጠይቁት ፍትህን ነበር። እርሱም የቤት ውስጥ የዘጋቢነት ኃላፊነቱን እየተወጣ አለም እንዴት እንደሰነበተች ለአባቱ መረጃ ያቀርባል። አባትም በልጃቸው የመተንተን ፣ የማስረዳት አቅም እየተደሰቱ ጎሽ ልጄ ይሉት ነበር።

ታላቅ ወንድሙ ለአለም የወንድወሰን እንደሚናገረው ፍትህ በትምህርቱም እየበረታ ፣ አለምአቀፍ ዕውቀቱንም እንደያዘ ወደ ዩኒቨርሲቲ ሊገባ ችሏል።

".....ፍትህ ከበፊት ጀምሮ ነገሮችን ሚዛን አስጠብቆ በማስኬድ ያምናል። የሚያነባቸው የፖለቲካል ኢኮኖሚ መፅሐፎች እገዛ ስለሚያደርጉለትም በአለም አቀፍ ጉዳይ ላይ ያለው መረዳት ከፍ ያለ ነው። ሲያወራም በቀላሉ የማሳመን ክህሎት አለው። ለእኔ 5ኛ ታናሼ ሲሆን ባለው የተለየ ዕውቀት አከብረዋለሁ።ከበፊትም ጀምሮ ለአመራር የሚሆን ሰብዕና እና አቅም እንዳለው እገነዘብ ነበር። አሁን በተግባር የማየውም ይህን የሊደርሺፕ ችሎታውን ነው። " በማለት ታላቅ ወንድሙ ምስክርነት ሰጥቷል።

ፍትህ ብዙም ሳያጠና ከሚገባቸው ጎበዝ ተማሪዎች አንዱ ነበር። ከክፍል አንደኛ ሲወጣ ተማሪዎች መቼ አጥንቶ ነው እያሉ ይገረሙበት ነበር። ፍትህ በፍልስፍና ፣ በፖለቲካ፣ በቀጠና ጉዳዮች ፣ በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ማንበብ ርካታ ይሰጣዋል። ዛሬም ቢሆን ፍትህ መፅሐፍት ከእጆቹ አይለዩም። በአገር ውስጥ ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ለአንዳንድ ሚድያዎች እና የፖለቲካ ፓርቲዎች ትንታኔ ይሠጣል። ይህ እንግዲህ ከአለምአቀፍ ፖለቲካ ጋር ያለውን የቅርብ ትስስር የሚያሳየን ሲሆን እርሱም ይህን አቅሙን በየጊዜው እያዳበረ ሄዶ ዛሬ ላይ መድረስ ችሏል።

ፍትህ በአንድ ወቅት ሶማሌ ክልል ለዘገባ አቅንቶ በነበረው ውጥረት ጥይት ካረፈበት ሆቴል እንዳለፈ ይነገራል። ይህም ለሙያው የከፈለውን ዋጋ የሚያሳየን ነው።

ፍትህ በ1998 ዓ.ም ወደ ሚድያው አለም ሲቀላቀል የዜና ክፍል ኃላፊ የነበረችው ብርቱካን ሐረገወይን የፍትህአወቅን ችሎታ ታደንቅ ነበር። እንዲህ ትላለች"... ያኔ አብረውት ከተቀጠሩት መካከል የተሻለ መረዳት ነበረው። የሚፅፋቸው ዜናዎችም በሳል እንደነቀሩ አስታውሳለሁ። የሚሠራውን ዜና በሚገባ አውቆት ስለሆነ ሚዛናዊ እና በዕውቀት የተሞላ ዘገባ እናገኝ ነበር። የፖለቲካ ዘገባን በልዩ መልኩ ይገነዘብ ነበር። ደግሞም በፍጥነት ስለሚያደርስ ይደነቅ እንደነበር አስታውሳለሁ። ፎርማት በመቅረፅና እና በአመራር ቦታም ላይ ሁኖ የተቻለውን እንዳደረገ አውቃለሁ" ስትል ብርቱካን ከተወዳጅ ሚድያ ለተጠየቀችው ምላሽ ሰጥታለች።

#የሐረር ልጅ!

ታሪካዊቷ የሐረር ከተማ ካበቀለቻቸው የሚድያ ፈርጦች መካከል ይጠቀሳል። ትውልድና እድገቱ በሐረር ከተማ የሆነው ፍትህአወቅ የወንድወሰን የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በየሺህ እመቤት ት/ቤት፣ በልዑል ራስ መኮንን ት/ቤት እና ሐረር ኤስ ኦ ኤስ ት/ቤቶች ተከታትሏል።

ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ዲግሪውንም አግኝቷል።

#ጋዜጠኛው

ከተማሪነት አንስቶ በሚድያና ጥበብ ንቁ ተዋናይ የሆነው ፍትህአወቅ ሚያዝያ 1998 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ራድዮን በመቀላቀል የጋዜጠኝነት ሙያውን ጀመረ። ከኢትዮጵያ ራድዮ ዜና ፋይል አንጋፋ ጋዜጠኞች ጋር መስራቱ በአጭር ጊዜ በሙያው ከፍተኛ ብቃት እንዲላበስ እንደረዳው ይናገራል። በ2001 የኢትዮጵያ ራድዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ውህደትን ተከትሎ በቴሌቪዥን ጋዜጠኝነትም ስማቸው ከሚጠቀሱ የ2000ዎቹ ጋዜጠኞች መካከል ሆነ።ከሪፖርተርነት እስከ ዋና አዘጋጅነት በቆየበት ኢቲቪ ለ12ዓመታት አገልግሏል።

ፍትህአወቅ የወንድወሰን በታላላቅ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና የዲፕሎማሲ የዜና ዘገባዎቹ እና ትንታኔዎቹ የሚታወቅ ሲሆን በተለይም 'ሚድያ ዳሰሳ' እና 'ዲፕሎማሲያችን' ፕሮግራሞች ከተመልካች ቤት ደርሷል። የአፍሪካ መዲና ከሆነችው አዲስ አበባ በርካታ የአፍሪካ ህብረት ጉባኤዎችን የዘገበ ሲሆን በተለያዩ የዓለም ሀገራት በመዘዋወር በርካታ ዓለም አቀፍ ዘገባዎችን አቅርቧል።

ከ2010 ዓ.ም አንስቶ ፍትህአወቅ የወንድወሰን ከባልደረቦቹ ጋር በመሆን የሚድያ ስራዎችን ማከናወኑን ቀጥሏል። በአሐዱ ራድዮ 94.3 'ቅዳሜ ገበያ' የሚሰኝ የቢዝነስና ኢኮኖሚ ሾው ዘወትር ሰኞ፣ ረቡዕ እና አርብ እያዘጋጀ ይገኛል።

ፍትህአወቅ የኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን አቅም ለማጎልበትና፣ ለመብታቸው ለመሟገት የተቋቋመው የኢትዮጵያ ዓርታኢያን ማህበር መስራች አባል ሲሆን የማህበሩ የጠቅላላ ጉባኤ ሰብሳቢ በመሆን እያገለገለ ይገኛል። ከኢትዮጵያ ባሻገር በአፍሪካ የነቃ ተሳትፎ በማድረግ የአፍሪካ አርታኢያን ፌደሬሽን አባል ሲሆን የምስራቅ አፍሪካ አርታኢያን ሶሳይቲ የቦርድ አባል ነው። ጋዜጠኛ ፍትህአወቅ በ2026 በተደረገው ጉባኤ የምስራቅ አፍሪካ አርታኢያን ሶሳይቲ ፕሬዘዳንት ሆኖ በመመረጥ የምስራቅ አፍሪካ ጋዜጠኞችን የማገልገል ኃላፊነት ተቀብሏል።

አብዱል ሰመድ መሐመድ ከፍትህአወቅ ጋር ከ17 አመት በላይ ትውውቅ አለው። አብዱልሰመድ ፍትህን ሲገልፀው ለነገሮች ልዩ ትኩረት የሚሰጥ ጠንካራ ሰው ይለዋል።ሀሣቡንም አብራርቶ ሲገልፅ አብዱልሰመድ እንዲህ ይላል

"....ፍትህ ፖለቲካ ሳይንስ እንደማጥናቱ በአለም ፖለቲካ ላይ የመተንተን ልዩ ክህሎት አለው ። ኢቲቪ በሠራባቸው ጊዜያትም ዜና ክፍል ኃላፊ ሆኖ ይሠራ ነበር። በዚያን ወቅት የማስተባበር ችሎታው ገራሚ ነው።" በማለት አብዱልሰመድ ምስክርነት ሰጥቷል።
ፍትህ እንደተባለው ከስሩ ያሉትን ሪፖርተሮች አሰማርቶ ሁሉንም እንደ ችሎታቸው ይዞ በጥሩ አክብሮት ሲያሠራቸው እንደነበር ብዙዎች ይመሰክራሉ። አብዱልሰመድ ይህን ተባብሮ የመሥራት ችሎታውን ያደንቅለታል።

"... ፍትሕ አንድ ነገር ከጀመረ ሳያጠናቅቀው አይተኛም።አዳዲስ ፕሮግራሞች የማፍለቅ ሀሣቦችንም የማዳበር ችሎታን ታድሏል።በአሐዱ ሬድዮ የሚቀርበው ቅዳሜ ገበያ የሚለውን ስም ፍትህ እርሱ ነው ያወጣው። ፕሮግራሙም ላይ እንደ አዘጋጅ የራሱን ትልቅ አሻራ ማኖር ችሏል።ፍትህአወቅ የአርታኢያን ማህበር እንዲመሠረት ትልቅ ጥረት አድርጎ ልፋቱም ፍሬ አፍርቷል። በአርታኢያን ማህበር ላይ በውይይት መድረክ የሚነሱ ሀሣቦች ጥልቅ እንዲሆኑም የተቻለውን ጥረት አድርጓል። የምስራቅ አፍሪካ አርታኢያን ማህበር ፕሬዚዳንት ሆኖ በመመረጡም የተሰማኝን ደስታ መግለፅ እወዳለሁ" በማለት አብዱል ሰመድ ምስክርነቱን ለተወዳጅ ሚድያ ሰጥቷል።

#ነፃነት ፈለቀ ስለ ፍትህአወቅ

ነፃነት በኢቢሲ የዕቅድ ዲፓርትመንት ኃላፊ ስትሆን ስለ ፍትህ ይህን ምስክርነት ሰጥታለች።

እኔ ፍትህአወቅ የወንደወሰንን የማውቀው ኢትዮጵያ ሬዲዮ ዜና ክፍል በሪፖርተርነት ሲቀጠር ጀምሮ ነው፤ በወቅቱ የዘገባ ሥራዎቹ ጥንቅቅ ያሉ ስለነበር ትንሹ ኤዲተር ይባል ነበር። የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ዜናና ወቅታዊ ክፍል በነበረበት ወቅትም የዘገባ ሥራዎቹ በመረጃ የዳበሩና ጥልቀት ያላቸው ናቸው፤ በቀጥታ ዘገባ ሥራው ንግግሩ የጽሑፍ ያህል ፍሰት ያለውና የአድማጭ ተመልካቹን ቀልብ የመያዝ አቅም የነበረው ነው። ቴሌቪዥን ላይ በዜና ኤዲተርነት አሉ ከሚባሉ የይዘት ኤዲተሮች አንዱ ነው። በወቅታዊ ፕሮግራሞችም እንዲሁ። ፍትህ ዓለም አቀፍና ሀገራዊ የፖለቲካ አውዱን በሚገባ ተረድቶ ወደ ሚዲያ ይዘት የሚቀይርበት አቅም ሁሌም የሚያስደንቅ ነው። ሪፖርተሮችን የማዳመጥና የተረጋጋ ተግባቦቱ ለሌሎች አስተማሪ ነው።
ፍትህ የምስራቅ አፍሪካ የኤዲተሮች ማሕበር ፕሬዝዳንት ሆኖ መመረጡ አቅሙን ለአፍሪካውያን ወንድሞች የማጋራት ዕድል ስለሚፈጥርለት እንኳን ደስ ያለህ ማለት እፈልጋለሁ። ከዚህም በላይ ይገባሃል 🙏

#ፍሬው አበበ ስለ ፍትህአወቅ

ፍትህአወቅ የወንድወሰን የዛሬ 7 አመት ገደማ የኢትዮጵያ አርታኢያን ማኀበር ከመሰረቱ ጥቂት ጋዜጠኞች ግንባር ቀደሙ ነው። ማኀበር መመስረት ብቻም ሳይሆን ማኀበሩ በሁለት እግሩ እንዲቆም በአመራርነት የላቀ ሚናውን ተወጥቷል። በእሱና በባልደረቦቹ ጥረት በአሁን ሰአት ማኀበሩ ለአባላቱ መብትና ጥቅም መቆም የሚችልና በጎ ተጽእኖ ፈጣሪ ለመሆን ችሏል።
ፍትህአወቅ በአሁን ሰአትም የማኀበሩ የጠቅላላ ጉባኤ ሰብሳቢ በመሆን በማገልገል ላይ ይገኛል።

ፍሬው አበበ

የኢትዮጵያ አርታኢያን ማኀበር ቦርድ ሰብሳቢ

የኢትዮጵያ አርታዒያን ማህበር አቶ ፍትህአወቅ የወንድወሰን የምስራቅ አፍሪካ አርታዒያን ሶሳይቲ (EAES) ፕሬዝዳንት ሆነው በመመረጣቸው የተሰማውን ታላቅ ደስታ ይገልፃል።እ.ኤ.አ. የካቲት 2...
03/03/2026

የኢትዮጵያ አርታዒያን ማህበር አቶ ፍትህአወቅ የወንድወሰን የምስራቅ አፍሪካ አርታዒያን ሶሳይቲ (EAES) ፕሬዝዳንት ሆነው በመመረጣቸው የተሰማውን ታላቅ ደስታ ይገልፃል።
እ.ኤ.አ. የካቲት 28 ቀን 2026 በናይሮቢ በአፍሪካ ሚዲያ ፌስቲቫል ማጠናቀቂያ ላይ በተካሄደው የምስራቅ አፍሪካ አርታዒያን ሶሳይቲ የአመራር ምርጫ ላይ አቶ ፍትህአወቅ በፕሬዝዳንትነት ወ/ሮ ዙቤይዳ ካኑ (ከኬንያ አርታዒያን ማህበር ) በምክትል ፕሬዝዳንትነት ተመርጠዋል፡፡
የአቶ ፍትህአወቅ በፕሬዝዳንትነት መመረጥ የኢትዮጵያ አርታዒያን ማህበር በቀጠናው ላይ ያለውን ተሰሚነት የሚያጎላ ሲሆን ፤ በእርሳቸው የስልጣን ዘመን ማህበራችን የቀጠናውን የሚዲያ ገጽታ ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ እና ድንበር ተሻጋሪ የአርታኢያን ትብብሮችን ለማጎልበት ያለውን ቁርጠኝነት ለመግለፅ ይወዳል።
የምስራቅ አፍሪካ አርታዒያን ሶሳይቲ (EAES) በኬንያ ፣ ታንዛኒያ ፣ ዩጋንዳ ፣ ደቡብ ሱዳን እና ኢትዮጵያ የሚገኙ የአርታዒያን ማኅበራት ጥምረት ነው፡፡
Editors’ Guild of Ethiopia (EGE) proudly congratulates Fitihawok Yewondwossen on his election as President of the Eastern Africa Editors’ Society (EAES).
The election, held on February 28, 2026, in Nairobi during the African Media Festival, is a significant institutional honor for the EGE. Fitihawok now carries the collective mandate and values of the Guild to the helm of the EAES (a coalition of editors’ societies from Kenya, Tanzania, Uganda, South Sudan, and Ethiopia).
His leadership represents the commitment of Ethiopian editors to advancing the region's media landscape and promoting cross-border solidarity.
EGE reaffirms its full support for the EAES under Fitihawok’s leadership. We are confident that through this role, EGE will help set a new tone for the region - one marked by collaboration, integrity, and a shared pursuit of excellence.

በኢቢኤስ ቲቪ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አማን ፍስሃጽዮን ሞት የኢትዮጵያ አርታኢያን ማህበር እጅግ አዝኗል! የኢትዮጵያ ትልቁን ነፃ የቴሌቪዥን ስርጭት በመገንባት ረገድ አቶ አማን የነበራቸው ሚ...
11/02/2026

በኢቢኤስ ቲቪ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አማን ፍስሃጽዮን ሞት የኢትዮጵያ አርታኢያን ማህበር እጅግ አዝኗል! የኢትዮጵያ ትልቁን ነፃ የቴሌቪዥን ስርጭት በመገንባት ረገድ አቶ አማን የነበራቸው ሚና በኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙሃን ታሪክ ውስጥ ተሰንዶ የሚቀመጥ ሲሆን ፤ የኢትዮጵያ አርታኢያን ማህበር ለቤተሰቦቹ ፣ ለጓደኞቹ ፣ እና ለኢቢኤስ ቲቪ ባልደረቦች በሙሉ መፅናናትን ይመኛል።
ታላቅ ሰው በማጣታችን ብናዝንም ፣ የአማን የልፋት ውጤት የሆነው ኢቢኤስ ቲቪ ነፃንቱን ጠብቆ እንደሚዘልቅ ጥርጥር የለንም።

Editors' Guild of Ethiopia is deeply saddened by the shocking loss of Aman Fissehatsion - CEO of EBS TV. His pioneering role in building Ethiopia’s largest independent broadcaster cemented his place in the Ethiopian media history. We extend our heartfelt condolences to his family, friends, and the EBS team. Though we mourn a giant, Aman’s enduring legacy will continue to inspire.

ህብረት ለጋዜጠኞች ደህንነት በኢትዮጵያ በይፋ ተመረቀአዲስ አበባ፡ የተለያዩ የጋዜጠኞች ማኅበራት በጋራ በመሰባሰብ ያቋቋሙት ህብረት ለጋዜጠኞች ደህንነት በኢትዮጵያ  በዚህ ሳምንት በኤሊሊ ኢን...
24/01/2026

ህብረት ለጋዜጠኞች ደህንነት በኢትዮጵያ በይፋ ተመረቀ
አዲስ አበባ፡ የተለያዩ የጋዜጠኞች ማኅበራት በጋራ በመሰባሰብ ያቋቋሙት ህብረት ለጋዜጠኞች ደህንነት በኢትዮጵያ በዚህ ሳምንት በኤሊሊ ኢንተርናሽናል ሆቴል ስራውን በይፋ ጀምሯል። የህብረቱ ምርቃት የመክፈቻውን ጠቅላላ ጉባኤ ተከትሎ የተከናወነ ሲሆን ፣ በቀጣይነትም የጋዜጠኞችን ደህንነት ለመጠበቅ እና በመላ ሀገሪቱ የፕሬስ ነፃነትን ለማስፈን ዓላማ ሰንቆ እንደሚንቀሳቀስ ይጠበቃል።
በጋዜጠኛ የሽዋ ማስረሻ ሰብሳቢነት የሚመራው ጠቅላላ ጉባኤው የአባልነት ጥያቄዎችን ገምግሞ የሶስት ማህበራትን የአባልነት ጥያቄ በማፅደቅ የጥምረቱን ውክልና ለማስፋት ወሳኝ እርምጃ ወስዷል። በዚህም የአማራ ጋዜጠኞች ማህበር፣ የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኛ ጋዜጠኞች ማህበር እና የኦሮሚያ ጋዜጠኞች ማህበር ህብረቱን ተቀላቅለዋል።
ሰብሳቢዋ የጉባኤውን ስኬታማነት ሲገልፁ ፣ “ይህ ስብሰባ በኢትዮጵያ ላሉ ሁሉም የሚዲያ ባለሙያዎች ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ያደረግነውን የጋራ ውሳኔ ያጠናክራል።” አባላቱንም በህብረት እና የተቀናጀ ስልታዊ መንገድ ለመጓዝ ላደረጉት ከፍተኛ ተሳትፎ አመስግነዋል።
በርካታ የሲቪክ ማህበራት፣ የሚዲያ ተወካዮች፣ አጋር ተቋማት፣ ምሁራን እና ባለድርሻ አካላት በተገኙበት የህብረቱ የምርቃት ፕሮግራም በድምቀት የተከናወነ ሲሆን ፤ የህብረቱ አባላት እስካሁን በነበረው ሂደቱት የኢትዮጵያ አርታኢያን ማህበር የተጫወተውን ሚና በጋራ አመስግነው ከ IMS በኩል ለተደረገውም ድጋፍ አድናቆታቸውን ሰንዝረዋል።
የዚህ ዓይነቱ ህብረት አስፈላጊነት በተሰብሳቢዎች አጽንዖት ተሰጥቶታል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነት ትምህርት ቤት ረዳት ፕሮፌሰር የሆኑት አብዲሳ ዘርአይ የምስረታውን አስፈላጊነት ላይ ትኩረት በማድረግ "በመላው ኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን ለመጠበቅ የሚደረገውን ልዩ ልዩ ጥረቶች ለማጠናከር እና የስራ ድግግሞሽን ለማስወገድ ፤ በተለይም ዓለም አቀፋዊ የሚዲያ ሥነ-ምህዳር ከፍተኛ አደጋዎች በተጋረጠበት በዚህ ወቅት ፤ እና የተቀናጀ ብሔራዊ ምላሽ ለመስጠት የዚህ ህብረት መመስረት በጣም ወሳኝ ነው።"
የህብረቱ ምርቃት የተከናወነው ፣ የጋዜጠኞችን ደህንነት ለመጠበቅ ያለመ እና ትኩረቱንም በግጭት ቀጠናዎች በሚሰሩ ጋጋዜጠኞች ላይ ያተኮረ የሁለት ቀናት የአሰልጣኞች ስልጠና ፕሮግራም በተሳካ ሁኔታ መፈጸሙን ተከትሎ ነው። ስልጠናው በኢትዮጵያ አርታኢያን ማህበር የተዘጋጀ ሲሆን ፣ በ IMS ፣ FCDO እና NORAD ድጋፍ ጋር የተተገበረ ነው። ስልጠናው የጋዜጠኞችን የአካል፣የህግ፣ዲጂታል እና አእምሯዊ ደህንነትን በተመለከተ አቅም ግንባታ ፣ ጥበቃ እና አፋጣኝ ምላሽ መስጠት የሚያስችሉ መመሪያዎች በአማርኛ ፣ በኦሮሚኛ እና በእንግሊዝኛ ታትመው የተሰራጩበት ነበር።
ህብረቱ በቀጣይ ባለው መደበኛ ስራው፣ በመላው ኢትዮጵያ የጋዜጠኞችን ደህንነት እና ሙያዊ ታማኝነትን በማስተዋወቅ የጥብቅና፣ ድጋፍ እና ስትራቴጂ ማእከላዊ አስተባባሪ እንደሚሆን ይጠበቃል።

https://youtu.be/WE-6tFeelQ8?si=I8aGxoFowRhvjbzu
16/12/2025

https://youtu.be/WE-6tFeelQ8?si=I8aGxoFowRhvjbzu

የኢትዮጵያ አርታኢያን ማህበር በሴት ጋዜጠኞች ላይ የሚደርሰውን በቴክኖሎጂ የተደገፈ ፆታዊ ጥቃት በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ያደረገው ውይይት ...

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Editors Guild of Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Editors Guild of Ethiopia:

Share