19/08/2025
በፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት በክረምት በከፊል የሚሰጡ የዳኝነት አገልግሎቶች
የፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/13 አንቀጽ 38 ንኡስ አንቀጽ 3 መሰረት ከመደበኛ የፍርድ ቤት የስራ ጊዜ ውጭ አስቸኳይ ጉዳዮች እንደሚስተናገዱ ይገልጻል፡፡
በዚህም መሰረት መሰረታዊ የመብት ጥሰት የሚያስከትሉ በባህሪያቸው ጊዜ የማይሰጡ መደበኛ የፍርድ ቤቱ የስራ ጊዜ እስኪጀመር አፋጣኝነታቸው ታይቶ ዉሳኔ ካልተሰጠባቸው የመብት መጣስን ሊያስከትል የሚችሉ እና ሊካስ የማይችል ጉዳት ሊያስከትሉ የሚችሉ ጉዳዮችን አይቶ መወሰን አስፈላጊ በመሆኑ ፍርድ ቤቶች በከፊል ዝግ በሚሆኑባቸው ጊዜ ማለትም ከነሃሴ 01 ቀን እስከ መስከረም 30 ቀን ባለው ጊዜ ውስጥ በተረኛ ችሎት በወንጀል እና በፍታብሄር ጉዳዮች መደበኛ የፍርድ ቤት የስራ ጊዜን የማይጠብቁ ጉዳዮች አስቸኳይ ጉዳዮች ሲቀርቡ የሚታዩ ይሆናል በዚሁ መሰረት፡-
በፍታብሄር ከሚቀርቡ ጉዳዮች ፡-
➢ አስቸኳይ የእግድ አቤቱታዎች
➢ የልጅ ቀለብ
➢ አካል ነጻ ለማውጣት ላይ የሚቀርቡ አቤቱታዎች
➢ እንቅስቃሴን ገዳቢ በሆኑ ጉዳዮች ላይ የሚቀርቡ አቤቱታዎች
➢ ሰራተኞች በአሰሪዎቻቸው ላይ የሚያቀርቡት የደመወዝ ክፍያ የሚመለከቱ አፈጻጸም ጉዳዮች
➢ ከግልግል ዳኝነት ትዕዛዞች ጋር ተያይዞ አስቸኳይ የማህተም አገልግሎት ጥያቄዎች (ለእግድ, መጥሪያ ለማድረስ..)
➢ አንገብጋቢ እና ጊዜ የማይሰጡ መደበኛ የፍርድ ቤቱን የስራ ጊዜ መጠበቅ የማይችሉ በተረኛ ችሎቱ ዳኛ የሚወሰኑ ሌሎች የፍታብሄር ጉዳዮች
በወንጀል ከሚቀርቡ ጉዳዮች፡-
➢ ዋስትና
➢ አመክሮ
➢ አርቲዲ (እስረኛ ያለባቸው የሚቀርቡ የወንጀል መዛግብት )
➢ በተሰብሮ የሚቀርቡ አቤቱታዎች
➢ ጊዜ ቀጠሮ(አራዳ ምድብ ችሎት)
➢ ለመሰየም የሚቀርብ አቤቱታ
➢ እስረኛ ያለባቸው መዝገቦች
➢ አንገብጋቢ እና ጊዜ የማይሰጡ መደበኛ የፍርድ ቤቱን የስራ ጊዜ መጠበቅ የማይችሉ በተረኛ ችሎቱ ዳኛ የሚወሰኑ ሌሎች የወንጀል ጉዳዮች
ባጠቃላይ ፍርድ ቤቶች በከፊል ዝግ በሚሆንባቸው ጊዜያት መደበኛ የፍርድ ቤቱን የስራ ጊዜ የማይጠብቁ ጊዜ የማይሰጡ እና አጣዳፊ የሆኑ የወንጀል እና የፍታብሄር ጉዳዮች በተረኛ ችሎት የሚስተናገዱ መሆኑን በማረጋገጥ ሁሉም የፍርድ ቤቱ ማህበረሰብ እንዲሁም ተገልጋዩ የራሱን አስተዋጽኦ እንዲወጣ እናሳውቃለን፡፡