OCCA - Oromia Construction Contractors Association

OCCA - Oromia Construction Contractors Association The Oromia Construction Contractors Association (OCCA) was legally established in 2012 by 88 members.

By now it has more than 300 members.
- It is non-profitable association ruled by board.

23/08/2024
Kaampanoota foramii konistiraakshiniif ispoonsara ta'anii fi warraa harka qalleeyyiif mana jireenyaa tola ooltummaan ija...
01/02/2024

Kaampanoota foramii konistiraakshiniif ispoonsara ta'anii fi warraa harka qalleeyyiif mana jireenyaa tola ooltummaan ijaaraniif sagantaa galateeffannaa fi beekkamtii kennuu hoteela Ililliitti Abbaa Taayitaa konstiraakshinii Oromiyaa fi Waldaa Kontiraaktaroota Konistraaksshinii Oromiyaatiin gaggeefame.

01/02/2024

Kaampanoota foramii konistiraakshiniif ispoonsara ta'anii fi warraa harka qalleeyyiif mana jireenyaa tola ooltummaan ijaaraniif sagantaa galateeffannaa fi beekkamtii kennuu hoteela Ililliitti Abbaa Taayitaa konstiraakshinii Oromiyaa fi Waldaa Kontiraaktaroota Konistraaksshinii Oromiyaatiin gaggeefame.

01/02/2024
በአዲስ አበባ በቀላል ባቡር እና ቀለበት መንገዶች 30 የእግረኛ ማቋረጫ ተሻጋሪ ድልድዮችና መተላለፊያዎች ሊገነቡ መሆኑን የአዲስ አበባ መንገዶች ባለሥልጣን አስታውቋል።በአዲስ አበባ ቀላል ባ...
09/01/2024

በአዲስ አበባ በቀላል ባቡር እና ቀለበት መንገዶች 30 የእግረኛ ማቋረጫ ተሻጋሪ ድልድዮችና መተላለፊያዎች ሊገነቡ መሆኑን የአዲስ አበባ መንገዶች ባለሥልጣን አስታውቋል።

በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር በሚያልፍባቸውና ውስጠኛው ቀለበት መንገድ ተብለው በሚጠሩ ቦታዎች ላይ መሸጋገሪያ ድልድዮችና መተላለፊያዎች ባለመኖራቸው እግረኞች ለትራፊክ አደጋ እየተጋለጡና መንገድ ለማቋረጥ ረዥም ርቀት ለመጓዝ እንደሚገደዱ ባለስልጣን መ/ቤቱ ገልጿል።

በመሆኑም ፤ 30 የእግረኛ ማቋረጫ ተሻጋሪ ድልድዮችና መተላለፊያዎች እንደሚገነቡ ይፋ አድርጓል።

ተሻጋሪ ድልድዮቹና መተላለፊያ መስመሮቹ ከመሬት በላይ እንዲሁም በመሬት ውስጥ እንደሚገነቡ ጠቁሟል።

የእግረኛ ተሻጋሪ ድልድዮቹ ፦
- ሐና ማርያም፣
- ኃይሌ ጋርመንት፣
- ሳሪስ ሐኪም ማሞ ሰፈር፣
- አደይ አበባ፣
- ጉርድ ሾላ፣
- አውቶቡስ ተራና አብነት አካባቢ እንዲሁም በሌሎችም አካባቢዎች ነው የሚገነቡት ብሏል።

ኢዜአ

የደህንነት ሄልሜቶች በቀለማት ሲለዩ▪️ነጭ ሄልሜት፦ ለኢንጂነሮች፣ ለማናጀሮች፣ ለፎርማኖች፣ ለሱፐርቫይዘሮች▪️ሰማያዊ ሄልሜት፦ ለኤሌክትሪሺያኖች ለአናፂዎችና ለቴክኒክ ሠራተኞች▪️ቀይ ሄልሜት፦...
28/12/2023

የደህንነት ሄልሜቶች በቀለማት ሲለዩ

▪️ነጭ ሄልሜት፦ ለኢንጂነሮች፣ ለማናጀሮች፣ ለፎርማኖች፣ ለሱፐርቫይዘሮች
▪️ሰማያዊ ሄልሜት፦ ለኤሌክትሪሺያኖች ለአናፂዎችና ለቴክኒክ ሠራተኞች
▪️ቀይ ሄልሜት፦ ለእሳት አደጋ ሠራተኞች
▪️አረንጓዴ ሄልሜት፦ ለሴፍቲ ሠራተኞች
▪️ግሬይ ሄልሜት፦ ለሳይት ጎብኚዎች
▪️ቢጫ ሄልሜት፦ ለጉልበት እና ለግንባታ ማሽን ኦፕሬተር ሠራተኞች
▪️ ብራዎን ሄልሜት፦ ለበያጆችና ከፍተኛ ሙቀት ባለበት ቦታ ለሚሰሩ ሠራተኞች

ሠራተኞች በሥራ ወቅት በደህንነት ጉድለት ምክንያት የተለያዩ አደጋዎች እና ጉዳቶች ሲያጋጥሟቸው ይሰተዋላል፡፡ ይህንንም ችግር ለመቀነስ የተለያዩ የሕግ፣ የህብረተሰብ ጤና እና ማህበራዊ ግንዝቤ ሥራዎች ሲሞከሩ ይታያል፡፡

በተለይም እኤአ ከ1919 ዓ.ም ጀምሮ የዓለም አቀፉ የሥራ ድርጅት (International Labour Organization/ILO) መቋቋምን ተከትሎ በርካታ ከሠራተኛ የሥራ ደህንነት ጋር የተያያዙ መርሆዎች እያደገ መምጣቱ አይዘነጋም፡፡

ይህንንም ተከተሎ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተ.መ.ድ) ጠቅላላ ጉባዔ እኤአ በ1948 ዓ.ም ባወጣው ሁሉን አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች መግለጫ (Universal Declaration of Human Rights-UDHR) የሥራ ላይ ደህንነት አንዱ የሠራተኞች መብት እነደሆነ ደንግጓል፡፡

የግንባታ ሥራ በራሱ እጅግ ውስብስብ ከመሆኑ ባሻገር በርካታ ሥራዎች በጉልበት የሚከናወኑ (labour intensive) በመሆናቸው ብሎም ከሥራው ባህሪ አንጻር ፈረጅ ብዙ የሥራ ክንውን የሚካሄድበት ስለሆነ በደህንነት ጉደለት ምክንያት በርካታ አደጋ እና ስጋት ሲያጋጥም ይሰታዋላል፡፡

እንደ ዓለም አቀፉ የሥራ ድርጅት (ILO) ሪፖርት ከሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በየአመቱ በግንባታ ወቅት ቢያንስ 60ሺ ሠራተኞች ከደህንነት ጉደለት ጋር በተያየዘ ለሞት የሚዳረጉና ከባድ የአካል ጉዳት አደጋዎች እንዳሚያጋጥማቸው ጠቁሟል፡፡ ይህም ማለት በየአስር ደቂቃው ውስጥ አንድ ከባድ አደጋ ይደርሳል እንደ ማለት ነው፡፡ ሪፖርቱም በተለይ ከአጠቃላይ የሥራ ላይ አደጋዎች ውስጥ 17 ፐርሰንት ይህም ከስድስት አደጋዎች ውስጥ አንዱ የሚሆነው ገዳይ አደጋ በግንባታ ዘርፍ እንደሆነ ያትታል፡፡

የግንባታ ደህንነት ሲባል አንድ የግንባታ ፕሮጀክት ከጥንስሱ እስከ ፍጻሜው ድረስ በሚካሄዱ መጠነ ሰፊ የግንባታ እንቅስቃሴዎች ውስጥ ሊደረጉ የሚገባቸው እንዲሁም ሊወሰዱ የሚችሉ ጥንቃቄዎች የሚይዝ አሰራር ነው፡፡

የግንባታ ደህንነትን በተመለከተም በ2005 ዓ.ም የወጣው የኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ፖሊሲ፣ የኮንስትራክሽን ሥራ ደህንነት ጉዳይ ከኢንዱስትሪው ዕድገት ጋር ተያይዞ በትይዩ ትኩረት የሚሠጠው ቁልፍ ስራ መሆን እንዳለበት ይናገራል፡፡ በፈጻሚ አካላት የሚስተዋለው በፕሮጀክት ሳይቶች የሥራ አካባቢ ደህንነት ፖሊሲ ስርዓት እንዲኖር ለማድረግ የሚወጣው ወጪና የሚመደበው ጊዜ እንደተጨማሪ ወጪ አድርጐ የመመልከት እሳቤ በመሠረታዊነት መቀየር እንዳለበትና ለስራ አካባቢ ሰራተኞች ጤንነትና ደህንነት ጥበቃ የሚወጣ ወጪ የግንባታ ወጪ በመሆኑ ትርፍ እንዳልሆነ አጥብቆ ያሳስባል፡፡

በኮንስትራክሽን ሥራ አካባቢዎች መደረግ የሚገባቸው ጥንቃቄዎች ባለመወሰዳቸው ምክንያት የሚደርሱ ከቀላል እስከ ከባድ የንብረትና ህይወት መጥፋት ጉዳቶች መከላከል ያሻል፡፡ እነዚን የመሰሉ አደጋዎች ለመከላለል የሚያስችል በግንባታ ሂደት መወሰድ ስለሚገባው ጥንቃቄ በቂ ስልጠናና አፈጻጸሙን መከታተል የዋናው ሥራ አካል ተደርጎ መፈጸም ይኖርበታል፡፡

የኮንስትራክሽን አካባቢ ደህንነት (Construction Site safety) የግንባታ ሂደቱ ጥራት፣ ቅልጥፍና እና ውጤታማነት መረጋገጥ ወሳኝ እርምጃ ተደርጐ መወሰድ ይኖርበታል፡፡ ስለዚህ በሀገራችን የኮንስትራክሽን ሥራ እንቅስቃሴ ደህንነት ማስፈን ፖሊሲው አጉልቶ ያስቀመጠበትን ሁኔታ መገንዘብ ጠቃሚ ነው፡፡

INVITATION FOR BID (REBID)Procurement Reference number: RE-BID/AAWSA/WSIDD/GOV/NCB/W007/20231. The A.A. Water and Sewera...
18/12/2023

INVITATION FOR BID (REBID)
Procurement Reference number: RE-BID/AAWSA/WSIDD/GOV/NCB/W007/2023

1. The A.A. Water and Sewerage Authority- Water and Sanitation Infrastructure Development Division invites sealed bid from eligible bidders for Construction of Electro-Mechanical Workshop.

2. The Invitation is open for contractors under category of BC3/GC4 and above in Construction work license (2016 E. C).

3. Bidding will be conducted through the National Competitive Bidding (NCB) contained in the public procurement proclamation of the Government of the Federal Democratic Republic of Ethiopia.

4. Interested eligible bidders may obtain further information from Procurement Department of the division and inspect the bidding documents at the address given below during working hours from 8:30 AM-12:30 PM in the morning and 1:30 PM to 5:30 PM in the afternoon.

5. A complete set of Bidding Documents in English language may be purchased by interested bidders from December 18, 2023 onwards during office hours at the address below upon payment of a nonrefundable fee of birr 1000.00 (One thousand Birr). The method of payment will be in cash.

6. Bid is two envelop bid and must be delivered with one original and two copies of technical and financial proposal in separate envelopes to the address given below at or before January 10, 2024 at 2: 00pm.

7. The bid shall be valid for the period of ninety (90) days and shall be accompanied by a Bid Security of ETB 500,000.00 (birr five hundred thousand only) in the form of unconditional Bank Guarantee or CPO (which should be valid for 120 calendar days starting from the date of bid opening). Late bids shall be rejected.

8. Bids will be opened in the presence of the bidders' representatives who choose to attend at the address below on January 10, 2024, at 2:30pm.

9. The A.A.W.S.A Water and Sanitation Infra-structure Development Division reserves the right to reject any or all of the bids.

The address referred to the above is:

A.A. Water and Sewerage Authority: Water and Sanitation Infrastructure Development Division, Lideta sub- city Woreda 08 around condominium houses on the left side of Lideta Menafesha. Tel. 0115579036 Attention Mrs. Mestawot Abebe, Procurement Support Process Head, Email Address: [email protected]

A.A.W.S.A Water and Sanitation Infrastructure Development Division

15/12/2023

በፕሮጀክቶች ላይ ለሚፈጠሩ አለመግባባቶች አማራጭ የግጭት አፈታት አገልግሎትን ያግኙ

🚧 “በብዙ የማህበራዊና የተፈጥሮ ሳይንስ ዘርፎች አለመግባባት ተፈጥሮአዊ መሆኑ ተደጋግሞ የተገለፅ እውነታ ነው፡፡ በህግ ወይንም በውል የተገለፁ መብቶች ያለመከበር እና የይገባኛል ጥያቄዎች ለእነዚህ አለመግባባቶች መፈጠር መሰረታዊ ምክንያት ናቸው፡፡ መሰል ይገባኛል ጥያቄዎችን በአግባቡ መፈታት ያልተቻለ እንደሆነ ጉዳዩ ወደ አለመግባባት ደረጃ የማደግ እድሉ ሰፊ ነው፡፡ ስለሆነም ያለመግባባቶች ከፍ ወዳለ ደረጃ ከማደጋቸውና ለፕሮጀክቶች አፈጻጸም እንቅፋት ከመሆናቸው በፊት መታረም መቻላቸው አስፈላጊ ነው፡፡

ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ በተያዘላቸው በጀት ለማጠናቀቅ ይቻል ዘንድ የተለያዩ የግጭት አፈታት ዘዴዎችን ተጠቅሞ ያጋጠሙ አለመግባባቶችን መፍታት አሁን አሁን ይበልጥ እየታመነበት የመጣ ጉዳይ ሆኗል፡፡ የግንባታ ዘርፉም ከግጭቶች/ ካለመግባባቶች የፀዳ ባለመሆኑ በተመሳሳይ ዕይታ የሚታይ እና መፈታት ያለበት ጉዳይ ነው፡፡

የግንባታ ሂደት በውስጡ ከሚሳተፉ ባለድርሻዎች፣ ከሚፈስበት መዋዕለ ነዋይ እንዲሁም ከሚወስደው ጊዜ ውስብስብነት ወዘተ አንፃር አለመግባባት መፈጠሩ የሚጠበቅ ነው፡፡ በግንባታ ሂደቶች ውስጥ የሚያጋጥሙ አለመግባባቶችን መፍታት ፈርጀ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው የዘርፉ ባለሙያዎች በስፋት ይገልጻሉ፡፡

ስለሆነም ግጭቶች/ አለመግባባቶች/ ወደ ፍርድ ቤት ከመሄዳቸው በፊት አማራጭ የግጭት አፈታት ዘዴዎችን በመጠቀም ሊያጋጥሙ የሚችሉ አለመግባባቶችን መፍታት በተከራካሪ ወገኖች መካከል መልካም ግንኙነትን ከማስቀጠል አኳያ፣ ከህግ ሙያ ውጪ ያሉ ሌሎች ባለሙያዎችን ከማሳተፍ በተጨማሪ ጊዜን፣ ወጪን እና በዳኝነት ተቋማት ላይ የሚፈጥረውን ጫና የሚቀንስ በመሆኑ ይህ አሰራር በግንባታ ዙሪያ የሚኖረው ጠቀሜታ የጎላ ነው፡፡

የሚኒስትሮች ምክር ቤት የፌዴራል መንግስት አስፈጻሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር ለመወሰን በወጣው አዋጅ 1263/2014 የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን የተቋቋመ እና ስልጣኑንና ተግባሩንም ለመወሰን እንደዚሁ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 524/2015 መሰረት አድርጎ መቋቋሙ ይታወቃል፡፡

ይህን መነሻ በማድረግ በኢትዮጵያ የዳኝነት እና የዕርቅ አሰራር ስርዓት አዋጅ ቁጥር 1237/2013ን መሠረት በማድረግ እና በደንብ ቁጥር 524/2015 አንቀጽ 5 (16) የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን በመንግስት ኮንስትራክሽን ስራዎች ለሚፈጠሩ የውል አለመግባባቶች በሚዘረጋው አሰራር ስርዓት ፕሮጀክቶች/ ተዋዋዮች በአማራጭ የግጭት መፍቻ ዘዴዎች መፍትሄ እንዲያገኙ የማድረግ ስልጣንና ተግባር ተሰጥቶታል፡፡

በዚህም መነሻነት፣ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን በመንግስት ኮንስትራክሽን ስራዎች ለሚፈጠሩ የውል አለመግባባቶች በዘረጋው የአሰራር ስርዓት በአማራጭ የግጭት መፍቻ ዘዴዎች መፍትሄ እንዲያገኙ እየሰራ መሆኑን እየገለፅን ማንኛውም የህንጻና የመሠረት-ልማት ፕሮጀክቶችን የሚያስገነቡ እና እያስገነቡ ያሉ የመንግስት አስፈጻሚ ተቋማት እና የሚመለከታቸው የባለድርሻ አካላት በመደበኛ ፍርድ ቤት የሚሰጡ አገልግሎቶች እንደተጠበቀ ሆኖ፤ አለመግባባቶችን በአማራጭ የግጭት አፈታት ዘዴዎች መፍታት የሚፈልጉ የመንግስት ተቋማት ወይም ግጭቶችን በአማራጭ የሙግት መፍቻ ዘዴዎች ለመፍታት የህግ ስልጣን ያላቸው ተቋማት አገልግሎቱን ከባለስልጣን መ/ቤቱ ማግኘት የሚችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን

በሶስት ሲሚንቶ ፋብሪካዎች ላይ እርምጃ ተወሰደበኦሮሚያ ክልል ሶስት የሲሚንቶ አምራች ኢንዱስትሪዎች ላይ የጥራት ችግር በመኖሩ ምክንያት እርምጃ መወሰዱ ተገልጿል፡፡በኦሮሚያ ክልል ከሚገኙ የሲ...
15/12/2023

በሶስት ሲሚንቶ ፋብሪካዎች ላይ እርምጃ ተወሰደ

በኦሮሚያ ክልል ሶስት የሲሚንቶ አምራች ኢንዱስትሪዎች ላይ የጥራት ችግር በመኖሩ ምክንያት እርምጃ መወሰዱ ተገልጿል፡፡

በኦሮሚያ ክልል ከሚገኙ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ወስጥ በጥራት ችግር ምክንያት ባለፉት ሶስት ወራት ውስጥ ሶስት ፋብሪካዎች ላይ አስተተዳደራዊ እርምጃ ወስደናል ሲሉ የኦሮሚያ ንግድ ቢሮ የኢንዱስትሪ ገበያ ቁጥጥር ቡድን መሪ አቶ ታጁ መሀመድ አስታውቀዋል፡፡

የምርት ሰርተፍኬት በመሰረዝ የማምረት ስራ እንዲያቆሙ ተደርጓል ያሉት ሀላፊው ሁለቱ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች እስከ ሶስት ወር ድረስ በመቆየት የጥራት ማስተካከያ አድርገው ወደ ማምረት ስራው ሊመለሱ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
የተቀረው አንደኛው ፋብሪካ ግን ወደ ስራ እናዳልገባ እና ማምረት እንዳልጀመረ ነው የገለፁት፡፡

አሁን ላይም የሲሚንቶ ዋጋ በገበያ ላይ ቅናሽ ማሳየተኑን እና የአቅርቦት ፍላጎት መጨመር እያሳየ ነው ሲሉ የገለፁትን መዘገባችን የሚታወስ ነው ፡፡

Via አሐሬ

ባዮቴክኖሎጂ በኮንስትራክሽን ኢንደስትሪ  ውስጥ ጥቅም ላይ ሊውል ነው__▪️በኢትዮጵያ  የኮንስትራክሽን ኢንደስትሪ  ውስጥ ባዮቴክኖሎጂን ለመጠቀም የሚካሄደው ጥናት ውጤት እያሳየ ነው።የኮንስት...
13/12/2023

ባዮቴክኖሎጂ በኮንስትራክሽን ኢንደስትሪ ውስጥ ጥቅም ላይ ሊውል ነው
__▪️
በኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ኢንደስትሪ ውስጥ ባዮቴክኖሎጂን ለመጠቀም የሚካሄደው ጥናት ውጤት እያሳየ ነው።

የኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት
ከአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ (ASTU) ጋር በቅንጅት እየሠራ ያለውን የባዮቴክኖሎጂ የምርምር ሥራ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል መድረክ በዩኒቨርስቲው ማዕከል አካሂዷል፡፡

የጥናትና የምርምር ሥራው የሚካሄደው ስነ- ህይወትን ( ባክቴሪያን) መሠረት ባደረገ ባዮቴክኖሎጂ የግንባታ ግብአቶችን ለማምረት እንዲሁም የመሰነጣጠቅ ችግር የሆነውን የግንባታ ፈተና ለማዳን እና ለማስወገድ ነው፡፡

ጥናቱ የሚካሄደው በዩኒቨርስቲው በተዋቀረ የጥናት ቡድን አማካኝነት ሲሆን፣ ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት ለጥናቱ በጀት መድቦ ውጤቱን እየተከታተለ ይገኛል፡፡

ጥናቱ እየተካሄደ ያለው Microbial Bio-cement, Bio- blocks, Bio- enzyme and Brick -making machine በሚሉ አራት ጉዳዮች ላይ ነው፡፡

በጉዳዮቹ ላይ የጥናት ቡድኑ አባላት ዶ/ር መስፍን ታፈሰ፣ አቶ ዳንኤል ሙሉ እንዲሁም ዶ/ር ኃይሉ ሽመልስ ዝርዝር ገለፃ አቅርበዋል፡፡

የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ታምራት ሙሉ ስሜ እንደተናገሩት፣ አማራጭ የግንባታ ግብአቶችን ለማግኘት የሚያስችሉ ጥናትና ምርምሮችን ማካሄድ፣ ቴክኖሎጂዎችን ማሸጋገር፣ የፈጠራ ሥራዎችን መደገፍና ማበረታታት የኢንስቲትዩቱ ስልጣን እና ተግባር በመሆኑ በእነዚህ ሥራዎች ዙሪያ በትኩረት እየሠራ ይገኛል ብለዋል፡፡

ይህ በASTU በኩል የሚካሄደው የባዮቴክኖሎጂ ጥናት እጅግ ጠቃሚ እና አዋጭ እንደሆነም ዋና ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡

በመድረኩ ላይ የተገኙት በከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ሚንስትር ዲኤታ የሆኑት ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ፣ ጥናቱ ከሂደት ወጥቶ በቶሎ ተግባራዊ መሆን እንዳለበት ያሳሰቡ ሲሆን፣ በሁሉም ጥናት ውጤቶች ሠርቶ ማሳያ በቅርቡ ማየት እንደሚፈልጉም ተናግረዋል፡፡

የመድረኩ ተሳታፊዎች ይህ ባዮቴክኖሎጂ ላይ የሚደረገው ጥናት የሀገሪቱን የኮንስትራክሽን ችግር የሚፈታና ለዜጎች የሥራ እድል ፈጠራ፣ አቅምን ያገናዘበ መኖሪያ ቤት ለማግኘት እንደሚረዳም ተናግረዋል፡፡

ግንባታዎች ከተጠናቀቁ በኋላ በሚደርስባቸው መሰነጣጠቅና በሚፈጥሩት ክፍተት በቶሎ ስለማይጠገኑ በሀገር ላይ የሚያስከትሉት ኪሳራ ከፍተኛ መሆኑንም ገልፀዋል።

የASTU ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ደረጀ እንግዳ በበኩላቸው፣ የተሰጡ ጠቃሚ አስተያየቶችን በግብአትነት በመውሰድ ጥናቶቹን ተግባራዊ በማድረግ ሥራ ላይ ለማዋል የበለጠ በቁርጠኝነት እንደሚሰሩና የጥናቶቹን የምርምር ውጤቶች በቅርብ እንደሚያሳዩ ቃል ገብተዋል፡፡

በዕለቱ Brick- making machine እና በዚህ ማሽን በተመረተ ብሎኬት የሚሠራ ቤት የሚታይበት መስክ በተሳታፊዎቹ ተጎብኝቷል።

13/12/2023

በፕሮጀክቶች ላይ ለሚፈጠሩ አለመግባባቶች አማራጭ የግጭት አፈታት አገልግሎትን ያግኙ

“በብዙ የማህበራዊና የተፈጥሮ ሳይንስ ዘርፎች አለመግባባት ተፈጥሮአዊ መሆኑ ተደጋግሞ የተገለፅ እውነታ ነው፡፡ በህግ ወይንም በውል የተገለፁ መብቶች ያለመከበር እና የይገባኛል ጥያቄዎች ለእነዚህ አለመግባባቶች መፈጠር መሰረታዊ ምክንያት ናቸው፡፡ መሰል ይገባኛል ጥያቄዎችን በአግባቡ መፈታት ያልተቻለ እንደሆነ ጉዳዩ ወደ አለመግባባት ደረጃ የማደግ እድሉ ሰፊ ነው፡፡ ስለሆነም ያለመግባባቶች ከፍ ወዳለ ደረጃ ከማደጋቸውና ለፕሮጀክቶች አፈጻጸም እንቅፋት ከመሆናቸው በፊት መታረም መቻላቸው አስፈላጊ ነው፡፡

ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ በተያዘላቸው በጀት ለማጠናቀቅ ይቻል ዘንድ የተለያዩ የግጭት አፈታት ዘዴዎችን ተጠቅሞ ያጋጠሙ አለመግባባቶችን መፍታት አሁን አሁን ይበልጥ እየታመነበት የመጣ ጉዳይ ሆኗል፡፡ የግንባታ ዘርፉም ከግጭቶች/ ካለመግባባቶች የፀዳ ባለመሆኑ በተመሳሳይ ዕይታ የሚታይ እና መፈታት ያለበት ጉዳይ ነው፡፡

የግንባታ ሂደት በውስጡ ከሚሳተፉ ባለድርሻዎች፣ ከሚፈስበት መዋዕለ ነዋይ እንዲሁም ከሚወስደው ጊዜ ውስብስብነት ወዘተ አንፃር አለመግባባት መፈጠሩ የሚጠበቅ ነው፡፡ በግንባታ ሂደቶች ውስጥ የሚያጋጥሙ አለመግባባቶችን መፍታት ፈርጀ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው የዘርፉ ባለሙያዎች በስፋት ይገልጻሉ፡፡

ስለሆነም ግጭቶች/ አለመግባባቶች/ ወደ ፍርድ ቤት ከመሄዳቸው በፊት አማራጭ የግጭት አፈታት ዘዴዎችን በመጠቀም ሊያጋጥሙ የሚችሉ አለመግባባቶችን መፍታት በተከራካሪ ወገኖች መካከል መልካም ግንኙነትን ከማስቀጠል አኳያ፣ ከህግ ሙያ ውጪ ያሉ ሌሎች ባለሙያዎችን ከማሳተፍ በተጨማሪ ጊዜን፣ ወጪን እና በዳኝነት ተቋማት ላይ የሚፈጥረውን ጫና የሚቀንስ በመሆኑ ይህ አሰራር በግንባታ ዙሪያ የሚኖረው ጠቀሜታ የጎላ ነው፡፡

የሚኒስትሮች ምክር ቤት የፌዴራል መንግስት አስፈጻሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር ለመወሰን በወጣው አዋጅ 1263/2014 የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን የተቋቋመ እና ስልጣኑንና ተግባሩንም ለመወሰን እንደዚሁ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 524/2015 መሰረት አድርጎ መቋቋሙ ይታወቃል፡፡
ይህን መነሻ በማድረግ በኢትዮጵያ የዳኝነት እና የዕርቅ አሰራር ስርዓት አዋጅ ቁጥር 1237/2013ን መሠረት በማድረግ እና በደንብ ቁጥር 524/2015 አንቀጽ 5 (16) የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን በመንግስት ኮንስትራክሽን ስራዎች ለሚፈጠሩ የውል አለመግባባቶች በሚዘረጋው አሰራር ስርዓት ፕሮጀክቶች/ ተዋዋዮች በአማራጭ የግጭት መፍቻ ዘዴዎች መፍትሄ እንዲያገኙ የማድረግ ስልጣንና ተግባር ተሰጥቶታል፡፡

በዚህም መነሻነት፣ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን በመንግስት ኮንስትራክሽን ስራዎች ለሚፈጠሩ የውል አለመግባባቶች በዘረጋው የአሰራር ስርዓት በአማራጭ የግጭት መፍቻ ዘዴዎች መፍትሄ እንዲያገኙ እየሰራ መሆኑን እየገለፅን ማንኛውም የህንጻና የመሠረት-ልማት ፕሮጀክቶችን የሚያስገነቡ እና እያስገነቡ ያሉ የመንግስት አስፈጻሚ ተቋማት እና የሚመለከታቸው የባለድርሻ አካላት በመደበኛ ፍርድ ቤት የሚሰጡ አገልግሎቶች እንደተጠበቀ ሆኖ፤ አለመግባባቶችን በአማራጭ የግጭት አፈታት ዘዴዎች መፍታት የሚፈልጉ የመንግስት ተቋማት ወይም ግጭቶችን በአማራጭ የሙግት መፍቻ ዘዴዎች ለመፍታት የህግ ስልጣን ያላቸው ተቋማት አገልግሎቱን ከባለስልጣን መ/ቤቱ ማግኘት የሚችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

(የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን)

Address

Around Haile Garment Addis Ababa
Addis Ababa

Telephone

+2510118443038

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when OCCA - Oromia Construction Contractors Association posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to OCCA - Oromia Construction Contractors Association:

Share