26/04/2026
ሳውዲ አረቢያ ከኢራን ጋር የሚደረገውን ድርድር ለማስቀጠል ሲባል በአሜሪካ በኩል በእስራኤል እና ሊባኖስ መካከል የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረግ ግፊት ማድረጓ ተገለጸ
በሊባኖስ የተኩስ አቁም ከመታወጁ አንድ ቀን ቀደም ብሎ በትራምፕ እና በልዑል መሀመድ ቢን ሰልማን መካከል የግል ስልክ ንግግር ተካሂዷል።
ሳውዲ አረቢያ ከኢራን ጋር የሚደረገውን ንግግር ለማስቀጠል አሜሪካ በሊባኖስ የተኩስ አቁም ለማምጣት ቅድሚያ እንዲሰጥ ግፊት ማድረጓን በርካታ የአሜሪካ፣ የምዕራባውያን እና የአረብ ባለስልጣናት ለ“ሚድል ኢስት አይ” ገልጸዋል። ይህ የሆነው ግዛቱ የሆርሙዝ ስርጥን እንደገና ለማስከፈት ድርድር እየተደረገ ባለበት ወቅት ነው።
የሳውዲ አረቢያው አልጋ ወራሽ ልዑል መሀመድ ቢን ሰልማን ባለፈው ረቡዕ በነበረው የግል ስልክ ንግግር በሊባኖስ የተኩስ አቁም ማድረግ ስላለው አስፈላጊነት ለፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ያሳሰቡ ሲሆን፣ ትራምፕ ሐሙስ ዕለት ያወጁት የ10 ቀን የተኩስ አቁም በዚሁ የሳውዲ አረቢያ ግፊት የመጣ መሆኑ ተነግሯል።
ይሁን እንጂ እስራኤል ለስምምነቱ ተገዢ መሆኗ እና ትራምፕ በኔታንያሁ ላይ የሚኖራቸው የጫና መጠን እስካሁን ግልጽ አይደለም። በሌላ በኩል ሄዝቦላህ የሊባኖስ መንግስት ከእስራኤል ጋር ቀጥተኛ ንግግር በማድረጉ ተቃውሞውን ገልጿል።