03/06/2024
በውመን ኢን ማይስ ኢትዮጵያ እና በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ትብብር በወላይታ ዞን ኪንዶ ኮይሻ ወረዳ በሌ ሀዋሳ ከተማ በሴቶች ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ላይ አተኩሮ የተካሄደው የ ሴቶች እና ወጣቶች የክርክር እና የውይይት መድረክ በስከት ተጠናቋል። በመድረኩ ላይ የኪንዶ ኮይሻ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ስምኦን ሳፓን ጨምሮ የወላይታ ዞን ሴቶችና ህጻናት ጉዳይ መምሪያ የትምህርት ጽ/ቤት ፣ እንተርፕራይዝና ሥራ ዕድል ፈጠራ ጽ/ቤት፣ ሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ጽ/ቤት ኀላፊዎችና ተወካዮች እንዲሁም የስቭክ መምህር ተገኝተው ስለ ሴቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎ እና ተጠቃሚነትን በሚመለከት መልዕክት አስተላልፈዋል።
በዚህ የክርክር እና የውይይት መድረክ ላይ በሁለት ጎራ ተከፍለው ክርክር ያደረጉ ስምንት ተሳታፊዎች እያንዳንዳቸው ሦስት ሦስት ደቂቃዎች ተሰጥቷቸው ባቀረቡት የክርክርና የውይይት ሀሳብ በሴቶች ላይ ይደርሱ የነበሩ ጫናዎችን በሚመለከት ሴቶች በቂ ዕድል ያለማግኘታቸው በልማትና መልካም አስተዳደር ላይ የፈጠረውን ክፍተት፣ ሴቶች ወደ ውሳኔ ሰጪነት እንዳይመጡ ያደረጋቸው የማህበረሰቡ የተሳሳተ ግንዛቤ እና በአጠቃላይ ከአባባል ጀምሮ በለተ ዕለት ሕይወት ውስጥ ስተገበሩ የቆዩ የተዛነፉ አመለካከቶች በስፋት ተነስተው በጥልቀት ውይይት ተደርጎባቸዋል። በዚህም የውይይቱና የክርክር መድረኩ ላይ የታደሙ ተሳታፍዎች ሴቶች ከዚህ ቀደም ይደርስባቸው ከነበሩ ጫናዎች ተላቀው ከወንዶች እኩል ማህበራዊ ፣ እኮኖሚያዊ እና ፖሌቲካዊ ተሳታፍነታቸው እና ተጠቃሚነታቸው እንዲያድግ ሰበአዊና ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን በቂጡ እንዲያውቁ እና እንዲጠቀሙበት ብሎም የውሳኔ ሰጭነት አቅማቸው እንዲያድግ የሚያግዝ መሰል መድረክ በመዘጋጀቱ ደስተኞች መሆናቸውን እና ይህንኑ መድረክ ያመቻቹ አካላትን ውመን ኢን ማይስ ኢትዮጵያ እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድን አመስግነዋል።