17/06/2026
የጸሎትና የድጋፍ ጥሪ፡ የጌታን ሥራ በአንድነት እናስቀጥል!
ለእግዚአብሔር ክብር ይሁን! በክረምቱ ወቅት ለሚከናወነው የ5-ቀን ክለብ፣ ለቀጣዩ ዓመት የምስራች ክለብ መርሐ ግብር፣ እንዲሁም ለተለያዩ የልጆች አገልግሎቶች እና ለአዋቂዎች ስልጠና የሚውሉ የCEF መጻሕፍት ተዘጋጅተው ተጠናቀዋል።
እነዚህ መጻሕፍት የብዙ ልጆችን ሕይወት ለመለወጥ ወሳኝ መሣሪያዎች ናቸው።
ሆኖም፣ በአሁኑ ሰዓት አንድ ትልቅ ፈተና ገጥሞናል፡ እነዚህን መጻሕፍት የምናስቀምጥበት አስተማማኝ የማከማቻ ሥፍራ (Store) በማጣታችን፣ የጌታ ሥራ እንዳይዘገይ ስጋት ገብቶናል።
እንዴት መርዳት ይችላሉ?
🙏በጸሎት፦ የጌታ ሥራ በቦታ እጥረት እንዳይዘገይ፣ እግዚአብሔር ለሥራው የሚሆን ምቹ እና ደህንነቱ የተጠበቀ ሥፍራ እንዲሰጠን በጸሎት አስቡን።
🏠 በቦታ ድጋፍ፦ መጻሕፍቱን ለጊዜው የምናስቀምጥበት ባዶ ቦታ ማዘጋጀት የምትችሉ ወገኖች፣ እባክዎን በአስቸኳይ ደውለው ያሳውቁን።
🤝በአገልግሎት አጋርነት፦ ይህንን የአገልግሎት እገዛ ለማድረግ የሚፈልጉ ሁሉ በሩ ክፍት ነው።
ሥራው የጌታ ነው፤ እኛ ደግሞ ለዚህ አገልግሎት የተቀመጥን ባለአደራዎች ነን።
ይህንን የትውልድ ስራ አብረን እናስቀጥል!
ለበለጠ መረጃ እና ድጋፍ ለመስጠት፦
📞 +251 96 896 9798
"የጌታን ሥራ አብረን እናስቀጥል!"
https://t.me/cefethiopia
https://t.me/cefethiopia