Child Evangelism Fellowship Ethiopia

Child Evangelism Fellowship Ethiopia Mathew 18:14 Gospel for children
እያንዳንዱን ልጅ | በእያንዳንዱ ቀን | በሁሉም ቦታ
📍 ልጆች በወንጌል መድረስ።

የጸሎትና የድጋፍ ጥሪ፡ የጌታን ሥራ በአንድነት እናስቀጥል!ለእግዚአብሔር ክብር ይሁን! በክረምቱ ወቅት ለሚከናወነው የ5-ቀን ክለብ፣ ለቀጣዩ ዓመት የምስራች ክለብ መርሐ ግብር፣ እንዲሁም ለተ...
17/06/2026

የጸሎትና የድጋፍ ጥሪ፡ የጌታን ሥራ በአንድነት እናስቀጥል!

ለእግዚአብሔር ክብር ይሁን! በክረምቱ ወቅት ለሚከናወነው የ5-ቀን ክለብ፣ ለቀጣዩ ዓመት የምስራች ክለብ መርሐ ግብር፣ እንዲሁም ለተለያዩ የልጆች አገልግሎቶች እና ለአዋቂዎች ስልጠና የሚውሉ የCEF መጻሕፍት ተዘጋጅተው ተጠናቀዋል።

እነዚህ መጻሕፍት የብዙ ልጆችን ሕይወት ለመለወጥ ወሳኝ መሣሪያዎች ናቸው።
ሆኖም፣ በአሁኑ ሰዓት አንድ ትልቅ ፈተና ገጥሞናል፡ እነዚህን መጻሕፍት የምናስቀምጥበት አስተማማኝ የማከማቻ ሥፍራ (Store) በማጣታችን፣ የጌታ ሥራ እንዳይዘገይ ስጋት ገብቶናል።

እንዴት መርዳት ይችላሉ?
🙏በጸሎት፦ የጌታ ሥራ በቦታ እጥረት እንዳይዘገይ፣ እግዚአብሔር ለሥራው የሚሆን ምቹ እና ደህንነቱ የተጠበቀ ሥፍራ እንዲሰጠን በጸሎት አስቡን።
🏠 በቦታ ድጋፍ፦ መጻሕፍቱን ለጊዜው የምናስቀምጥበት ባዶ ቦታ ማዘጋጀት የምትችሉ ወገኖች፣ እባክዎን በአስቸኳይ ደውለው ያሳውቁን።
🤝በአገልግሎት አጋርነት፦ ይህንን የአገልግሎት እገዛ ለማድረግ የሚፈልጉ ሁሉ በሩ ክፍት ነው።
ሥራው የጌታ ነው፤ እኛ ደግሞ ለዚህ አገልግሎት የተቀመጥን ባለአደራዎች ነን።

ይህንን የትውልድ ስራ አብረን እናስቀጥል!
ለበለጠ መረጃ እና ድጋፍ ለመስጠት፦
📞 +251 96 896 9798
"የጌታን ሥራ አብረን እናስቀጥል!"

https://t.me/cefethiopia
https://t.me/cefethiopia

CYIA 2026 ቀኑ ደረሰ! 🌟ክርስቲያን ወጣት በተግባር ጊዜው ደርሷል! በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የCYIA 2026 የዝግጅት ዘመን ደጃፋችን ላይ ነው።ልጆችን ለማገልገል፣ ህይወታቸውን በወንጌ...
15/06/2026

CYIA 2026 ቀኑ ደረሰ! 🌟ክርስቲያን ወጣት በተግባር ጊዜው ደርሷል! በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የCYIA 2026 የዝግጅት ዘመን ደጃፋችን ላይ ነው።
ልጆችን ለማገልገል፣ ህይወታቸውን በወንጌል ለመቅረጽ እና ክህሎታችንን ለማዳበር የተዘጋጀንበት ልዩ ጊዜ ነው። ይህ ጉዞ ታላቅ ተልእኮን ያነገበ ነው ሁሉም ቤተክርስቲያና ከወጣቱና ከአገልግሎቱ ጎን በፀሎት ይቁም።
✅ ምን ይጠብቀናል?
ጥልቅ የሆነ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት
ውጤታማ የወንጌል ስርጭት ዘዴዎች
የማይረሱ የህብረት ጊዜያት
ለዚህ ታላቅ የልጆች አገልግሎት ሁሉም ወጣቶች ተመዝግበው ተዘጋጅተዋል ለበለጠ መረጃ ቴሌግራማችንን ይጎብኙ።
https://t.me/cefethiopia
https://t.me/cefethiopia

📖 የነገን ትውልድ ዛሬ በቃሉ እናንጽ!የልጆች አገልግሎት ውጤታማ የሚሆነው የልጆችን ልብ እና አይን በሚስብ መልኩ ሲቀርብ ነው። ሲኢ ኤፍ (CEF) ለሰንበት ትምህርት ቤቶች፤ ለትንንሽ ልጆች ...
11/06/2026

📖 የነገን ትውልድ ዛሬ በቃሉ እናንጽ!

የልጆች አገልግሎት ውጤታማ የሚሆነው የልጆችን ልብ እና አይን በሚስብ መልኩ ሲቀርብ ነው። ሲኢ ኤፍ (CEF) ለሰንበት ትምህርት ቤቶች፤ ለትንንሽ ልጆች መፅሐፍ፤ ለክረምት የሚሆኑ፤ ለመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርቶች፤ ለCYIA and 5day እና ለምስራች ቡድኖች የሚሆኑ ድንቅ የትምህርት ቁሳቁሶችን ያቀርባል።

🎨 የሲ ኢ ኤፍ (CEF) የትምህርት ቁሳቁሶች ልዩ የሚያደርጋቸው፦
• ባለቀለም ስዕላዊ መጽሐፍት (Flashcards): የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮችን በልጆች አእምሮ ውስጥ በቀላሉ እንዲሳሉ የሚያደርጉ ማራኪ ስዕላት።
• ለልጆች የወንጌል መመስከሪያ ስልቶች: እንደ "Wordless Book" (ቃል አልባ መጽሐፍ) ያሉ ወንጌልን በቀለማት ትርጉም ብቻ ለልጆች የሚያስረዱ ልዩ ዘዴዎች።

• የመምሪያ መጽሐፍት: ወይም (Manual)፦ ሰልጣኞች የሚሰለጥኑትን ስልጠና ደረጃ በደረጃ ዕውቀት የሚያገኙበት መፅሐፍ ነው።
• መዝሙሮች እና ጥቅሶች: ልጆች ቃሉን በዜማ እና በጨዋታ በቀላሉ እንዲያጠኑ የሚያግዙ ግብዓቶች።

🏠 ለምን አገልግሎት ይውላሉ?

1. ለሰንበት ትምህርት ቤት መምህራን: ትምህርቱን ግልጽ እና ሳቢ ለማድረግ።
2. ለወላጆች: በቤት ውስጥ ልጆቻቸውን በወንጌል እንዲደርሱና በክርስቲያናዊ ስነ-ምግባር ለማሳደግ። በተጨማሪም ደቀ መዝሙር ለማድረግ።
3. በየሰፈሩ እና በየመንደሩ ለሚደረጉ የልጆች የምስራች ጊዜ ፕሮግራሞች (Good News Club)።

Child Evangelism Fellowship Ethiopia 🇪🇹 🌟 ራዕያችን"እያንዳንዱን ልጅ በእያንዳንዱ ቀን በሁሉም ስፍራ!" በወንጌቁሳቁሶችን ለማግኘትና ለበለጠ መረጃ፦
Jon us Telegram
https://t.me/cefethiopia
https://t.me/cefethiopia

ተነሺ፥ አብሪ! የትውልድ ፀሎትና የሲኢ ኤፍ (CEF) አገልግሎት ጥሪ 🌟ኢሳይያስ 60:1“ብርሃንሽ መጥቶአልና፥ የእግዚአብሔርም ክብር ወጥቶልሻልና ተነሺ፥ አብሪ።”ይህ ቃል ዛሬ በብዙ ግራ መጋ...
03/06/2026

ተነሺ፥ አብሪ! የትውልድ ፀሎትና የሲኢ ኤፍ (CEF) አገልግሎት ጥሪ 🌟
ኢሳይያስ 60:1
“ብርሃንሽ መጥቶአልና፥ የእግዚአብሔርም ክብር ወጥቶልሻልና ተነሺ፥ አብሪ።”

ይህ ቃል ዛሬ በብዙ ግራ መጋባትና ጨለማ ውስጥ ለሚያድጉት ልጆችና አዳጊ ወጣቶች የተሰጠ ታላቅ መለኮታዊ ተልዕኮ ነው።
የትውልድ ፀሎት ማለት የነገዋን ቤተክርስቲያን ዛሬ በጉልበታችን የምንወልድበትና ልጆችን በክርስቶስ ብርሃን የምንጋርድበት መንፈሳዊ ጋሻ ነው!
ዶክተር ሳም ዶርቲ (Dr. Sam Doherty) እንዲህ ይላሉ፦

ይህ "ልጆችን በፀሎት መደገፍና ወደ ክርስቶስ መምራት የወደፊት ምርጫ ሳይሆን፣ አሁን አጣዳፊ የሆነና ነገን የሚወስን የቤተክርስቲያን ቀዳሚ ተግባር ነው። ዛሬ በልጆቻችን ላይ ካልጸለይንና የክርስቶስን ብርሃን ካላበራንላቸው፣ ነገ ዓለም በራሱ ጨለማ ይውጣቸዋል።"

በCEF ራዕይ መሠረት እያንዳንዱ የደግነት ክበብ (GNC) እና የስልጠና (TCE) ንቅናቄ ፍሬ የሚያፈራው በትውልድ ፀሎት ነው። ጨለማው በልጆቹ ላይ ከመስልጠኑ በፊት በፀሎት ቀድመን ስፍራውን መያዝ አለብን!

የዛሬው ጥሪያችን ለቤተክርስቲያን እና ለትውልድ አገልጋዮች በሙሉ፦
• ተነሺ፦ ስለ ትውልዱ መዳን በጉልበታችን እንቁም!
• አብሪ፦ የጸለይንለትን ትውልድ በጌታ ቃል እንቅረጽ!

የእግዚአብሔር ክብር በእኛ ላይ ወጥቷል፤ የልጆች ነገር የነገ ምርጫ ሳይሆን የዛሬ አጣዳፊ ሥራችን ነው። ዛሬ በፀሎት እንነሳ፥ እናብራ! 🔥ስለልጆቻችሁ የበለጠ ለመረዳት ቴሌግራሙን ይቀላቀሉ ተባረኩ
https://t.me/cefethiopia
https://t.me/cefethiopia

የሲኢኤፍ መሪ ቃልና የትውልዱ አጣዳፊነት"እያንዳንዱ ልጅ፣ በእያንዳንዱ ቀን፣ በሁሉም ቦታ!"ይህ የሲኢኤፍ ኢትዮጵያ የዘወትር ጥሪና ሸክም ነው። ዛሬ በየመንገዱ፣ በየቀበሌውና በየቤታችን ያሉ ...
31/05/2026

የሲኢኤፍ መሪ ቃልና የትውልዱ አጣዳፊነት
"እያንዳንዱ ልጅ፣ በእያንዳንዱ ቀን፣ በሁሉም ቦታ!"
ይህ የሲኢኤፍ ኢትዮጵያ የዘወትር ጥሪና ሸክም ነው። ዛሬ በየመንገዱ፣ በየቀበሌውና በየቤታችን ያሉ ልጆች ወንጌልን ሳይሰሙ እንዲያድጉ መፍቀድ ትውልዱን ለአደጋ አሳልፎ መስጠት ነው።
ልጆች ወንጌል የሚያስፈልጋቸው "ሲያድጉ" አይደለም፤ አሁን ገና በልጅነታቸው ነው።
ዓለም በራሷ መርዝና ፍልስፍና ሳትመርዛቸው በፊት፣ የእግዚአብሔርን አዳኝነት በለስላሳ ልባቸው ላይ መዝራት የዛሬ ስራችን ሊሆን ይገባል።
📖 "እንዲሁ ከነዚህ ከታናናሾቹ አንዱ እንዲጠፋ በሰማያት ያለው አባታችሁ ፈቃድ አይደለም።"

(ማቴዎስ 18:14)የዛሬ ተግባር፦ ዛሬ በአካባቢዎ የሚያዩትን እያንዳንዱን ልጅ እንደ እግዚአብሔር መንግስት እምቅ ሀብት አድርገው ይመልከቱት።

👇 በእርስዎ አመለካከት፣ በአሁኑ ሰዓት ልጆችን ከወንጌል እውነት እያራቃቸው ያለው ትልቁ የዘመኑ ፈተና ምንድነው?
ሀሳብዎን በኮሜንት ያካፍሉን?
ቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/cefethiopia
https://t.me/cefethiopia

CEF's Motto and the Urgency of the Generation
"Every child, every day, everywhere!"
This is the constant call and burden of CEF Ethiopia. Allowing children on every street, in every kebele, and in our homes today to grow up without hearing the Gospel is handing this generation over to danger.
Children need the Gospel not "when they grow up"; it is right now, in their childhood.
Before the world poisons them with its own venom and philosophy, sowing God's salvation upon their tender hearts must be our work today.
📖 "In the same way your Father in heaven is not willing that any of these little ones should perish."
(Matthew 18:14) Today's Action: Today, look at every child you see around you as a potential asset of the Kingdom of God.
👇 In your opinion, what is the biggest challenge of our time that is currently distancing children from the truth of the Gospel?
Share your thoughts in the comments?

27/05/2026

ወላጆች ልጆቻችሁን ሁሌም በእግዚአብሔር ላይ እንዲታመኑ ንገሯቸው። ኮመንት ላይ በኢየሱስ እታመናለው እያላችሁ ፃፉ

26/05/2026

እግዚአብሔር እጅግ ስለሚወደን ኃጢአታችንን ይቅር ብሎ የቤተሰቡ አካል ሊያደርገን ይፈልጋል ❤️
ዛሬ የእግዚአብሔር ቤተሰብ መሆን ትፈልጋለህ? በኢየሱስ እመን ኮሜንት ላይ አሜን በሉ
#ሲኢኤፍ #ልደት #ቤተሰብ #ልጅ

CYIA “Christian Youth In Action”ወጣትነት + ወንጌል = ታሪክ ለዋጭ ትውልድ መሆን! 🔥የ CYIA ስልጠና ሊጀምር ጥቂት ወራት ቀርተውታል።✅ ልጆችን ማገልገል ትወዳለህ?✅ ራ...
19/05/2026

CYIA “Christian Youth In Action”
ወጣትነት + ወንጌል = ታሪክ ለዋጭ ትውልድ መሆን! 🔥
የ CYIA ስልጠና ሊጀምር ጥቂት ወራት ቀርተውታል።

✅ ልጆችን ማገልገል ትወዳለህ?
✅ ራስህን ማሳደግ ትፈልጋለህ?
✅ የወንጌል አምባሳደር መሆንስ?
✅ የመሪነትን ጥበብ እየፈለክ ነው?
✅ የክረምቱ 10 ቀናት መላ ሕይወትህን ይቀይረዋል ከእኛ ጋር ሰልጥን።

የክረምት እቅድ ካለህ
እንግዲያውስ ቦታህን አሁኑኑ አቅድ! የክርስቶስ ወታደር ሆነህ የምትሰለጥንበት ልዩ ጊዜ እንዳያመልጥህ። CYIA “Christian Youth In Action” በሲ ኢ ኤፍ ኢትዮጲያ በየአመቱ ከ15-19 ዕድሜ ያሉትን አዳጊ ወጣቶችን ከኢትዮጵያ ከሁሉም አቅጣጫ በመቀበል ለ10 ቀናት የሚያሰለጥንበት አገልግሎት ነው።

አሁኑኑ ቴሌግራሙን በመቀላቀል ቀኑን ይከታተሉ።

አሁን በዚህ ይቀላቀሉ
👇👇👇
https://t.me/cefethiopia
https://t.me/cefethiopia
https://t.me/cefethiopia

የጂንካ TCE-2 ሥልጠና በድል ተጠናቀቀ! 🎊“ቀን ሳለ የላከኝን ሥራ ላደርግ ይገባኛል...” (ዮሐንስ 9፥4)በእግዚአብሔር ልዩ ረዳትነትና ቸርነት፣ በጂንካ ሲሰጥ የነበረው የ TCE-2 ሥልጠ...
13/05/2026

የጂንካ TCE-2 ሥልጠና በድል ተጠናቀቀ! 🎊

“ቀን ሳለ የላከኝን ሥራ ላደርግ ይገባኛል...” (ዮሐንስ 9፥4)
በእግዚአብሔር ልዩ ረዳትነትና ቸርነት፣ በጂንካ ሲሰጥ የነበረው የ TCE-2 ሥልጠና በታላቅ ድልና በስኬት ተጠናቋል።

በሥልጠናው ላይ የነበሩ ሁሉም ተማሪዎች ትምህርታቸውን በብቃት ማጠናቀቅ ችለዋል።

ምስክርነት
ወንድማችን አሰልጣኝ አማኑኤል ወደ ስልጠና ማእክል ለመሳፈር በሚወጣበት በደረሰበት የዝርፊያ እና የድደባ አደጋ ምክንያት በስልጠናው ላይ ባይካፈልም እግዚአብሔር ግን ለክፉዎች አሳልፎ አልሰጠውም በሰላም ተርፎ ለቤቱ በቅቷል በዚህ ሁሉ እና ሌሎች ተግዳሮቶች እያለፍን ጌታ በድል እያስጓዘን ነው ለብዙ ልጆች ወንጌልን በፍጥነት የሚያደርሱ ወታደሮችን እያፈራን እንገኛለን እግዚአብሔር ይመስገን።

ለዚህም ስኬት መንገዱን ላሳየን ለአምላካችን ክብርና ምስጋና ይግባው!
በጸሎት አብራችሁን የሆናችሁ ሁሉ ተባረኩ አሁንም፦

• ስልጠናው በሰላም እንዲጠናቀቅ የደከሙ አስተባባሪዎችንና አሰልጣኞችን ጌታ ስለረዳቸው እናመሰግናለን።
• ተመራቂ ሠልጣኞች ወደ ተግባራዊ አገልግሎት ሲሰማሩ ለቤተክርስቲያንና ለወገኖቻቸው የሚተርፍ ውጤታማ ሥራ እንዲሰሩ።
ቀጣዩ መርሃ ግብራችን በአዲስ አበባ የሚካሄድ ሲሆን፣ ጌታ በዚያም መልካም እንዲያደርግልን እንጸልያለን።

አገልግሎታችንበእግዚአብሔር ረዳትነት ይቀጥላል!

ሲኢኤፍን በፀሎት በምክር በገንዘብ አጋር በመሆን አብራችሁን ልጆችን በንጌል እየደረሳችሁ ያላችሁ ሁሉ ተባረኩልን። ሲ ኢ ኤፍ ኢትዮጲያ "እያንዳንዱን ልጅ በእያንዳንዱ ቀን በሁሉም ስፍራ!" 🌍👦👧
ለበለጠ መረጃ👇👇👇
https://t.me/cefethiopia
https://t.me/cefethiopia

ልጆች ማለት እግዚአብሔር ለሰው ልጅ የሰጠው ትልቁ የይቅርታ እና የፍቅር ማረጋገጫ ናቸው። እያንዳንዱ ልጆች ወደዚህች ምድር ሲመጣ፣ ፈጣሪ ገና በሰው ልጅ ላይ ተስፋ እንዳልቆረጠ የሚገልፅበት ...
02/05/2026

ልጆች ማለት እግዚአብሔር ለሰው ልጅ የሰጠው ትልቁ የይቅርታ እና የፍቅር ማረጋገጫ ናቸው። እያንዳንዱ ልጆች ወደዚህች ምድር ሲመጣ፣ ፈጣሪ ገና በሰው ልጅ ላይ ተስፋ እንዳልቆረጠ የሚገልፅበት ምስጢራዊ ቋንቋው ነው።
ለምን ልጆችን በጥልቀት ልንመለከታቸው ይገባል?
• ያለ ቅድመ ሁኔታ መውደድ፦ ልጅ ፍቅርን የሚሰጠው ለጥቅም ወይም ለምላሽ አይደለም። የእናት እና የአባቱን እቅፍ ብቻ በመናፈቅ ውስጥ ያለው ፍቅር፣ ዓለም ከሚሰጠን ማንኛውም ቁሳቁስ በላይ ውድ ነው።
• የንፅህና መስታወት፦ በልጆች አይን ውስጥ ቂም የለም፣ በልባቸው ውስጥ ጥላቻ ስፍራ የለውም። ተጣልተው በደቂቃ ውስጥ ተመልሰው መጫወታቸው፣ ዓለም ሰላም እንድትሆን ምን እንደሚያስፈልጋት የሚያስተምረን ትልቅ ትምህርት ነው።
• የነገው ቀለም፦ ዛሬ በልጆቻችን ልብ ውስጥ የምንዘራው የደግነት፣ የጥንካሬ እና የክብር ዘር ነገ ለሀገርና ለወገን የሚተርፍ ጥላ ሆኖ ይበቅላል።
መልክታችን ይሁን፦
ልጆችን በቁሳቁስ ማርካት ብቻ ሳይሆን፣ በጊዜያችን፣ በጥሞናችን እና ባልተቆጠበ ፍቅራችን እናሳድጋቸው። የእነሱ ሳቅ የቤታችን ሙቀት፣ የእነሱ ስኬት ደግሞ የድካማችን ውጤት ነው። ዛሬ የምንሰጣቸው ትኩረት ነገ ለሚገነቡት ዓለም መሰረት ነው።
"ልጅ የእናት እና የአባት ስም መጠሪያ ብቻ አይደለም፤ የነገው ዓለም መሪ፣ የዛሬው ልብ ሰላም ነው!

"እነሆ፥ ልጆች የእግዚአብሔር ስጦታ ናቸው፤ የሆድም ፍሬ የእርሱ ዋጋ ነው።"
(መዝሙረ ዳዊት 127:3)
Jon Telegram Channel
https://t.me/cefethiopia

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Child Evangelism Fellowship Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share