20/04/2026
ከወጣት-ተኮር እና ወጣት-መር ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ከኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት እና ከኢትዮጵያ ወጣቶች ፌዴሬሽን የተወጣጡ ወጣት መሪዎች ሚያዝያ 8 ቀን 2018 ዓ.ም “ወጣቶች የሰላም ዘብ” በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው የአንድ ቀን የባለድርሻ አካላት የውይይት መድረክ ላይ ተገኝተው ጥልቅ ምክክር አድርገዋል።
በኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት አዘጋጅነት እና በናሽናል ዴሞክራቲክ ኢንስቲትዩት የገንዘብ ድጋፍ የተካሄደው ይህ መድረክ፤ በዋናነት በ7ኛው አገራዊ ምርጫ ወቅት ግጭቶችን ለመከላከል የሚያስችሉ የጋራ ዕቅዶችን እና ተግባራትን ማከናወን በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ መክሯል።
የምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት አቶ አህመድ ሁሴን ለወጣቶቹ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ለተሻለች ኢትዮጵያ ግንባታ የወጣቶች ንቁ ተሳትፎ እና ለሰላም ግንባታ የሚያደርጉት አስተዋፅኦ ወሳኝ መሆኑን አስምረውበታል።
በመድረኩ ላይ ከአማራ፣ ከትግራይ፣ ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ ከድሬዳዋ፣ ከሐረሪ፣ ከአፋር፣ ከጋምቤላ፣ ከሲዳማ፣ ከደቡብ ኢትዮጵያ እና ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልሎች የተወጣጡ 40 ያህል ተሳታፊዎች እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተወካዮች ተገኝተዋል።
የናሽናል ዴሞክራቲክ ኢንስቲትዩት ተወካይ አቶ ልዑልሰገድ ግርማ በበኩላቸው፤ ይህ ውይይት የወጣቶችን ጉልበት ወደ ገንቢ የሲቪክ ተሳትፎ ለመቀየር እና የምርጫ ሂደቱ ሰላማዊና ሁሉንም ያካተተ እንዲሆን በጋራ ለመሥራት ትልቅ እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል።
ውይይቱ የተጠናቀቀው ተሳታፊዎች የሰላም፣ የኃላፊነት እና የገንቢ ተሳትፎ መልዕክቶችን ወደየማህበረሰባቸው ለማድረስ ቃል በመግባት እና የጋራ የአቋም መግለጫ በማጽደቅ ነው።
ፌስቡክ (https://lnkd.in/g9bz7izX)
ቴሌግራም (https://lnkd.in/erSZWhG2)
ዩትዩብ (https://lnkd.in/d2bsKXiw)
ትዊተር (X) (https://lnkd.in/gVr55XbE)
ሊንክድኢን (https://lnkd.in/g9bz7izX)
Young leaders from youth-led and youth-focused civil society organizations, political parties, the Ethiopian Youth Council, and the Ethiopian Youth Federation came together here in Addis Abeba on April 16, 2026, to have their say at a one-day-long Youth Multi-Stakeholder Dialogue held under the theme “Youth as Guardians of Peace.”
The meeting organized by the Ethiopian Civil Society Organizations Council (ECSOC) through the financial support of the National Democratic Institute (NDI) addressed the topics of youth, collaborative development of joint commitments and action plans to prevent violence during the upcoming 7th National Elections among others.
In his address to the youth gathering, President of ECSOC, Ahmed Hussen, emphasized that the active contribution of young people to peacebuilding is essential for ensuring a better future for Ethiopia.
The event brought together some 40 participants representing regions of Amhara, Tigray, Benishangul-Gumuz, Dire Dawa, Harari, Afar, Gambella, Sidama, Southern Ethiopia, and South West Ethiopia, among others as well as the National Election Board of Ethiopia (NEBE).
Representing NDI, Leulseged Girma, said that the dialogue is a crucial step in ensuring that the energy of Ethiopia’s youth is channeled into constructive civic participation and a collective pledge to keep the electoral process peaceful and inclusive.
Facebook (https://lnkd.in/e4QQ3cUp)
Telegram (https://lnkd.in/erSZWhG2)
YouTube (https://lnkd.in/d2bsKXiw)
X (Twitter) (https://lnkd.in/gVr55XbE)
LinkedIn (https://lnkd.in/g9bz7izX)