Addis Kidan Church Toronto - አዲስ ኪዳን ቤተ ክርስቲያን በቶሮንቶ

  • Home
  • Canada
  • Toronto, ON
  • Addis Kidan Church Toronto - አዲስ ኪዳን ቤተ ክርስቲያን በቶሮንቶ

Addis Kidan Church Toronto - አዲስ ኪዳን ቤተ ክርስቲያን በቶሮንቶ "We love because He first loved us" (1 John 4:19). We believe that His love is the foundation of everything we do.

06/14/2026

አመስግኑት፤ ስሙንም ባርኩ፤

06/12/2026
እውነተኛ ክርስቲያናዊ ሕይወት በየዕለቱ ክርስቶስን በመምስል በቃልና በምስክርነት የሚያድግ ነው። እርሱን አዳኝና ጌታ አድርገን በተቀበለው እውነት ባለተቆጠበ መሰጠት ልንኖር ተጠርተናል። አዳኝ...
06/10/2026

እውነተኛ ክርስቲያናዊ ሕይወት በየዕለቱ ክርስቶስን በመምስል በቃልና በምስክርነት የሚያድግ ነው። እርሱን አዳኝና ጌታ አድርገን በተቀበለው እውነት ባለተቆጠበ መሰጠት ልንኖር ተጠርተናል። አዳኝነቱና ጌትነቱ የሚለያዩ አይደሉም። በመስቀሉ ቤዛዊ ሞትና በትንሣኤው ድነት ማግኘታችን፣ እርሱን በሁሉ ነገር ጌታና ገዢ ባደረገ ሕይወት ሊገለጥ ይገባዋል። ያም ማለት ለእርሱ ፈቃድ ሁለንተናን አሳልፎ በመስጠት መኖር ማለት ነው።

ሐዋርያው ጳውሎስ ይህኑ እውነት ለቈላስይስ አማኞች እንዲህ በማለት በአጽንዖት ያሳስባል፦ "እንግዲህ ጌታ ክርስቶስ ኢየሱስን እንደ ተቀበላችሁት እንዲሁ በርሱ ኑሩ፤ በርሱ ተተክላችሁና ታንጻችሁ እንደ ተማራችሁት በእምነት ጸንታችሁ፣ የተትረፈረፈ ምስጋና እያቀረባችሁ ኑሩ።" (ቈላስይስ 2፡6-7)። "በእርሱ ተተክላችሁና ታንጻችሁ" የሚሉት መንታ ቃሎች የሚይሳዩን ስለማይታዩ ሁለት መሠረታዊ እውነቶች ነው። የመጀመሪያው የዛፍን ሥር የሚያመለክት ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ የቤትን ወይም የሕንጻን መሠረት የሚያሳይ ነው። ለዛፍ ሕይወትና ልምላሜ ሥሩ ለም መሬት ላይ መስደት አለበት። ሕይወት የሚያገኘው ከሥሩ ነውና! በንፋስ ተገፍቶ እንዳይወድቅ የሚጠብቀው ሥሩ ላይ ሥር ሰዶ በመተከሉ ነው።

ልክ እንዲሁ “ታንጻችሁ” የሚለው ሁለተኛው ቃልም የሚያመለክተው ስለማይታየውና ቤትን ወይም ሕንጻን ደግፎ ስለሚይዝ ጽኑ መሠረት ነው። አንድ ቤት በንፋስና ጐርፍ የመወደቁና ያለመውደቁ ብርታ የሚለካው በመሠርቱ ጥንካሬ ነው። በተመሳሳይ መልኩ ጌታም እንዲህ ይላል፦ “እንግዲህ ይህን ቃሌን ሰምቶ በተግባር የሚያውል፣ ቤቱን በዐለት ላይ የሠራን ብልኅ ሰው ይመስላል። ዶፍ ወረደ፤ ጐርፍም ጐረፈ፤ ነፋስም ነፈሰ፤ ያን ቤት መታው፤ በዐለትም ላይ ስለ ተመሠረተ አልወደቀም።" (ማቴ. 7፥ 24-26)።

የአማኝም ሕይወትም እንዲሁ ሊሆን ይገባዋል። ሥርና መሠረታችን (የማይታየው) በክርስቶስ ሕይወት፣ ሥራና ትምህርት ላይ ሥር ሊሰድ፤ ሊመሠረትም ይገባዋል። ሕይወታችን ፍሬያማ ሊሆን የሚችለው ክርስቶስን እንደተቀበልንበት መጠን ስንኖር ነው። ያም በተግባር የሚከተሉት ያጠቃልላል፦

⚓️ በቃሉ የበላይ ባለሥልጣንነት መኖርን
⚓️ በመንፈስ ቅዱስ ኀይል መመራትን
⚓️ በቅዱሳን ኅብረት ውስጥ - በክርስቶስ አካል ውስጥ መኖርን
⚓️ የኀጢአት ኑሮን መደበኛ (perpetual) ካደረገ ሕይወት በመለየት በቅድስና መኖርን
⚓️በቃልና በሕይወት ምስክርነት ሥርዐት ባለው የደቀ መዝሙርነት ሕይወት መመሥረትን

"እንደ ተማራችሁት በእምነት ጸንታችሁ፣ የተትረፈረፈ ምስጋና እያቀረባችሁ ኑሩ" - በእውነትኛና ጤናማ በሆነ አስተምህሮ መጽናት፤ እንዲሁም እግዚአብሔር በክርስቶስ ስለ ሰጠን የዘላላም ሕይወት፣ ልጅነት፣ ተስፋና ቅድስና በየዕለቱ እያመሰገንን መኖር ማለት ነው። ክርስትና ሲሰማን ብቻ የሚኖር ሕይወት አይደለም። ክባዶ ስሜታዊነት ያለፈና በፍሬያማነት በየጊዜው የሚያድግ ሕያውነት እንጂ! በራስ ጽድቅ ላይ በተመሠረተ “የአድርግና የአታድርግ” ሕግጋት አምላኪነት ደረቅ ሕይወት ሳይሆን፣ እግዚአብሔር ከመውደዳችን የተነሣ ራሳችንን ለእርሱ ጌትነት አሳልፈን በመስጠት የምንኖረው የምስጋና ሕይወት ነው። ለእግዚአብሔር ወሰን የሌለው ፍቅር ያለን ምላሽ እውነተኛና ያልተበረዘ ሕያው አምልኮ ነው። ይህም ማለት፣ ከሚታወቅና በድፍረት ከሚኖር ዓለማዊነት በመለየት በሁሉ ረገድ በቅድስና ለእግዚአብሔር ክብር ለመኖር መወሰን ማለት ነው።

ቅርንጫፍ ሕያውነቱ የሚለካው ከግንዱ ጋር በተጣበቀት ልክ እንደ ሆነ፤ የሕንጻም ጽናት በመሠረቱ ጥንካሬ እንደሚወሰን፣ የእኛ ፍሬያማነትና ጥንካሬ የሚወሰነው በክርቶስ ላይ ተመሥርተን ሥር በሰደድንበት መጠን ያህል ብቻ ነው። ጳውሎስ እንዳለ “በእምነት፣ በቃል፣ በዕውቀት፣ በፍጹም ትጋትና ፍቅር” ማደግ ነው። (2 ቆሮ. 8፥7)

ጌታ ሆይ ጸጋህን ስጠን። አሜን!

06/07/2026

በምስጋና ወደ ደጆቹ፣ በውዳሴም ወደ አደባባዮቹ ግቡ፤

“ከጌታ የተቀበልኩትና ለእናንተም ያስተላለፍኩላችሁ ትምህርት ይህ ነው፤ ጌታ አልፎ በተሰጠበት ሌሊት ኅብስት አነሣ፤ የምስጋናም ጸሎት አድርጎ ቈረሰውና “[እንካችሁ ብሉ፤] ይህ ለእናንተ የሚሆ...
06/07/2026

“ከጌታ የተቀበልኩትና ለእናንተም ያስተላለፍኩላችሁ ትምህርት ይህ ነው፤ ጌታ አልፎ በተሰጠበት ሌሊት ኅብስት አነሣ፤ የምስጋናም ጸሎት አድርጎ ቈረሰውና “[እንካችሁ ብሉ፤] ይህ ለእናንተ የሚሆን ሥጋዬ ነው፤ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት” አለ። እንዲሁም ከእራት በኋላ ጽዋውን አንሥቶ “ይህ ጽዋ በደሜ የሚመሠረት አዲስ ኪዳን ነው፤ በምትጠጡበት ጊዜ ሁሉ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት” አለ። ይህን ኅብስት በምትበሉበትና ይህንንም ጽዋ በምትጠጡበት ጊዜ ሁሉ ጌታ እስከሚመጣበት ጊዜ ድረስ ሞቱን ትናገራላችሁ። ” (1 ቆሮ. 11‬:‭23‬-‭26)

“እግዚአብሔርን አንዲት ነገር እለምነዋለሁ፤ እርሷንም እሻለሁ፤ ይኸውም በሕይወቴ ዘመን ሁሉ፣ በእግዚአብሔር ቤት እኖር ዘንድ፣ የእግዚአብሔርን ክብር ውበት አይ ዘንድ፣ በመቅደሱም ሆኜ አሰላስ...
06/05/2026

“እግዚአብሔርን አንዲት ነገር እለምነዋለሁ፤ እርሷንም እሻለሁ፤ ይኸውም በሕይወቴ ዘመን ሁሉ፣ በእግዚአብሔር ቤት እኖር ዘንድ፣ የእግዚአብሔርን ክብር ውበት አይ ዘንድ፣ በመቅደሱም ሆኜ አሰላስል ዘንድ ነው። በመከራ ቀን፣ በድንኳኑ ውስጥ ይሰውረኛልና፤ በተቀደሰ ድንኳኑም ውስጥ ይሸሽገኛል፤ በዐለቱ ላይ ከፍ ያደርገኛል። “ፊቴን ፈልጉ” ባልህ ጊዜ፤ ልቤ፣ እግዚአብሔር ሆይ፤ ፊትህን እሻለሁ አለች . . . (መዝሙር‬ ‭27‬:‭4‬-‭5‬, ‭8‬)

“የገዛ ወንድሞቹ እንኳ አላመኑበትም ነበር።” (ዮሐንስ‬ ‭7‬:‭5‬)
06/03/2026

“የገዛ ወንድሞቹ እንኳ አላመኑበትም ነበር።” (ዮሐንስ‬ ‭7‬:‭5‬)

05/31/2026

በቅዱስ ስሙ ተጓደዱ፤ እግዚአብሔርን የሚፈልጉ ሁሉ፣ ልባቸው ሐሤት ያድርግ። (መዝሙር 105:3)

Address

871 Pape Avenue
Toronto, ON
M4K3T7

Opening Hours

Friday 6pm - 9pm
Sunday 1pm - 6pm

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Kidan Church Toronto - አዲስ ኪዳን ቤተ ክርስቲያን በቶሮንቶ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Addis Kidan Church Toronto - አዲስ ኪዳን ቤተ ክርስቲያን በቶሮንቶ:

Share