25/05/2026
Outcome based curriculum Review workshop ተካሄደ።
ግንቦት 17፣ 2018 ዓ.ም
በወልድያ ዩኒቨርሲቲ በቴክኖሎጅ ኢንስቲቱት በሲቪልና ውሃ ሃብት ምህንድስና ት/ቤት ኮንስትራክሽን ቴክኖሎጂ እና ማኔጅመንት ትምህርት ክፍል የቅድመ ምረቃ ስርዓተ-ትምህርት ክለሳ የውጭ ግምገማ (ወርክሾፕ) አካሂዷል።
በስርአተ ትምህርት ክለሳ መድረክ ላይ የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ፕሮግራሞች ዳይሬክተር መ/ር ሳሙኤል ንጋቴ፣ የት/ቤቱ ዲን መ/ረ ምላሹ ሲሳይ፣ የወልድያ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ጥራት ዳይሬክተር ወ/ሮ ዙፋን አበበ ፣የትምህርት ክፍል ሃላፊዋ መ/ርት ሰላማዊት አባይ ፣ ከየክፍሎቹ የመጡ መምህራን በአካል የተገኙ ሲሆን፤ የውጭ ገምጋሚ ባለሙያዎች ከትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን የተከበሩ አቶ አቦነህ ተስፋየ እና ከሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዶ/ር ደሳለኝ ግርማ በበይነ-መረብ በመገኘት ሰፊ ግምገማ አካሂደዋል።
ኮንስትራክሽን ቴክኖሎጂ እና ማኔጅመንት ትምህርት ክፍል ኃላፊ መ/ርት ሰላማዊት አባይ ለገምጋሚዎች ከልብ የመነጨ ምስጋና በመስጠት የወርክሾፑ ዋና ዓላማ ተማሪዎችን በተግባራዊ እውቀትና በምርምር ውጤታማ ሊያደርግ የሚችል ውጤት ተኮር (Outcome-based) ስርዓተ-ትምህርት መቅረጽ መሆኑን ተናግረዋል።
የት/ቤቱ ዲን መ/ር ምላሱ በበኩላቸው በዘርፉ ያለውን ወቅታዊ የሳይንስና ቴክኖሎጂ እድገት ያገናዘበ እና የሀገሪቱን ፍላጎት የሚያሟላ የቴክኖሎጂ ትምህርት ለመስጠት እንዲቻል፣ ቀደም ሲል የነበረውን ስርዓተ-ትምህርት አሻሽለናል። ከትምህርት ክፍል እስከ ኮሌጅ (ት/ቤት) ደረጃ የተገመገመውን ይህንን ሰነድ ዛሬ ለውጭ ምሁራንና ባለሙያዎች ግምገማ ማቅረብ ችለናል ብለዋል።
ለውይይቱ መነሻ የሚሆን በትምህርት ክፍሉ የተከናወነ የዳሰሳ ጥናትና የስርዓተ-ትምህርት ክለሳ ሰነድ በአዘጋጅ ኮሚቴው አማካኝነት ቀርቧል።
በቀረበው ሰነድ ላይ በመነሳት ከትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን አቶ አቦነህ ተስፋየ ፣ ከሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዶ/ር ደሳለኝ ግርማ እና ሌሎች የዘርፉ ባለሙያዎች በበየነ መረብ በመግባት በርካታ ጠቃሚና ገንቢ አስተያየቶችን ሰጥተዋል።
በማጠቃለያውም፣ የትምህርት ክፍሉ አዘጋጅ በውስጣዊና በውጫዊ ተሳታፊ አካላት የተሰጡትን ጠቃሚ ሀሳቦችና የተግባር ትምህርትን ይበልጥ የሚያጠናክሩ ግብዓቶችን በሙሉ በመውሰድ፣ ደረጃውንና ጥራቱን የጠበቀ ስርዓተ-ትምህርት አዘጋጅተው ለማጠናቀቅ በትኩረት እንደሚሰሩ አስታውቀዋል።
ስለ ፎቶው : በስልክ የተቀረፀ ነው።
Addresses
E-mail
[email protected]" rel="ugc" target="_blank">https://[email protected]
TG: t.me/CoTM_assocciation
FB: facebook.com/CoTMassociation
YT: youtube.com/
TT: tiktok.com/