09/05/2026
[ወልድያ፤ ግንቦት 30 ቀን 2018 ዓ.ም]
የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰጧቸውን ትምህርቶች በጥራትና በደረጃ መመዘኛ (Accreditation) ማለፍ እንዳለባቸው ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት፤ በወልድያ ዩኒቨርሲቲ የሲቪልና ውሃ ሀብት ምህንድስና ትምህርት ቤት ስር የሚገኘው የኮንስትራክሽን ቴክኖሎጂና ማኔጅመንት (CoTM) የትምህርት ክፍል ይህንኑ መመዘኛ በብቃት አሟልቶ አፅድቋል።
በተካሄደው ልዩ ጉባኤ፣ የትምህርት ቤቱ ዲን አቶ ምላሹ ሲሳይ እና የትምህርት ክፍሉ ኃላፊ ወረ/ት ሰላማዊት አባይ እንዲሁም የSAC አባላት በሙሉ በተገኙበት፣ የክለሳ ሰነዱ በጥልቀት ተገምግሞ በሙሉ ድምፅ ጸድቋል።
Outcome-Based Education (OBE) መሸጋገሩ ከሀገራዊ ፋይዳው ባሻገር የሚከተሉትን ስትራቴጂካዊ ጥቅሞች ያስገኛል፦
1. International Recognition: ይህ ስርዓተ-ትምህርት እንደ Washington Accord ያሉ ዓለም አቀፍ የምህንድስና ስምምነቶችን መመዘኛ የተከተለ በመሆኑ፣ ተማሪዎቻችን በዓለም ዙሪያ በሚገኙ የትምህርት ተቋማትና የሥራ ገበያዎች በቀጥታ እውቅና እንዲያገኙ ያደርጋል።
2. Student Mobility: ምሩቃኖቻችን በውጭ ሀገር የትምህርት ዕድሎችን (Scholarships) ሲያመለክቱ የወሰዱት ትምህርት በዓለም አቀፍ ደረጃ ተመጣጣኝነቱ (Equivalency) በቀላሉ የሚረጋገጥ ይሆናል።
3. Industry Alignment: ትምህርቱ በውጤትና በክህሎት ላይ የተመሰረተ በመሆኑ፣ አሰሪ ድርጅቶች የሚፈልጉትን ብቁ ባለሙያ በቀጥታ ለማግኘት ያስችላቸዋል።
4. Continuous Quality Improvement: ስርዓቱ በየጊዜው ራሱን የሚገመግምና ከቴክኖሎጂ እድገት ጋር አብሮ የሚራመድ እንዲሆን ያደርገዋል።
ይህንን ውጤት ተከትሎ፣ በወልድያ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት በስርዓተ-ትምህርት አተገባበር እና በዘርፉ የወደፊት አቅጣጫዎች ላይ የሚመክር ታላቅ ወርክሾፕ (Grand Workshop) በቅርቡ ይካሄዳል። በዘርፉ ባለድርሻ አካላት የሆናችሁ ሁሉ በዚህ መድረክ ላይ እንድትገኙ በአክብሮት ተጋብዛችኋል።
መልካም ቀን
Addresses
E-mail
[email protected]" rel="ugc" target="_blank">https://[email protected]
Telegram
https://t.me/CoTM_assocciation
Youtube:
www.youtube.com/
Tiktok
tiktok.com/
Facebook https://www.facebook.com/CoTMassociation
`