Wolayta Zone Health Department /ወላይታ ዞን ጤና መምሪያ

  • Home
  • Ethiopia
  • Sodo
  • Wolayta Zone Health Department /ወላይታ ዞን ጤና መምሪያ

Wolayta Zone Health Department /ወላይታ ዞን ጤና መምሪያ Health for All!!

"የተሳሳተ መረጃ የተሳሳተ ውሳኔ እንዲወሰን ያደርጋል"አቶ ነቢዩ ቤዛበደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የሰው ኃብት አስተዳደርና ልማት ዳይሬክቶሬት ዞን ጤና መምሪያዎችና ተጠሪ ተቋማት የጋራ ም...
19/06/2026

"የተሳሳተ መረጃ የተሳሳተ ውሳኔ እንዲወሰን ያደርጋል"አቶ ነቢዩ ቤዛ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የሰው ኃብት አስተዳደርና ልማት ዳይሬክቶሬት ዞን ጤና መምሪያዎችና ተጠሪ ተቋማት የጋራ ምክክር መድረክ እያካሄደ ነው፡፡

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ጤና ቢሮ ኃላፊና አስተዳደርና ፋይናንስ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነቢዩ ቤዛ በመክፈቻ ንግግራቸው በጤናው ሴክተር የጤና ሰው ሀብቱን ማጠናከር ቁልፍ ተግባር በመሆኑ በትኩረት ሊሠራበት ይገባል ብለዋል፡፡

የመረጃ ጥራትና የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማስፈት የሰው ኃብቱን ማብቃት ዋንኛ ተግባር ነው ያሉት አቶ ነቢዩ፤ ሪፎርሙን መሠረት ያደረገ ክልላዊ የጤና ሴክተር ሰው ኃይል አሠራርን በዕውቀት መሥራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

መድረኩ ከሰው ኃይል አንፃር ያልተፈቱ የሴክተሩ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችለን መድረክ በመሆኑ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ አሳስበዋል፡፡

በጤና ሚኒስትር የብቃትና የሰው ኃብት ልማት አስተዳደር መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሐብታሙ ደምሴ ሰነድ ባቀረቡበት ወቅት እንደተናገሩት፤ በጤናው ሴክተር የአገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርምን ማጠናከር ያስፈልጋል ብለዋል።

ነፃና ገለልተኛ ሲቪል ሰርቫንት መገንባት፣ ብዝሃነትና አካታችነትን፣ የመንግስት አስተዳደርና አደረጃጀትን ማጠናከር፣ ቀልጣፋና ተደራሽ የጤና አገልግሎት ተደራሽ ማድረግ እንዲሁም የብቃት ማረጋገጫና ምዘና ሥርዓትን መዘርጋት እንደሚገባ አቶ ሐብታሙ አስገንዝበዋል፡፡

በጤና ቢሮ የሰው ኃብት አስተዳደርና ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አምሳሉ ተስፋዬ የጤና ሴክተር ሪፎርም ሥራን በማጠናከርና የሰው ኃይል ሥምርትን በአግባቡ በመጠቀም የሰው ኃይል እጥረትን መቅረፍ የሚያስችል ስርዓት ነው ብለዋል፡፡

የሰው ኃብት መረጃ አያያዝና ምዝገባ ሥርዓትን ዲጂታላይዝድ በማድረግ የመረጃ ድግግሞሽ፣ የመጥፋትና መቅረት ችግሮችን መቅረፍ የሚያስችል ተግባቦት እንደሚያስፈልግ ዳይሬክተሩ አሳስበዋል፡፡

ለጤና ባለሙያው አጋዥ አሰራርና የመረጃ አደረጃጀት ሥርዓትን በመዘርጋት ዞኖች ችግር ፈቺ ተግባር በማከናወን የባለሙያውን እንግልት መቅረፍ የሚያስችል አሠራር መከተል እንዳለባቸው አቶ አምሳሉ ተናግረዋል፡፡

በቢጠና መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል አንድት እናት ሦስት ልጆችን በሠላም ተገላገለች በወላይታ ዞን ዱጉና ፋንጎ ወረዳ ቢጠና መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል አንድት እናት ሦስት ልጆችን በሠላም ተገላግላ...
18/06/2026

በቢጠና መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል አንድት እናት ሦስት ልጆችን በሠላም ተገላገለች

በወላይታ ዞን ዱጉና ፋንጎ ወረዳ ቢጠና መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል አንድት እናት ሦስት ልጆችን በሠላም ተገላግላለች።

በአሁኑ ሰዓት እናትም ጨቅላዎቹም በመልካም ጤንነት ላይ መሆናቸውን ከሆስፒታሉ በደረሰን መረጃ ለማወቅ ተችሏል።

የዓለም ስጋት የሆነው የፀረ-ተህዋሲያን መድሃኒቶች በጀርሞች መላመድ የፀረ-ተህዋሲያን መድሃኒቶች በጀርሞች መላመድ የዓለም ትልቁ ስጋት ሆኗል አለ የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን።የፀ...
18/06/2026

የዓለም ስጋት የሆነው የፀረ-ተህዋሲያን መድሃኒቶች በጀርሞች መላመድ

የፀረ-ተህዋሲያን መድሃኒቶች በጀርሞች መላመድ የዓለም ትልቁ ስጋት ሆኗል አለ የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን።

የፀረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች በጀርሞች መለመድ የግንዛቤ ማስጨበጫ ቀን እየተከበረ ይገኛል።

የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሄራን ገርባ በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ የፀረ-ተህዋሲያን መድሃኒቶች በጀርሞች መለመድ ችግር በዓለም አቀፍ ደረጃ በየዓመቱ ለ750 ሺህ ሰዎች ሞት ምክንያት ይሆናል።

ችግሩ በአዳጊ ሀገራት ከፍ እንደሚል አንስተው ÷ ወደ 5 በመቶ የኢኮኖሚ ኪሳራ እንደሚያደርስ ጥናቶች ማረጋገጣቸውን ጠቁመዋል።

አግባብ ያልሆነ የፀረ-ተዋህሲያን መድሃኒቶችን መጠቀም፣ ከትዕዛዝ ውጪ መድሃኒቶችን ጨምሮና ቀንሶ መውሰድ፣ የግልና የአከባቢ ንፅህናን አለመጠበቅ እና መሰል ጥንቃቄ የጎደላቸው ተግባራት ችግሩን ከሚያስከትሉ መንስኤዎች መካከል ናቸው ብለዋል።

ችግሩን ለመቅረፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ሀገር አቀፍ የማህበረሰብ ፋርማሲዎች እንዲቋቋሙ ለማድረግ እየተሰራ እንደሆነ ገልጸዋል።

ባለስልጣኑ ከጤና ሚኒስቴር እና ከሌሎች መንግሥታዊና መንግሥታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር በጋራ የግንዛቤ ማስፋት ሥራ እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

(ኤፍ ኤም ሲ)

በዳሞት ጋሌ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ከJSI ከተባለ ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር የክትባት ፍትሃዊነት እና ተደራሽነት እንድሁም የ11 ወራት የእናቶች ህጻናት ጤናና ስርዓተ ምግብ አፈጻጸም ...
17/06/2026

በዳሞት ጋሌ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ከJSI ከተባለ ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር የክትባት ፍትሃዊነት እና ተደራሽነት እንድሁም የ11 ወራት የእናቶች ህጻናት ጤናና ስርዓተ ምግብ አፈጻጸም መድረክ ተካሂዷል

በመድረኩ የዳሞት ጋሌ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍሰሃ ዮናስ እንደገለጹት የእናቶች እና ህጻናት ጤና በዘላቂነት መጠበቅ ማህበራዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ጉልህ ሚና ይጫወታል ሲሉ አሳስበዋል።

ባለፉት 11 ወራት በእናቶች ህጻናት ጤናና ሥርዓተ-ምግብ አገልግሎት ሥራዎች አፈጻጸም የታዩ ጉድለቶች በፍጥነት ሊታረም እንደሚገባ ኃላፊው ጠቁመዋል።

በሁሉም ካችመንቶች የሚሰሩ አጠቃላይ የጤና ተግባራትን ሁሉም ባለድርሻ አካላት የሚጠበቅበትን ኃላፊነት በተገቢው መወጣት እንደሚገባ አሳስበዋል።

በመድረኩ የወላይታ ዞን ጤና መምሪያ የእናቶች ህጻናት ጤናና ስርዓተ ምግብ ዳይሬክቶሬት ቡድን መሪ አቶ ጎጆለ ጎአ፣ በJSI ኢትዮጵያ የወላይታ ክላስተር ክትባት አስተባባሪ አቶ ሙሉቀን ፋንታ፣ የወረዳው ጤና ጽ/ቤት ማነጅመንት አባላት፣ የጤና ጣቢያ ኃላፊዎች እና የጤና ኤክስቴሽን ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል።

የ2019 በጀት ዓመት ወረዳን መሰረት ያደረገ ዞናዊ ዕቅድ ማስጀመሪያ መድረክ ተጀመረ ሰኔ 10 2018 ዓ.ም፤ወላይታ ሶዶ፤የወላይታ ዞን ጤና መምሪያ የ2019 በጀት ዓመት ወረዳን መሰረት ያደ...
17/06/2026

የ2019 በጀት ዓመት ወረዳን መሰረት ያደረገ ዞናዊ ዕቅድ ማስጀመሪያ መድረክ ተጀመረ

ሰኔ 10 2018 ዓ.ም፤ወላይታ ሶዶ፤የወላይታ ዞን ጤና መምሪያ የ2019 በጀት ዓመት ወረዳን መሰረት ያደረገ የጤና ዕቅድ መድረክ መካሄድ ጀምሯል።

በመድረኩ ማስጀመሪያ ላይ የተገኙት የወላይታ ዞን ጤና መምሪያ ሀላፊ አቶ ዳዊት ደሳለኝ ባስተላለፉት መልዕክት መምሪያው መረጃን መሠረት ያደረገ የጤና ሥርዓት ግንባታን እንደ ዋና ምሰሶ ወስዶ እየሠራ መሆኑን ተናግረዋል።

ቀጣዩ ዓመት የማህበረሰቡን መሰረታዊ የጤና አገልግሎት ክፍተቶች የምንሞላበት ዓመት መሆኑን የገለጹት ሀላፊው እቅዱ የዞኑን የጤና ሥርዓት ወደ ላቀ ደረጃ በማሸጋገር ለክልላዊና ሀገራዊ የጤና ትራንስፎርሜሽን ግብ ስኬት ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት አስረድተዋል።

ዕቅዱ በትክክለኛ የመነሻ መረጃ ላይ ተመስርቶ መሰራት እንዳለበት ገልጸው፣ የዞኑ ነባራዊ ሁኔታ፣ የጤና ተቋማት አቅም፣ የአገልግሎት ሽፋን፣ የጥራት መመዘኛዎችና የልማት አጋሮች ድጋፍ በተገቢው ሁኔታ ተገምግሞ ወደ ዕቅድ ሊገባ እንደሚገባ አሳስበዋል።

የዕቅድ ሂደቱም “አንድ ዕቅድ፣ አንድ በጀት እና አንድ ሪፖርት” በሚለው መርህ ላይ ተመስርቶ በሁሉም የጤና ዘርፍ መዋቅሮች መካከል ተናባቢነትን ማጠናከር እንደሚጠበቅም አሳስበዋል።

የወላይታ ዞን ጤና መምሪያ የልማት ዕ/ኢ/አ/ዳይሬክቶሬት ቡድን መሪ አቶ መሳይ ሳሙኤል በበኩላቸው የተሻለ መረጃ፣ የተሻለ ዕቅድ፣ የተሻለ የጤና አገልግሎት” በሚል መርህ ታሳቢ ያደረገው ይህ ዕቅድ የዞኑን የጤና ሥርዓት ለውጥን የሚያፋጥን መሠረታዊ ሰነድ እንደሚሆን ጠቁመዋል::

በዕቅድ ዝግጅቱ ወቅት የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም በጥልቀት እንደሚተነተን እና በዚህም የታዩ ጠንካራ አፈጻጸሞች፣ ያጋጠሙ ተግዳሮቶች፣ የመረጃ ክፍተቶችና ስጋቶች በመለየት ለ2019 በጀት ዓመት የተሻለ አፈጻጸም እንዲመዘገብ መሠረት ይጣላል ብለዋል።

በዕቅድ ዝግጅቱ ላይ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ከፍተኛ ባለሙያዎች፣ የዞኑ ጤና መምሪያ ማኔጅመንት፣ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፣ ከወረዳ/ከተማ ጤና ጽ/ቤት የተወጣጡ ባለሙያዎች እንዲሁም የሆስፒታል እና ጤና ጣቢያ ሀላፊዎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።

የቦምቤ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በአንድ ዓመት ጊዜ ዉስጥ ለ100 እናቶች የማህፀን ዉልቃት ቀዶ ህክምና አገልግሎት መሰጠቱ ተገለፀ በወላይታ ዞን በቦምቤ ከተማ አስተዳደር የቦምቤ መጀመሪያ ደ...
16/06/2026

የቦምቤ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በአንድ ዓመት ጊዜ ዉስጥ ለ100 እናቶች የማህፀን ዉልቃት ቀዶ ህክምና አገልግሎት መሰጠቱ ተገለፀ

በወላይታ ዞን በቦምቤ ከተማ አስተዳደር የቦምቤ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በአንድ ዓመት ጊዜ ዉስጥ ለ100 እናቶች የማህፀን ዉልቃት ቀዶ ህክምና አገልግሎት በመደበኛ ህክምና መሰጠቱ ተገለጸ።

ይህ የተገለጸው ሆስፒታሉ ባዘጋጀው የ100ኛ እናት ቀዶ ህክምና በስኬት መጠናቀቁን ተከትሎ ለአገልግሎቱ መሳካት የላቀ አሰተዋጽኦ ላበረከቱት የሆስፒታሉ የማህጸንና የፅንስ ህክምና ስፔሻሊስት ሀኪም ዶ/ር ጌታሁን ወዳሎ፣ አጠቃላይ የኦፕራስዮን ክፍል ባለሙያዎች እና ለሆስፒታሉ ማኔጅመንት በተዘጋጀው የምስጋና ፕሮግራም ነው።

ከዚህ በፊት በማህፀን ውልቃት በሽታ የተጠቁ እናቶች ወላይታ ሶዶ እና ሌሎች አከባቢዎች በመጓዝ ለኢኮኖሚው፣ ማህበራዊ እና ስነልቦናዊ ቀውስ ውስጥ ገብተው የህክምና አገልግሎት እያገኙ መቆየታቸው ይታወሳል።

በባይራ ኮይሻ ወረዳ የአልጋ አጎበር ስርጭትና አጠቃቀም ዙሪያ ለባለሙያዎች ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል በወላይታ ዞን ባይራ ኮይሻ ወረዳ የአልጋ አጎበር ስርጭት፣ አሰቃቀልና አጠቃቀም ዙሪያ ለባለ...
16/06/2026

በባይራ ኮይሻ ወረዳ የአልጋ አጎበር ስርጭትና አጠቃቀም ዙሪያ ለባለሙያዎች ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል

በወላይታ ዞን ባይራ ኮይሻ ወረዳ የአልጋ አጎበር ስርጭት፣ አሰቃቀልና አጠቃቀም ዙሪያ ለባለሙያዎች ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ከወላይታ ዞን ጤና መምሪያ እና PMI Evolve ከተባለው አጋር ድርጅት ጋር በመተባበር የአልጋ አጎበር ስርጭት ቅድመ ምዝገባ፣ ስርጭት እና የድህረ ዘመቻ ሥራዎች ዙሪያ ለባለድርሻ አካላት የተዘጋጀ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና መሆኑ ተነግሯል።

የወባ በሽታ ስርጭትን ለመግታት የአልጋ አጎበር አጠቃቀምን ለማሻሻል የጤና ባለሙያዎችና የባለድርሻ አካላት ቁርጠኝነት ወሳኝ እንደሆነም ተነስቷል።

መድረኩ በዋናነት በተቀናጀ መንገድ ሁሉን የህብረተሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ የአልጋ/የመኝታ አጎበር በማሰራጨት አጠቃቀሙን ለማሻሻል ያለመ እንደሆነ ተጠቁመዋል።

በመድረኩ የወላይታ ዞን ጤና መምሪያ የወባ፣ ተላላፊ ያልሆኑና ትኩረት የሚሹ በሽታዎች አስተባባሪ አቶ ሳሙኤል ናና፣ የወረዳው ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አካሉ ኮሮቶ ጨምሮ የወረዳ ጤና ጽ/ቤት ባለሙያዎች፣ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛሉ።

“እንዲህ ዓይነቱ ነገር በኢትዮጵያም ሆነ በአፍሪካ ሆኖ የማያውቅ ነው”ወንድሙን በ6 ሳምንት የበለጠው ሕፃን እና የ74 ቀን የሆስፒታል ቆይታአንዲት የ19 ሳምንት እርጉዝ እናት ከፍተኛ የደም ...
15/06/2026

“እንዲህ ዓይነቱ ነገር በኢትዮጵያም ሆነ በአፍሪካ ሆኖ የማያውቅ ነው”

ወንድሙን በ6 ሳምንት የበለጠው ሕፃን እና የ74 ቀን የሆስፒታል ቆይታ

አንዲት የ19 ሳምንት እርጉዝ እናት ከፍተኛ የደም መፍሰስ እና የምጥ ምልክቶች እያሳየች ወደ ማህፀንና ፅንስ ክፍል መጣች። በተረኛ የነበሩት ሚድዋይፎች ሲመረምሯት፣ የአንድ ፅንስ እጅ ከማህፀን በር ውጭ(Prolapsing hand)መታየቱን አስተዋሉ። ይህንንም ሁኔታ ለተረኛው የማህፀንና ፅንስ ሐኪም በአስቸኳይ አሳወቁት።

ሐኪሙ በፍጥነት በመድረስ ምርመራ ሲያደርግ፣ እናቱ መንታ እርግዝና እንዳላት አረጋገጠ። አንደኛው ሕፃን በመወለድ ሂደት ላይ ነበር፤ ሌላኛው ደግሞ ገና በማህፀን ውስጥ ነበር። ብዙም ሳይቆይ አንደኛው መንታ በ19 ሳምንት ተወለደ(ዉርጃ ሆነ)።

በዚህ ጊዜ ሐኪሙ ሁለተኛውን ፅንስ በማህፀን ውስጥ ለማቆየት የሚያስችል ልዩ ውሳኔ አደረገ። ይህም Rescue Cerclage በመባል የሚታወቀው በጊዜያዊነት የማህፀን በር ማጥበብ ሕክምና ነበር። ህክናዉን በማድረግ እናት ሆስፒታል ዉስጥ እንድትቆይ ተደረገ።ሕክምናው ተሳክቶ፣ ሁለተኛው ፅንስ ተጨማሪ 6 ሳምንታት በማህፀን ውስጥ መቆየት ቻለ።

ከ6 ሳምንታት በኋላ፣ በ25 ሳምንት እርግዝና እና 960 ግራም ክብደት ሁለተኛው መንታ በተፈጥሯዊ ምጥ ተወለደ። ምንም እንኳን በእርግዝና ዕድሜው እና በክብደቱ መሰረት እጅግ ቀድሞ የተወለደ ሕፃን ቢሆንም፣ ወዲያውኑ ወደ ጨቅላ ሕፃናት ጥብቅ ጥንቃቄ (NICU) ክፍል ተዛወረ።

በNICU ውስጥ በመተንፈሻ ማሽን ድጋፍ ተደረገለት፣ እንዲሁም የሳምባ እድገትን የሚያግዝ surfactant መድሃኒት ተሰጠው። የጨቅላ ሕፃናት ክፍል ባለሙያዎች ቀንና ሌሊት ያለ እረፍት ባደረጉት ጥረት፣ ሕፃኑ 74 ቀናት በሆስፒታል ካሳለፈ በኋላ ክብደቱ 2055 ግራም ደርሶ በጤና ወደ ቤቱ ተሸኘ።

ይህ ታሪክ የሕክምና ዕውቀት፣ ፈጣን ውሳኔ እና የቡድን ሥራ በአንድነት ሲሰሩ ሕይወት እንዴት ሊድን እንደሚችል የሚያሳይ አስደናቂ ምሳሌ ነው።

የrescue cerclage (በጊዜያዊነት የማህፀን በር ማጥበብ)የሰሩት ዶ/ር ኔት (የማህፀን እና ፅንስ ስፔሻሊስት ሀኪም) ሲናገሩም :-
ታምራት ታምራት ነዉ ።ለ30 ዓመት የማህፀን እና ፅንስ ሃኪም ሁኘ ብዙ ልጆች አዋልጃለሁ። ከአንደኛዉ መንታ ዉርጃ በኋላ ሌላዉ እንዲቀጥል ብዙ ጊዜ ሞክሬ አዉቃለሁ ። የሞከሩም አዉቃለሁ። ነገር ግን ተሳክቶልኝ ሁለተኛዉ መንታ መሃፀን ዉስጥ አድጎ ተወልዶ አያዉቅም ። በአፍሪካም በኢትዮጵያም ተሳክቶ የታተመ ወረቀት አላየሁም። ስለዚህ ታምራት በዚህ መንገድ ተወልዶ ያደገ በኢትዮጵያ እንዲሁም በአፍሪካ የመጀመሪያዉ ነዉ የሚሆነዉ። ይህ ደግሞ የእግዚአብሔር ስራ ነዉ ።

ቤተሰብ:- ሆስፒታሉ ከመጀመሪያዉ ቀን ወደ ማህፀን እና ፅንስ ክፍል በ19ሳምንት እርግዝና በኋላ ከአጋጠማቸዉ አንደኛዉ ልጅ ዉርጃ ጀምሮ ስተደረገላቸዉ እንክብካቤ አመስግነዋል። ህክምናዉም በነፃ በመደረጉ ለልጁ እድገት ከፍተኛ አስተዋፆ እንዳደረገ ተናግረዋል።

የሆስፒታሉ አስተዳደር :-ለዚህ ህፃን ከዚህ መድረስ አስተዋፅዖ ላደረጉት ለማህፀን እና ፅንስ ሀኪሞች :ለህፃናት ስፔሻሊስት ሀኪሞች :ለለጠቅላላ ሀኪሞች :ነርሶች : ሚድዋይፎች :ጥበቃ እና ፅዳት ሰራተኞች ምስጋና አቅርበዋል። ሰርፋክታት ላቀረበልን ድርጅት እና የህክምና ወጭ ለሸፈነዉ BF ምስጋና አቅርበዋል።

ምንጭ_ ሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታል

"ሰብአዊ ተግባር ሕይወት ይታደጋል፤ ብርሀን ይመልሳል!"ሰኔ 7 አለም አቀፍ የደምና የአይን ብሌን ለጋሾች ቀን
14/06/2026

"ሰብአዊ ተግባር ሕይወት ይታደጋል፤ ብርሀን ይመልሳል!"
ሰኔ 7 አለም አቀፍ የደምና የአይን ብሌን ለጋሾች ቀን

ለምግብ አጥረት በሽታ_ Malnutrition  ሕክምና አገልግሎት በሚውሉ ግብዓቶች ዙሪያ ቁጥጥር በማድረግ የዜጎችን ጤና ለመጠበቅ እየሰራ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ።ለ...
14/06/2026

ለምግብ አጥረት በሽታ_ Malnutrition ሕክምና አገልግሎት በሚውሉ ግብዓቶች ዙሪያ ቁጥጥር በማድረግ የዜጎችን ጤና ለመጠበቅ እየሰራ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ።

ለምግብ አጥረት በሽታ_ Malnutrition ሕክምና አገልግሎት የሚዉሉ የፕላምፒኔት እና ፕላምፒሳፕ ግብዓቶች ቁጥጥር ሥራ እየተከናወነ ነው።

ሕይወት አድን አልሚ ግብዓቶች (ፕላምፒኔት እና ፕላምፒሳፕ) ላልተፈለገ ዓላማ እንዳይውሉ ለማድረግና በህገወጥ መንገድ ይዘው እየሸጡ በተገኙ ግለሰቦች ላይ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ የቁጥጥር ቡድኑ አስታውቋል።

በጤና ቢሮ የምግብና መዲሃኒት ቁጥጥር ባለሥልጣን ከእናቶችና ህፃናት፣ ሥርዓተ ምግብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት በጋራ በመቀናጀት የድንገተኛ ቁጥጥር ሥራ በማካሄድ ላይ ይገኛሉ።

ሕይወት አድን አልሚ ግብዓቶች (ፕላምፒኔት እና ፕላምፒሳፕ) ግብዓቶቹ የተገኙባቸው ሱቆች በግብረኃይሉ የታሸጉ ሲሆን፤ እንደየጥፋታቸው አስተዳደራዊ እና ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድባቸውም ታውቋል።

ህብረተሰቡ እንዲህ አይነት ህገወጥ ተግባር የሚያደርጉ ግለሰቦችን እና ሱቆችን በመጠቆም የህፃናትን ህይወት ከሞት ለማዳን ሴክተሩ የሚያደርገውን ጥረት ለማገዝ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ የክልሉ ጤና ቢሮ ጥሪ አቅርቧል።

Address

In Wolaita Development Association Building
S**o
0036

Telephone

+251465512158

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wolayta Zone Health Department /ወላይታ ዞን ጤና መምሪያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share