02/08/2025
የሰሜን ወሎ ዞን አደጋ መከላለልና ምግብ ዋስትና በሃራ ከተማ አስተዳደር ለሚገኙ አቅመ–ደካሞችና መሳኪኖች ከ243,000 ብር በላይ የሚገመት ብረት ድስትና ደብተር ድጋፍ አደረጉ።
የሰሜን ወሎ ዞን አደጋ መከላለልና ምግብ ዋስትና መምሪያ ኃላፊ አቶ አለሙ ይመር Alemu Yimer ይህ ድጋፍ የመጀመሪያችን ሲሆን ወደፊት ኃብት በማፈላለግ በቻልነው ሁሉ በመደገፍ ከጎናችሁ እንሆናለን ብለዋል።140 ብረት ድስት፣ጭልፋ እና 30 ደርዘን ደብተር ከ243,000 ብር በላይ የሚገመት ድጋፍ ማድረጋቸውን ገልፀዋል።
የሰሜን ወሎ ዞን ስፖርት መምሪያ ሃላፊ አቶ አሸናፊ ሰማው Ashenafi Semaw ከሃራ ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ ጋር ንግግር በማድረግ ይህ ድጋፍ ወደ ሃራ እንድመጣ ማድረግ ተችሏል ብለዋል።
ሀላፊው መንግስታችን ድሃ ተኮር ስለሆነ የተቸገሩ ሰዎችን መርዳት ትልቁ አላማው ነው ብሏል።በጎነት ማለት ከተረፈን መስጠት ሳይሆን ካለን ማካፈል ሲሆን ይህ ደግሞ በፈጣሪም በሰውኛ ባህሪም እርካታ የሚሰጥ ተግባር ነው ብለዋል።
የሃራ ከተማ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሪት ጀሚላ ፋሪስ Jemila Farise ባህላችን የሆነውን መረዳዳትና መተባበር ማስቀጠል ይኖርብናል፤የኔ ሆድ ሞልቶ ጎረቤቴ ፆም ማደር የለበትም የሚል መንፈስ ሊያድርብን ይገባል።እኛ ስንተዛዘን አላህም ያዝንልናል፤በእርግጥ ለዚህ በጎ ተግባር ወሎየዎች አይታሙም ብለዋል።
የከተማው ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አህመድ ሞላ Ahmed Molla ስፖርቱን ብቻ ሳይሆን የምናነቃቃው የክረምት በጎ አድራጎት ተግባራትንም ዋነኛ ሚናችን አድርገን እንሰራለን ብለዋል።
« የተቸገሩ ወገኖችን በመርዳት፤አለን ከጎናችሁ እንበል »