Sidama Region Youth Council

Sidama Region Youth Council Voice of Sidama Youth

የአለታ ወንዶ ወረዳ ወጣቶች ምክር ቤት  ስራ አስፈጻሚ አባላት በተለያዩ የስራ ዘርፎች በማህበር ተደራጅተው እየስሩ የሚገኙትን ወጣቶች የማበርታታት ከወጣቶች ጋር የውይይት መርሐ-ግብር  አካሄ...
16/06/2026

የአለታ ወንዶ ወረዳ ወጣቶች ምክር ቤት ስራ አስፈጻሚ አባላት በተለያዩ የስራ ዘርፎች በማህበር ተደራጅተው እየስሩ የሚገኙትን ወጣቶች የማበርታታት ከወጣቶች ጋር የውይይት መርሐ-ግብር አካሄዱ

በዛሬው ዕለት 09/10/2018 ዓ.ም የአለታ ወንዶ ወረዳ ወጣቶች ምክር ቤት ከአለታ ወንዶ ወረዳ ሥራ ፈጠራ፣ አሠሪና ቴክኒክ ልማት ጽሕፈት ቤት ጋር በመተባበር ወጣቶችን በሥራ ዕድል፣ በክህሎት ማሻሻያ እና በተለያዩ የሥራ ዘርፎች ተጠቃሚ የሆኑ ወጣቶችን በመጎብኘት ልምድ የመለዋወጥ መርሃ ግብር አካሂደዋል።

በጉብኝቱ ወቅት በተለያዩ የሥራ መስኮች ተሰማርተው የራሳቸውንና የሌሎችን ሕይወት እየቀየሩ የሚገኙ ወጣቶች ያከናወኗቸውን ተግባራት በቅርብ የመመልከት እና ለሌሎች ወጣቶች ተነሳሽነት የሚፈጥሩ ልምዶችን የመቅሰም እድል ተፈጥሯል።

ወጣቶች በክህሎታቸው በመታገዝ፣ የሥራ ፈጠራ አቅማቸውን በማጎልበት እና የሚገኙ የሥራ ዕድሎችን በመጠቀም ራሳቸውን ተጠቃሚ ከማድረግ ባለፈ ለአካባቢያቸው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከቱ መሆኑ ተገልጿል።

የአለታ ወንዶ ወረዳ ወጣቶች ምክር ቤትም በቀጣይ ወጣቶችን በሥራ ፈጠራ፣ በክህሎት ልማት እና በራስ ሥራ እንዲሰማሩ የሚያበረታቱ ተመሳሳይ መርሃ ግብሮችን እንደሚያጠናክር ገልጿል።

ምንጭ: አለታ ወንዶ ወረዳ ወጣቶች ምክር ቤት

የአለታ ወንዶ ከተማ ወጣቶች ምክር ቤት በበጎ ፈቃድ ሥራ ተሳትፎ አደረገየአለታ ወንዶ ከተማ ወጣቶች ምክር ቤት አባላት ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር በመተባበር የውሃ ፍሰት መንገዶችን በማፅዳትና ...
12/06/2026

የአለታ ወንዶ ከተማ ወጣቶች ምክር ቤት በበጎ ፈቃድ ሥራ ተሳትፎ አደረገ

የአለታ ወንዶ ከተማ ወጣቶች ምክር ቤት አባላት ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር በመተባበር የውሃ ፍሰት መንገዶችን በማፅዳትና በማስተካከል የማህበረሰብ አገልግሎት ሥራ አከናውነዋል።

በተከናወነው ሥራ ወጣቶች የተዘጉ የውሃ መውረጃ ቦዮችን በማፅዳት፣ የጎርፍ አደጋን ለመከላከልና የመንገድ ተጠቃሚዎችን ለማገዝ በንቃት ተሳትፈዋል።

ወጣቶች በአንድነት ሲሰሩ ለማህበረሰቡ ዘላቂ ጥቅም የሚያመጡ በርካታ ለውጦችን ማምጣት እንደሚችሉ ተግባራዊ ማሳያ ሆነዋል።


ኢትዮጵያውያን ወጣቶች በአለም አቀፍ ደረጃ ያላቸውን ሁለንተናዊ ተጽኖ ፈጣሪነት ለማጠናከር ቅንጅታዊ አሰራርን ገቢራዊ ማድረግ ይገባል፤ፕሬዚደንት ፉአድ ገና የኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት ፕሬዚ...
11/06/2026

ኢትዮጵያውያን ወጣቶች በአለም አቀፍ ደረጃ ያላቸውን ሁለንተናዊ ተጽኖ ፈጣሪነት ለማጠናከር ቅንጅታዊ አሰራርን ገቢራዊ ማድረግ ይገባል፤ፕሬዚደንት ፉአድ ገና

የኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት ፕሬዚደንት ፉአድ ገና በሩሲያ ፌዴሬሽን የኢትዮጵያ ኤምባሲን ጎበኙ።

ፕሬዝዳንቱ በጉብኝታቸው በሩሲያ ፌዴሬሽን ከኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ገነት ተሾመ ጋር ተወያይተዋል።

ፕሬዝዳንቱ የኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት እያካሄዳቸው ያሉ ተግባራትን በተመለከተ ለአምባሳደሩ ገለጻ አድርገዋል። ከAll-Russian public-state movement of children and youth, "Movemeng of the first" ጋር የተደረሰውን የትብብር ስምምነት አስመልክቶም ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ውይይቱ በኢትዮጵያና ሩሲያ መካከል ያለውን የወጣቶች ትብብር ለማጠናከር እንዲሁም ለኢትዮጵያ ወጣቶች በወጣቶች መሪነት ልማት፣ በትምህርት፣ በባህላዊ ልውውጥ፣ በስራ ፈጠራ፣ በክህሎት ልማት እና በዓለም አቀፍ የወጣቶች አጋርነት መስኮች እድሎችን ለማስፋፋት ተግባራዊ መንገዶችን በመፈለግ ላይ ያተኮረ ነበር።

ውይይቱ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች በአለም አቀፍ ደረጃ ያላቸውን ተሳትፎ፣ተደማጭነትና ተጽኖ ፈጣሪነት ሁሉን አቀፍ በሆነ መልኩ ለማሳደግ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው።

በተጨማሪ የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲያዊ ተቋማት የወጣቶች ግንኙነትን ለማራመድ፣ ዓለም አቀፍ አጋርነትን ለማጠናከር እና ወጣት መሪዎችን ለማበረታታትና ለማብቃት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይም ምክክር ተደርጓል።

ፕሬዚዳንት ፉአድ ገና በኤምባሲው ለተደረገላቸው አቀባበልና ለነበራቸው ፍሬያማ የውይይት ጊዜ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

የኢ/ወ/ም/ቤት

A meaningful step forward for Ethiopian youth on the global stage.I am truly honored to share that I had the opportunity...
10/06/2026

A meaningful step forward for Ethiopian youth on the global stage.

I am truly honored to share that I had the opportunity to participate in a high-level international engagement in the Russian Federation, where I officially signed a Cooperation Agreement between the Ethiopian Youth Council and the All-Russian public-state movement of children and youth, “Movement of the First,” in the presence of H.E. Ambassador Teshome Genet, Ambassador of Ethiopia to the Russian Federation. The agreement was jointly signed with Mr. Artur Orlov, Chairman of the Board of the All-Russian public-state movement of children and youth “Movement of the First” of the Russian Federation.

Signing this agreement on behalf of Ethiopian youth was more than a formal occasion. It was a proud moment that reflects the growing voice, potential, and global engagement of young people in Ethiopia.

This partnership opens exciting opportunities for cooperation between Ethiopia and Russia in areas including youth leadership, educational and cultural exchange, innovation and entrepreneurship, skills development, peacebuilding initiatives, digital learning, tourism exchange, international networking, and joint youth programs.

Most importantly, this collaboration is about connecting young people beyond borders bringing together ideas, cultures, experiences, and innovations to inspire a generation that is ready to lead, create, and transform the future.

Today’s world demands young people who are globally connected, forward-thinking, and actively engaged in shaping positive change. I strongly believe youth diplomacy and international cooperation are no longer optional; they are essential for building understanding, strengthening partnerships, and creating sustainable opportunities for future generations.

As President of the Ethiopian Youth Council, I remain committed to ensuring Ethiopian youth are represented, empowered, and given access to international platforms that help unlock their full potential.

The future belongs to young people who dare to dream beyond borders, and this is only the beginning.

08/06/2026
06/06/2026
ሰባተኛውን ሀገራዊ  ምርጫ በጠመንጃ ወደ ስልጣን የመምጣትን ምኞት ያጠፋ የሀገራችን ዜጎች ለዲሞክራሲያዊ የስልጣን ሽግግር ያላቸውን ቁርጠኝነት ያሳዩበት ታርካዊ ኩነት ሆኖ ተጠናቋል::ሰባተኛው...
04/06/2026

ሰባተኛውን ሀገራዊ ምርጫ በጠመንጃ ወደ ስልጣን የመምጣትን ምኞት ያጠፋ የሀገራችን ዜጎች ለዲሞክራሲያዊ የስልጣን ሽግግር ያላቸውን ቁርጠኝነት ያሳዩበት ታርካዊ ኩነት ሆኖ ተጠናቋል::

ሰባተኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ፍጹም ፣ ሰላማዊ ፣ዲሞክራሲያዊና ስኬታማ በሆነ መልኩ መጠናቀቁን አስመልክቶ የሲዳማ ክልል ወጣቶች ምክር ቤት ለክልላችን ወጣቶች ምስጋና አቅርበዋል ።

የሲዳማ ክልል ወጣቶች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ወጣት ይስሐቅ ሳንቡሬ በሰጡት መግለጫ 7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ፍጹም ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊና ስኬታማ በሆነ መልኩ እንዲጠናቀቅ መላው የክልላችን ወጣቶች ፣የወጣቶች ምክር ቤት ጠቅላላ አመራሮችና አባላት እንዲሁም የወጣት አደረጃጀቶችን ላደረጉት አስተዋጽኦ በሙሉ የላቀ ምስጋና አቅርበዋል።

ሀገራዊ ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የሲዳማ ክልል ወጣቶች ምክር ቤት በቅድመ ምርጫ ፣በምርጫው ዕለት ፣እንዲሁም በድህረ ምርጫ ወቅት ወጣቶች ንቁ ተሳትፎ እንዲኖራቸው በልዩ ትኩረት የሰራ ሲሆን አሁንም ወጣቶች ሀገርን አሸናፊ በማድረግ ረገድ የሀገር ባለቤቶች በመሆናቸው የራሳቸውን ድርሻ በብቃት የመወጣት ፅኑ ሃላፊነት አላቸው::

የሲዳማ ክልላ ወጣቶች ምክር ቤት የክልላችን ወጣቶች የምርጫ ካርዳቸውን በአግባቡ በመውሰድ የዜግነት መብታቸውን እንዲጠቀሙ በማንቃትና ሌሎች ወጣቶች እንዲሁም ዜጎችን የምርጫው ድምፅ አሰጣጥ ላይ የተለያዩ አማራጭ በመጠቀም በማስተማር በተጨማሪ ተቋማችን ከምርጫ ቦርድ በተሰጠው ይሁንታ በቁጥር 750 የምክር ቤቱ ወክል ታዛቢዎች እንዲሁም ከ100 በላይ አስተባባሪዎች በማሰማራት የምርጫ ሂደት ተዟዙረዉ ጉብኝት በማድርግ ወጣቶች ድምፅ ከመስጠት የዘለለ ምርጫ ፍጹም ፣ ሰላማዊ ዲሞክራሲያዊና ስኬታማ እንዲሆን ተጨማሪ ሃላፊነት መወጣት ተችሏል::

7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሂደቱ ምንም ዓይነት ችግር ሳይገጥመው በሰላም መጠናቀቅ የቻለው የክልላችን ወጣቶች ንቁ ተሳትፎ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅትና በቅርበት በመስራት ለሰላም ቁርጠኛ ርብርብ በማድረግ መሆኑን አብራርተው በተለይም ወጣቱ የምርጫውን ሂደት በባለቤትነት ስሜት በመጠበቅና ለሰላም ቅድሚያ በመስጠት ላሳየው ብስለት ልባዊ ምስጋና ይገባቸዋል።

በመቀጠልም ለቀጣይ አምስት አመታት ሀገርቱን ለመምራት ከህዝብ ይሁንታ የሚያገኘው ማንም ይሁን ማንም ውጤቱን ወጣቶች በፀጋ በመቀበል የሀገርቱን የዜጎችን ሰላም በማፅናት አኳያ የጎላ ርብርብ ማድረግ ይጠበቃል።

በመጨረሻም ምርጫው በተሳካ ሁኔታ እንዲካሄድ በሁሉም መስክ አስተዋጽኦ ያደረጉ መላው የክልላችን ወጣቶች በየደረጃ ያሉ የወጣቶች ምክር ቤት አመራሮችና አባላቶች ፣የወጣቶች ምክር ቤት ወክል ታዛቢዎች፣ አስተባባሪዎች ጠቅላላ የወጣቶች አደረጃጀቶች የተሰጣቸውን ትልቅ አደራ በመወጣት ምርጫውን በስኬት ስላጠናቀቁ ምስጋና አቅርበዋል ።

02/06/2026
01/06/2026

Address

Hawassa
Hawassa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sidama Region Youth Council posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share