በሀዋሳ ከተማ የምስራቅ ክ/ከተማ ወጣቶች ማህበር ቅ/ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Hawassa
  • በሀዋሳ ከተማ የምስራቅ ክ/ከተማ ወጣቶች ማህበር ቅ/ጽ/ቤት

በሀዋሳ ከተማ የምስራቅ ክ/ከተማ ወጣቶች ማህበር ቅ/ጽ/ቤት Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from በሀዋሳ ከተማ የምስራቅ ክ/ከተማ ወጣቶች ማህበር ቅ/ጽ/ቤት, Youth Organization, Hawassa, Hawassa.

11/04/2026

ውድ የሲዳማ ክልል ወጣቶች እና መላው የክርስትና እምነት ተከታዮች፣ እንኳን ለትንሣኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ። የትንሣኤ በዓል የአዲስ ጅምር፣ የተስፋ እና የድል ምልክት ሲሆን ይህ በዓል በተለይም ለወጣቶች አዲስ እድሎችን ለመፍጠር፣ በፈጠራ ሀሳብ ለመንቀሳቀስ እና ለማህበረሰብ ልማት ተግባራዊ ሚና ለመወጣት የሚያነሳሳ መንፈሳዊ እሴት አለው።

በዚህ የትንሣኤ ወቅት ወጣቶች የሰላም፣ የአንድነት እና የመተሳሰብ እሴቶችን በማጠናከር ለማህበረሰባችን ተስፋ የሚሆኑ ተግባራትን እንድንፈጽም፤ ወጣቶች የዛሬ ኃይል እና የነገ ተስፋ እንደመሆናችን በሰላም ግንባታ፣ በልማት ስራዎች እና በማህበራዊ አብሮነት ውስጥ ያለንን ሚና እንድንወጣ በዚህ አጋጣሚ ጥሪዬን አቀርባለሁ።

ይህ የትንሣኤ በዓል ለሁላችን አዲስ ተስፋ፣ ሰላም፣ ፍቅር እና ስኬት ያምጣልን። በአንድነት ቆመን የክልላችንን እና የሀገራችንን ብሩህ ተስፋ ወደፊት እንገንባ።

እንኳን አደረሳችሁ!
መልካም የትንሣኤ በዓል!

ወጣት በቃሉ መሠረት
የሲዳማ ክልል ወጣቶች ማህበር ፕሬዝዳንት

በሀዋሳ ከተማ ምስራቅ ክፍለ ከተማ ተምሳሌት የወጣቶች በጎ አድራጎት ማህበር በ "እኔም_የድርሻዬን" ቻሌንጅ ስር የተሰበሰበ ድጋፍ ለአቅመ ደካማ አረጋዊያንና አካል ጉዳተኞች ተበረከተ።በሀዋሳ ...
11/04/2026

በሀዋሳ ከተማ ምስራቅ ክፍለ ከተማ ተምሳሌት የወጣቶች በጎ አድራጎት ማህበር በ "እኔም_የድርሻዬን" ቻሌንጅ ስር የተሰበሰበ ድጋፍ ለአቅመ ደካማ አረጋዊያንና አካል ጉዳተኞች ተበረከተ።

በሀዋሳ ከተማ ምስራቅ ክፍለ ከተማ አስተዳደር በተምሳሌት የወጣቶች በጎ አድራጎት ማህበር፣ በ "እኔም_የድርሻዬን" ቻሌንጅ ስር በማህበራዊ ሚዲያ በተደረገ ማስተባበር የተሰበሰበ ድጋፍ ለአቅመ ደካማ አረጋዊያንና አካል ጉዳተኞች አድርሷል።

በዚሁ ወቅት አቶ ማራዶና ዘለቀ በመልዕክታቸው ኢትዮጵያዊያን በበጎ ትብብር የሚታወቁ ሕዝቦች መሆናቸውን ገልጸው፣ ከጊዜ በኋላ የደበዘዘውን ይህን በጎ ተግባር በዶ/ር አብይ አህመድ አነሳሽነት ዳግም በተጠናከረ ሁኔታ መቀጠሉን ገልጸዋል። እንደ አቶ ማራዶና ገለፃ የብልጽግና ፓርቲ እና ፓርቲው የሚመራው መንግስት ከሀገር አቀፍ እስከ አካባቢ ድረስ በሰው ተኮር ተግባራት ዘርፈ ብዙ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ጠቁመዋል።

በተጨማሪም ተምሳሌት የበጎ አድራጎት ማህበር በሀዋሳ ከተማ በህፃናት ምገባ እና በአረጋዊያን ድጋፍ እያከናወነ ያለው ስራ አበረታች መሆኑን ገልጸው፣ ለማህበሩ ስራዎች ዘለቂነት ሁሉም አካል ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።

በዚህም መሰረት የአስቤዛ ድጋፍ እና የቅርጫ ስጋ ወይፈን በመስጠት የአብሮነትና የርህራሄ እሴቶች በተግባር ተገልጿል።

በፕሮግራሙ ላይ የሀዋሳ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ማራዶና ዘለቀ፣ የከተማው መምሪያ ሀላፊዎች፣ የምስራቅ ክፍለ ከተማ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጴጥሮስ ቤጤላ እና የክፍለ ከተማው ካቢኔ አባላት እንዲሁም ድጋፍ አድራጊዎች ተገኝተው ፕሮግራሙን አክብረዋል።

07/04/2026
27/03/2026
‎ ‎‎“ትንሽ ርህራሄ… ለእነሱ ግን ሕይወት ነው።”‎‎አንድ አረጋዊ እጅ በመዘርጋት‎“ልጄ… እንደገና ትመጣላችሁ?” ብሎ ሲጠይቅ‎ልብ አይሰበርም?…‎ለእኛ ቀላል የሆነው‎ለእነሱ ግን የቀን ተስ...
20/03/2026



‎“ትንሽ ርህራሄ… ለእነሱ ግን ሕይወት ነው።”

‎አንድ አረጋዊ እጅ በመዘርጋት
‎“ልጄ… እንደገና ትመጣላችሁ?” ብሎ ሲጠይቅ
‎ልብ አይሰበርም?…
‎ለእኛ ቀላል የሆነው
‎ለእነሱ ግን የቀን ተስፋ ነው።

‎ላለፉት 4 ዓመታት ከናተ ደጋግ ሰዎች ጋር በመሆን ቻሌጅ በመክፈት የምግብ እና የአስቤዛ ድጋፍ የቅርጫ ስጋ በጋራ በመተባበር ብዙ አረጋዊያንን አስደስተናል።

‎ስለዚ
‎ዛሬም እነሱ በመንገድ አይናቸውን አንስተው
‎“ይመጣሉ…” ብለው እየጠበቁ ነው።

‎እኛ ካልመጣን…
‎ያ ተስፋ ይቀራል።
‎ያ ፈገግታ ይጠፋል።
‎👉 እባክህ… እጅህን አክል
‎👉 እባክሽ… አብረን እንሁን
‎ዛሬ የምትሰጠው ትንሽ ነገር
‎ለአንድ አረጋዊ ተስፋን ያለመልማል

‎በድጋፉ መሳተፍ ለምትፈልጉ:-

‎📞 ለበለጠ መረጃ:
‎0916 116705 | 0941 015804 | 0916 868339

‎🏦 CBE: 1000 738 988 168
‎ተምሳሌት የወጣቶች በጎ አድራጎት ማህበር


14/03/2026

Ayiide Cambalaalla!

Ayiiraddu sidaamu daga gobbate giddonna gobbaanni heedhinanniri hatono ayiiraddu wedellu hawalle sidaamu daga diru soorro ayyaani fichee cambalaallate keerunni iillishi'ne .Kuni ayyaani mittimmanna baxille kaajjishshanno ayyaanaati.konni ayyaanira daganke haaro diru soorro ayyaani adhatenni mitttimanke kaajjishanno .

Fichee cambalaalla sidaamu daga xaggenna ayiimma xawissanno ayyaana ikkasinni,wedellu gedeno konne dona agaranna dagganno ilamara sayisa ninke qeechati.Wedellu budu aana jawa illacha tugatenni mittimmateninna mimmitu ledo ayirisamatennina irkisamatenni konne ayyaana iibadu garinni ayirisanno gede sokka'ya sayiseemmo.

Ledoteno fichee cambalaallate ayyaani keere duduwa,kaa'lamatenna latishshu sokka sayiisemmo jawa ayyaanaati.konnirano wedellinkera qoqqowinkenna gobbanke keerinna lopho giddo noonsa qeecha hedatenni mittimmatenni loose lopha suffanno gede jawaachinsheemmo.Jeefoteno xaphooma sidaamu daganna wedellu hawalle fichee cambalaallate ayyaanira keerunni iillishi'ne.Kuni haaru diri baalunkura keerunniha lopho abbannoha ikkonke.

Dancha Fichee Cambalaallate Ayyaana!

Beqaalu Meseret
Sidaamu Qoqqowi Wedellu Maamari pirezidaante

የፊቼ ጨምበላላ በዓል መግለጫ
ከሲዳማ ክልል ወጣቶች ማህበር ፕሬዝዳንት

ውድ የሲዳማ ህዝብ በሀገር ውስጥና በውጭ፣ በተለይም ውድ ወጣቶች፤ እንኳን ለሲዳማ ብሔር የዘመን መለወጫ ታላቅ ባህላዊ በዓል ፊቼ ጨምበላላ በሰላምና በደስታ አደረሳችሁ። ይህ በዓል የአንድነት፣ የፍቅር፣ የመተሳሰብ እና የአብሮነት እሴቶችን የሚያጠናክር ልዩ ባህላዊ ትውፊታችን ነው። በዚህ በዓል ላይ ህዝባችን አዲስ ዓመትን በመቀበል አንድነታችንን ያጎለብታል፣ ወገናዊ ግንኙነቶችንም ያጠናክራል።

ፊቼ ጨምበላላ የሲዳማ ህዝብ ታሪክና ማንነት የሚያንጸባርቅ በዓል ሲሆን፣ እንደ ወጣቶች ትውልድ ይህን ቅርስ መጠበቅና ለሚቀጥለው ትውልድ ማስተላለፍ የእኛ ሀላፊነት ነው። ወጣቶች በባህላችን ላይ ትልቅ ኩራት በማድረግ በአንድነትና በእርስ በእርስ መከባበር እና መደጋገፍ መንፈስ ይህን በዓል በደመቀ መልኩ እንድናከብር ጥሪዬን አቀርባለሁ።

በተጨማሪም ፊቼ ጨምበላላ በዓል የሰላም፣ የመተባበርና የልማት መልዕክት የሚያስተላልፍ ታላቅ ዕድል ነው። ስለዚህ ወጣቶች በክልላችን እና በሀገራችን ሰላምና እድገት ውስጥ ያላቸውን ሚና በመገንዘብ በአንድነት መስራት እንዲቀጥሉ እናበረታታለን።

በድጋሚ ለሁሉም የሲዳማ ህዝብ እና ለወጣቶች በተለይ እንኳን ለፊቼ ጨምበላላ በዓል አደረሳችሁ። ይህ አዲሱ ዘመን ለሁላችንም ሰላም፣ እድገት፣ አንድነትና ብልጽግና የሚያመጣ ይሁን።

መልካም የፊቼ ጨምበላላ በዓል!

በቃሉ መሰረት
የሲዳማ ክልል ወጣቶች ማህበር
ፕሬዝዳንት

02/03/2026
01/03/2026

🇪🇹 የአድዋ ድል በዓል እና ለወጣቶች ያለው ትርጉሙ 🇪🇹

የአድዋ ድል በዓል የነፃነት፣ የአንድነት እና የመንፈሳዊ ጽናት ምልክት ነው። ሕዝቦች በተባበረ ኃይል ሀገራችንን ኢትዮጵያ ከቅኝ ግዛት አዳኑ።

👉 ለወጣቶች የሚያስተምረው፦
• አንድነት ከልዩነት በላይ መሆኑን
• በዕውቀት፣ በጥረት እና በጽናት መተባበር
• የሀገር ልማት እና ሰላም ለመገንባት ራስን መስጠት

ዛሬ የአድዋን መንፈስ በመውሰድ ወጣቶች በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊ እና በኢንተርፕረነርሺፕ መስኮች የሀገራችንን ወደፊት መገንባት ይገባናል።

✊ እኛ እንደ ሲዳማ ክልል ወጣቶች ማህበር ወጣቶችን እንዲተባበሩ እና የአድዋን መንፈስ እንዲቀጥሉ እንሰራለን።

አድዋ ድል ነው – አድዋ መንፈስ ነው – አድዋ ኃይል ነው!

Address

Hawassa
Hawassa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በሀዋሳ ከተማ የምስራቅ ክ/ከተማ ወጣቶች ማህበር ቅ/ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share