11/04/2025
ጎንደር ከተማ ንግድና ዘርፍ ማ/ም/ቤት ከIHK Reutlingen ጋር በመተባበር 2025 ዓ/ም የሃኖቨር የንግድ ትርኢት፣ ኤግዚቢሽንና ባዛር ከመጋቢት 22 እስከ መጋቢት 26 / 2017 ዓ/ም ወይም እ.ኤ.አ March 31 – April 4 ድረስ ለተከታታይ 5 ቀናት በጀርመን ሃገር ሃኖቨር ከተማ ተካሄዷል፡፡
በዚህ የንግድ ትርዒት፣ ኤገዚቢሽንና ባዘር የኢንዳስትሪና የሎጅስቲክ ምርቶች የተዋወቁበት ሲሆን የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ጠቀሜታ፣ የ5G ኔትወርክ መስፋፋት ለቴክኖሎጂ መስፋፋት ያለው ጠቀሜታ፣ ሌሎች የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ለዓለም የንግድ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ በሚል የተዘጋጀ ሲሆን ከተለያዩ የዓለም ሃገራት የመጡ አምራቾች፣አገልግሎት ሰጪዎች፣ አስመጪና ላኪዎች፣ አከፋፋዮችና ጅምላ ነጋዴዎች ተሳትፈዋል፡፡
በዚህ ዝግጅት ምክር ቤታችን የጎንደር ከተማ ንግድና ዘርፍ ማ/ም/ቤት ከአጋራችን ከIHK Reutlingen ጋር በመተባበር አባሎቻቸንን ለማሳተፍ ችለናል፡፡ በዚህም ሳንወሰን ይህንን መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ሌሎች የሃገራችን ንግድ ምክር ቤቶች (ኦሮሚያ ንግድና ዘርፍ ማ/ም/ቤት እና መቀሌ ንግድና ዘርፍ ማ/ም/ቤት) አባሎቻቸውን እንዲሳትፉ በማድረግ ተጠናቋል፡፡ ይምጡ አባላችን ይሁኑ።