ERCS - Gedeo Zone Branch

ERCS - Gedeo Zone Branch Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ERCS - Gedeo Zone Branch, Non-Governmental Organization (NGO), Dilla Town, Dilla.

ይህ የጌዴኦ ዞ/ቀይ መስቀል ቅ/ጽ/ቤት ትክክለኛ የፌስቡክ ገጹ ነው።በገጹም ስለ ቅ/ጽ/ቤት አጠቃላይ መረጃዎችን ፣ ትምህርቴ መስቀል ፣ ማስታወቂያዎች ፣ ሰብዓዊ ስራዎች ማግኘት ይችላል።
ስልክ:- +251909145440/Gedeozoneredcross(Tg)
Email:- [email protected] ማግኘት ይችላሉ።
አድራሻ:- ዲላ ከተማ ፣ ማሞ ኮሞልቻ አደባባይ ከፍ ብሎ

የቀይ መስቀልና የቀይ ጨረቃ መሠረታዊ መርህዎች           ...የቀጠለ...6.  #አንድነት🖌 በአንድ ሀገር ሊኖር የሚችለው   ወይም   ብሔራዊ ማኅበር ብቻ ነው፡፡ 🖊 ይህ ማኅበር ለማን...
31/05/2026

የቀይ መስቀልና የቀይ ጨረቃ መሠረታዊ መርህዎች
...የቀጠለ...
6. #አንድነት
🖌 በአንድ ሀገር ሊኖር የሚችለው ወይም ብሔራዊ ማኅበር ብቻ ነው፡፡

🖊 ይህ ማኅበር ለማንኛውም ዜጋ ለስራ እና ለአባልነት ክፍት ሲሆን ፤ አገልግሎቱንም በሀገሪቱ ውስጥ በሁሉም አካባቢዎች ማዳረስ አለበት:: አንድ ብሔራዊ ማኅበር።

❖ ለሁሉም ክፍት መደረግ አለበት፣
❖ በመላ ሀገሪቱም መስራት ይጠበቅበታል፡፡

7.

🖍 የቀይ መስቀልና ቀይ ጨረቃ እንቅስቃሴ ብሔራዊ ማኅበራት ሁሉ በእኩልነት መብትና የኃላፊነት መንፈስ እርስ በርሳቸው የሚረዳዱበት ዓለም አቀፋዊ ተቋም ነው፡፡

❖ እንቅስቃሴው ዓለም ዓቀፋዊ ነው፡፡
❖ ሁሉም ብሔራዊ ማኅበራት በእንቅስቃሴው ወሳኝ አካላት (governing bodies) እኩል ድምጽ ይኖራቸዋል፡፡

🖋 የእንቅስቃሴው መሰረታዊ መርሆዎች እርስ በርስ የሚገናኙ ፤ አንዱ ለሌላው መሰረት የሆኑና ሁሉም የእንቅስቃሴው አካላት በጋራ ኃላፊነት የሚያከብሩዋቸው ናቸው፡፡

ለምሳሌ እንቅስቃሴው ነጻነቱን ማስጠበቅ ካልቻለ በገለልተኝነት እና ባለማዳላት ተግባሩን ማከናወን አይችልም፡፡

🔹 የመሰረታዊ መርሆዎች በአንዱ የእንቅስቃሴው አካል አለመከበር ሌሎችንም የእንቅስቃሴው አካላት የሚጎዳና በተለይም በግጭትና ጦርነት ወቅት ለአደጋ የሚያጋልጥ ነው።
ERCS - Gedeo Zone Branch

የERCS - Gedeo Zone Branch  ስለ ቀይ መስቀልና ስለ ቀይ ጨረቃ ማህበር እንዲያውቅ ፣  የማህበሩን ዓላማ አውቆ ማህበሩን እንዲደግፍ ፣ የቅ/ጽ/ቤት ተግባራቶችንና ስራዎችን እንድ...
30/05/2026

የERCS - Gedeo Zone Branch ስለ ቀይ መስቀልና ስለ ቀይ ጨረቃ ማህበር እንዲያውቅ ፣ የማህበሩን ዓላማ አውቆ ማህበሩን እንዲደግፍ ፣ የቅ/ጽ/ቤት ተግባራቶችንና ስራዎችን እንድከታተል ፣ እንዲደግፍ ፣ ትምህርቴ ቀይ መስቀል እንድማር ፣ ተምረው ስለተቋሙ እንዲያውቅ የተለያዩ የሚዲያ አማራጮችን እየተጠቀመ ይገኛል።

ስለዚህ ይህንን የፌስቡክ ገጻችን follow በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
https://www.facebook.com/gedeozonebranch
ERCS - Gedeo Zone Branch

30/05/2026

ለሰብዓዊነት እንኖራለን!

            ...የቀጠለ...4.  #ነፃነት (ተቋማዊና የአሰራር ነጻነት)✔️ እንቅስቃሴው የሥራ አፈፃፀም ነፃነት አለው:: ብሔራዊ ማኅበራት ለየሀገሮቻቸው ሕጎች ተገዥ በመሆን መንግስት...
30/05/2026


...የቀጠለ...
4. #ነፃነት (ተቋማዊና የአሰራር ነጻነት)
✔️ እንቅስቃሴው የሥራ አፈፃፀም ነፃነት አለው:: ብሔራዊ ማኅበራት ለየሀገሮቻቸው ሕጎች ተገዥ በመሆን መንግስት ለሚያበረክታቸው ሰብአዊ አገልገሎት አጋዥ (ረዳት) አካላት ናቸው።

ይሁን እንጂ በቀይ መስቀልና ቀይ ጨረቃ መርሆዎች መሠረት ብሔራዊ ማኅበራት ተግባራቸውን ለማከናዎን እንዲችሉ ሙሉ የሥራ አፈፃፀም ነፃነት አላቸው::

በዚህ መርሀ መሰረት እንቅስቃሴው፡-

🖊በሥራ አፈጻጸሙ ነፃ ነው፣
🖍የሀገሪቱን ሕግ ያከብራል፣
🖊በማንኛውም አካል ተፅዕኖ አይደረግበትም።
🖌 እንቅስቃሴው ነጻ ነው ሲባል ሁሉም የእንቅስቃሴው አካላት የራሳቸው ነጻነት ያላቸውና በራሳቸው የሚመሩ መሆናቸውንም ያጠቃልላል።

በመንግስታትም ይሁን በሌላ በየትኛውም አካል ተፅዕኖ ሊደረግባቸው አይገባም::

✔️ የእንቅስቃሴው እካላትም እርስ በርሳቸው በሚኖራቸው ግንኙነት ነጻነታቸውን ማክበር አለባቸው።

ለምሳሌ ብሄራዊ ማኅበራትም ሆኑ የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ በፌደሬሽን ላይ ጫና ሊያሳድሩበት አይችሉም፡፡

የብሄራዊ ማኅበራትም የየሀገራቸው የመንግስት አጋዥ ቢሆኑም በመሰረታዊ መርሆዎች ብቻ በመመራት ስራቸውን ማከናወን አለባቸው።

የሚያከናውኑት ተግባር ከእንቅስቃሴው መሰረታዊ መርሆዎች ጋር የማይቃረን መሆኑን ማረጋገጥ አለባቸው። የአሰራር ነጻነታቸውን ለማስከበር ሲባል ሁሉም ብሄራዊ ማኅበራት በነጻነት የሚመረጥ አመራር (ቦርድ) አላቸው።

የነጻነት መርሀ ሁሉም የእንቅስቃሴው አካላት ተረጂዎችን በቀጥታ ማነጋገር እንዲሁም የደረሰውን ጉዳት በሚመለከት የራሳቸውን ዳሰሳ (ጥናት) ማድረግ ይችላሉ።

5. የበጎ ፈቃድ አገልግሎት

🖌 የቀይ መስቀልና ቀይ ጨረቃ እንቅስቃሴ በምንም ዓይነት #ለትርፍ ያልተቋቋመ ፣ ብቻ #ተነሳስቶ በችግር ላይ ያሉ ሰዎችን የሚረዳ ሰብዓዊ ድርጅት (እንቅስቃሴ) ነው::

በዚህም መሰረት እንቅስቃሴው፡-
❖ የበጎ-ፈቃድ ሰብዓዊ አገልግሎት ያበረክታል፣
❖ ትርፍ የማግኘት ዝንባሌ/ዓላማ አይኖረውም፡፡

🖍🖍 ከዚህ መርህ አንፃር በእንቅስቃሴው የሚሰጡ አገልግሎቶች በሙሉ በፍቃደኝነት የሚሰጡ ናቸው፡፡

ብሄራዊ ማኅበራትም በፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተ በሰብአዊ ተግባራት የመንግስት አጋዥ ወይም ደጋፊ በመሆን ይሰራሉ፡፡

29/05/2026
29/05/2026
We Live for Humanity❗️
29/05/2026

We Live for Humanity❗️

ማኅበሩ በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን በግጭት ለተፈናቀሉ ወገኖች የሰብዓዊ ድጋፍ አደረገበኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የአማራ ክልል ቅርንጫፍ በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን በቻግኒ እና በ...
27/05/2026

ማኅበሩ በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን በግጭት ለተፈናቀሉ ወገኖች የሰብዓዊ ድጋፍ አደረገ

በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የአማራ ክልል ቅርንጫፍ በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን በቻግኒ እና በአይሁ ጋጉሳ ወረዳዎች ለተፈናቀሉ ማኅበረሰቦች የሰብዓዊ ድጋፍ አድርጓል።

ድጋፉ ከቀያቸው ለተፈናቀሉ ቤተሰቦች አስቸኳይ ፍላጎቶቻቸውን ለማሟላት፣ እንዲሁም በዚህ ፈታኝ ወቅት ጤንነታቸውን፣ ደህንነታቸውን እና ክብራቸውን ለመጠበቅ የሚያስፈልጉ መሰረታዊ ነገሮችን ለማቅረብ ያለመ ነው።

ድጋፉ ከእንግሊዝ መንግስት የውጭ ጉዳይ ልማት ቢሮ (FCDO) በ Ec2R ፕሮጀክት አማካኝነት የተገኘ ሲሆን ድጋፉም ለ500 አባወራዎች ተበርክቷል።

ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በግጭት ለተጎዱ ማኅበረሰቦች የሰብዓዊ ድጋፍ አደረገበኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር  የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በሲዳማ ክልል ጭሬ፣ አሮሬሳ እና ሆኮ ወረዳዎች እና በምዕ...
25/05/2026

ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በግጭት ለተጎዱ ማኅበረሰቦች የሰብዓዊ ድጋፍ አደረገ

በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በሲዳማ ክልል ጭሬ፣ አሮሬሳ እና ሆኮ ወረዳዎች እና በምዕራብ ጉጂ ዞን ሃራንፋማ ወረዳ በተፈጠረው ግጭት ለተጎዱ ማኅበረሰቦች ከግንቦት 22-24 ቀን 2026 ሰብዓዊ ድጋፍ አድርጓል።

Address

Dilla Town
Dilla

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ERCS - Gedeo Zone Branch posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share