31/05/2026
የቀይ መስቀልና የቀይ ጨረቃ መሠረታዊ መርህዎች
...የቀጠለ...
6. #አንድነት
🖌 በአንድ ሀገር ሊኖር የሚችለው ወይም ብሔራዊ ማኅበር ብቻ ነው፡፡
🖊 ይህ ማኅበር ለማንኛውም ዜጋ ለስራ እና ለአባልነት ክፍት ሲሆን ፤ አገልግሎቱንም በሀገሪቱ ውስጥ በሁሉም አካባቢዎች ማዳረስ አለበት:: አንድ ብሔራዊ ማኅበር።
❖ ለሁሉም ክፍት መደረግ አለበት፣
❖ በመላ ሀገሪቱም መስራት ይጠበቅበታል፡፡
7.
🖍 የቀይ መስቀልና ቀይ ጨረቃ እንቅስቃሴ ብሔራዊ ማኅበራት ሁሉ በእኩልነት መብትና የኃላፊነት መንፈስ እርስ በርሳቸው የሚረዳዱበት ዓለም አቀፋዊ ተቋም ነው፡፡
❖ እንቅስቃሴው ዓለም ዓቀፋዊ ነው፡፡
❖ ሁሉም ብሔራዊ ማኅበራት በእንቅስቃሴው ወሳኝ አካላት (governing bodies) እኩል ድምጽ ይኖራቸዋል፡፡
🖋 የእንቅስቃሴው መሰረታዊ መርሆዎች እርስ በርስ የሚገናኙ ፤ አንዱ ለሌላው መሰረት የሆኑና ሁሉም የእንቅስቃሴው አካላት በጋራ ኃላፊነት የሚያከብሩዋቸው ናቸው፡፡
ለምሳሌ እንቅስቃሴው ነጻነቱን ማስጠበቅ ካልቻለ በገለልተኝነት እና ባለማዳላት ተግባሩን ማከናወን አይችልም፡፡
🔹 የመሰረታዊ መርሆዎች በአንዱ የእንቅስቃሴው አካል አለመከበር ሌሎችንም የእንቅስቃሴው አካላት የሚጎዳና በተለይም በግጭትና ጦርነት ወቅት ለአደጋ የሚያጋልጥ ነው።
ERCS - Gedeo Zone Branch