ኢትዮጲያዊነት የበጎ አድራጎት ማህበር ዲላ

  • Home
  • Ethiopia
  • Dilla
  • ኢትዮጲያዊነት የበጎ አድራጎት ማህበር ዲላ

ኢትዮጲያዊነት የበጎ አድራጎት ማህበር ዲላ ዘር ቀለም ሀይማኖት ሳንመርጥ ሰውን በሰውነቱ ብቻ እንርዳ

መኖራችን የሚሰማን ለሌሎች ስንኖር ነው 💚💛❤️

ኢትዮጵያዊነት የበጎ አድራጎት ማህበር ዲላ

በሀገራችን የተለያዩ ቦታዎች ማህበራዊ ድጋፍ የሚሹ በሚልዮን የሚቆጠሩ የማህበረሰብ ክፍሎች እንዳሉ ይታወቃል። ምንም እንኳን አባይን በማንኪያ መጨለፍ ቢመስልም ይህንን ማህበራዊ ችግር ሁላችንም የተቻለንን በማድረግ መቅረፍ ይቻላል ብለን በዲላና አካባቢዋ ባሉ ቅን እና የመልካም ልብ ባለቤት ወጣቶች ይህንን ማህበር በ2012 ዓም የመሰረትን ሲሆን ዘር፣ ብሄር፣ ሀይማኖት እና ቦታ ሳይገድበው በኢትዮጵያዊነት ኢትዮጵያውያንን የሚረዳ ነው

ከማህበራችን ዘርፈ ብዙ ስራዎች መካከል:-

በዲላ እና በአካባቢው የሚገኙ ጧሪ የሌላቸውን አረጋውያን፣ አካል ጉዳተኞች ፣ በከፊል በጎዳና ያሉ ወገኖችን፣ ታ

ራሚዎችን፣ በሆስፒታል እና ቤታቸው ተኝተው የሚታከሙ እና ሌሎች የማህበሩን እገዛ ለሚፈልጉ ሁሉ
፟- ቤት ማደስ፣ ህክምና እንዲያገኙ ማድረግ፣ ማስታመም፣ ንፅህና መጠበቂያዎችን ማደል፣ ማጠብ
- የወር አስቤዛ መስጠት፣ በየቀኑ ምግብ ማደል፣የቤት ክራይ መክፈል፣ በዓላትን ከአረጋውያን እና ከጎዳና ተዳዳሪዎች ጋር ማሳለፍ፣
- በተለያየ ምክንያት ወደጎዳና የወጡ ልጆችን ወደቤተሰባቸው እንዲመለሱ እና ባሉበት እገዛ እንዲያገኙ ማድረግ፣ የአልባሳት እና የተለያዩ ቁሳቁሶች ድጋፍ ማድረግ እና
-ሌሎች ያልተጠቀሱ እገዛዎችን ማድረግ
አላማችሁ አላማችን ነው ብላችሁ ከጎናችን እንደምትሆን ተስፋ እናደርጋለን

በጉልበት፣ በሀሳብ፣ ገንዘብ እንዲሁም በቁሳቁስ ማገዝ ለምትሹ:-
+251936450843 ነብዩ
+251976060511 ማስተዋል
0461312600 የቢሮ
እንዲሁም በንግድ ባንክ አካውንታችን 1000342158707( ኢትዮጵያዊነት የበጎ አድራጎት ማህበር) የቻላችሁትን መላክ ወይም ማስገባት ትችላላችሁ

“ መኖራችን የሚሰማን ለሌሎች ስንኖር ነው ”

10/05/2026

☕️ የፍቅር እና የክብር ቀን በዲላ
​ዛሬ በዲላ በኢትዮጵያዊነት ቢሮ የእናቶች ቀንን ስናከብር ከምንም በላይ የደመቀው የእናቶቻችን ፈገግታ ነበር።
​የቡና ቁርስ፦ በባህላዊው የቡና ስነ-ስርዓት ተባርከን፣ አብረን ኬክ በመቁረስ ደስታችንን ገልጸናል።
​የክብር ነጠላ፦ ለእነዚህ ባለውለታ እናቶቻችን ነጠላ በማልበስ ያለንን ጥልቅ ፍቅርና አክብሮት በጋራ አሳይተናል።
​እናቶች የቤታችን መሠረት፣ የማህበረሰባችንም ምሶሶ ናቸው። እናቶቻችንን ማክበር ኢትዮጵያዊነታችንን ማክበር ነው።

10/05/2026
"ቡና ጠጡ" ከእናቶቻችን ጋር! ☕️🌸​እኛ በኢትዮጵያዊነት የበጎ አድራጎት ማህበር በየሳምንቱ እናቶቻችንን ተሰብስበን  በጋራ "ቡና ጠጡ" የምንልበትና የምንወያይበት የተቀደሰ ቀን አለን። ዛሬ...
10/05/2026

"ቡና ጠጡ" ከእናቶቻችን ጋር! ☕️🌸
​እኛ በኢትዮጵያዊነት የበጎ አድራጎት ማህበር በየሳምንቱ እናቶቻችንን ተሰብስበን በጋራ "ቡና ጠጡ" የምንልበትና የምንወያይበት የተቀደሰ ቀን አለን። ዛሬ ግንቦት 2 የሚከበረውን ዓለም አቀፍ የእናቶች ቀን ደግሞ ከወትሮው በተለየ መልኩ ከዚሁ የ"ቡና ጠጡ" ፕሮግራማችን ጋር በማያያዝ በታላቅ ድምቀት በቢሯችን አክብረናል ።

10/05/2026

እናትነት ድንበር የለውም!

​የአንዱ እናት የሁላችንም እናት ናት። የእነርሱ መራብ የኛ ርሀብ የእነርሱ መቸገር የኛም ህመም ነው። ለዚህ ነው ኢትዮጵያዊነት የበጎ አድራጎት ማህበር "ሁሉም እናቶች የኛም እናቶች ናቸው" በሚል መሪ ቃል እናቶችን ለመጠየቅና ለመደገፍ የተነሳው።

10/05/2026

ሁሉም እናቶች የኛም እናቶች ናቸው!

ግንቦት 2 የሚከበረውን ዓለም አቀፍ የእናቶች ቀን ስናስብ በቤታችን ያሉትን እናቶች ብቻ ሳይሆን በከተማችን ጎዳናዎችና በችግር ውስጥ ያሉትን እናቶች ሁሉ በማሰብ ሊሆን ይገባል።
​እናትነት ድንበር የለውም!

መልካም የእናቶች ቀን 💚💛❤️

የጥበብ እና የበጎነት ምሽት​"ጥበብን ለበጎነት፣ በጎነትን ለሰው ልጅ"​የኢትዮጵያዊነት በጎ አድራጎት ማህበር የዲላ ከታላቁ የሩጫ ሳምንት በኋላ የኪነ-ጥበብ ምሽቱን በድጋሚ መጀመሩን በታላቅ ...
09/05/2026

የጥበብ እና የበጎነት ምሽት
​"ጥበብን ለበጎነት፣ በጎነትን ለሰው ልጅ"
​የኢትዮጵያዊነት በጎ አድራጎት ማህበር የዲላ ከታላቁ የሩጫ ሳምንት በኋላ የኪነ-ጥበብ ምሽቱን በድጋሚ መጀመሩን በታላቅ ደስታ ያበስራል። ይህ መድረክ ጥበብን ከመዝናኛነት ባለፈ፣ ማህበረሰባዊ ኃላፊነትን ለመወጣት እና የበጎነትን ባህል በጋራ ለማስረጽ የምንገናኝበት ልዩ መድረክ ነው።
​ቀጠሮ፦ በየሳምንቱ ዓርብ
​ቦታ፦ ቁጥር ሁለት በአቤ ሆቴል

​ኑ! በጥበብ እየተዝናናን፣ ስለ በጎነት እየተወያየን የበጎነት አምባሳደር እንሁን።

06/05/2026

256 likes, 13 comments. “Dila !!! #”

Address

Near Bekele Dilla Hotel
Dilla

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ኢትዮጲያዊነት የበጎ አድራጎት ማህበር ዲላ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to ኢትዮጲያዊነት የበጎ አድራጎት ማህበር ዲላ:

Share