29/04/2026
እዩ-ኢትዮጵያ ነጻ የዓይን ሞራ ቀዶ ህክምና አገልግሎት ሰጠ ::
እዩ-ኢትዮጵያ ከአማራ ክልል ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር በደ/ወሎ ዞን በአርጎባ ልዩ ወረዳ በመዲና ከተማ የዓይን ሞራ ቀዶ ህክምና እና ሌሎች አገልግሎቶችን ሰጥቷል ።
የህክምና አገልግሎቱም የአካባቢው እና አጎራባች ቦታዎች የሚኖሩ የዓይን ሞራ (Cataract)፣ የዓይን ግፊት (Glaucoma) እና ሌሎች መሠል ችግሮች ተጠቂ የሆኑ ማህበረሰቦችን ያካተተ ነበር። የዓይን ቀዶ ህክምና አገልግሎቱም ከ 120 በላይ ሰዎችን ያሳተፈ ሲሆን ከዚህ ዉስጥ ከ38% በላይ የሚሆኑት ሴቶች ሲሆኑ፤ እንዲሁም ሌሎች በዓይን ጠብታዎች ህክምና ከተደረገላቸው 530 ሰዎች መካከል ደግሞ ከ33% በላይ ሚሆኑት የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ሴቶች ነበሩ::
ህክምናውን ያገኙ ታካሚዎችና ቤተሰቦቻቸዉ እይታቸው በመመለሱ በጣም ደስተኛ እንደሆኑ ገልጸው ከዚህ ቀደም ህክምናውን ለማግኘት ቦሮ ሜዳ ድረስ መሄድ እንደሚያስፈልጋቸው ይህን ለማድረግ ደግሞ አቅም እንዲሁም የትራንስፖርት እንግልቱና ወጪ መሸፈን ከባድ እንደሆነባቸው ገልፀዉ ይህ አገልግሎት በወረዳቸው ለመጀመሪያ ጊዜ በቅርብ በማግኘታቸው ደስተኛ እንደሆኑ ገልጸው ለእዩ-ኢትዮጵያ ከፍ ያለ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ።
የሶሻል ሚዲያችን ይቀላቀሉ:-
🌍 Website: www.eyuethiopia.org
🐦 Twitter/X: https://x.com/Eyu_Ethiopia
📘 Facebook: https://web.facebook.com/EyuEthiop/
🔗 LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/eyuethiopia
📢 Telegram: https://t.me/+tPeu-xg9T_w4OTFk
እዩ-ኢትዮጵያ
ለተሻለ እይታ እንሰራለን !