27/05/2026
በነቃ ተሳትፎ የተደራጀ ጥረት ለምርጫችን ስኬት!
በሰሜን ጎጃም ዞን የይልማና ዴንሳ ወረዳ የ7ኛው ሀገረዊ ምርጫ ሰራ በነቃ ተሳትፎ የተደራጀ ጥረት ለምርጫችን ስኬት በሚል መሪ ቃል እና በቀሪ ቀናት የምርጫ ሰራዎች በተመለከተ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው
ግንቦት 19/2018 ዓ.ም ይልማና ዴንሳ ወረዳ ኮሙኒኬሽን
በውይይቱ ላይ የክልል እና የዞን ደጋፊ አመራሮችና የወረዳ ጠቅላላ አመራሩ ተገኝተዋል።
ይህ መድረክ በቀሪዎቹ ቀናት የሚሰሩ ስራዎችን በውጤታማነት ለመምራትና ለላቀ ስኬት ለመዘጋጀት ያለመ መሆኑን የይልማና ዴንሳ ወረዳ የብልፅግና ፖርቲ ቅ /ፅ/ቤት የህዝብ ግንኙነት እና የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ መለሰ ታፈረ ገልፀዋል።
ምርጫው ፍጹም ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ እንዲካሄድና የህዝባችንን የነቃ ተሳትፎ ለማረጋገጥ በቀሩት ጥቂት ቀናት ውስጥ ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡ ዋና ዋና ተግባራት ላይ ያተኮረ ግምገማና የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ላይ በትኩረት ተይዞ መሰራት እንዳለበት ተገልጿል።