Yilmana Densa Communication

Yilmana Densa  Communication በማህበራዊ፣በኢኮኖሚያዊ፣ፖለቲካዊ እና በታሪካዊ ጉዳዮች ወቅታዊ መረጃ ለህዝብ ማድረስ።

በነቃ ተሳትፎ የተደራጀ ጥረት ለምርጫችን ስኬት! በሰሜን ጎጃም ዞን የይልማና ዴንሳ  ወረዳ የ7ኛው ሀገረዊ ምርጫ ሰራ በነቃ ተሳትፎ የተደራጀ  ጥረት ለምርጫችን ስኬት በሚል መሪ ቃል እና በ...
27/05/2026

በነቃ ተሳትፎ የተደራጀ ጥረት ለምርጫችን ስኬት!

በሰሜን ጎጃም ዞን የይልማና ዴንሳ ወረዳ የ7ኛው ሀገረዊ ምርጫ ሰራ በነቃ ተሳትፎ የተደራጀ ጥረት ለምርጫችን ስኬት በሚል መሪ ቃል እና በቀሪ ቀናት የምርጫ ሰራዎች በተመለከተ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው

ግንቦት 19/2018 ዓ.ም ይልማና ዴንሳ ወረዳ ኮሙኒኬሽን

በውይይቱ ላይ የክልል እና የዞን ደጋፊ አመራሮችና የወረዳ ጠቅላላ አመራሩ ተገኝተዋል።

ይህ መድረክ በቀሪዎቹ ቀናት የሚሰሩ ስራዎችን በውጤታማነት ለመምራትና ለላቀ ስኬት ለመዘጋጀት ያለመ መሆኑን የይልማና ዴንሳ ወረዳ የብልፅግና ፖርቲ ቅ /ፅ/ቤት የህዝብ ግንኙነት እና የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ መለሰ ታፈረ ገልፀዋል።

ምርጫው ፍጹም ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ እንዲካሄድና የህዝባችንን የነቃ ተሳትፎ ለማረጋገጥ በቀሩት ጥቂት ቀናት ውስጥ ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡ ዋና ዋና ተግባራት ላይ ያተኮረ ግምገማና የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ላይ በትኩረት ተይዞ መሰራት እንዳለበት ተገልጿል።

እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አል-አደሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ​የአዴት ከተማ አስተዳደር በከተማችንና በዙሪያዋ ለምትገኙ፣ እንዲሁም ለመላው የዕምነቱ ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ14...
27/05/2026

እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አል-አደሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

​የአዴት ከተማ አስተዳደር በከተማችንና በዙሪያዋ ለምትገኙ፣ እንዲሁም ለመላው የዕምነቱ ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አል-አደሃ (አረፋ) በዓል በሰላም፣ በጤና እና በደስታ አደረሳችሁ ይላል።

​የከተማ አስተዳደሩ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ልመንህ ምህረት በዓሉን አስመልክተው ያስተላለፉት መልዕክት፦

የኢድ አል-አደሃ በዓል የታላቁን ነብይ የኢብራሂምን የፅናት፣ የቅንነትና የመታዘዝ ታሪክ የምናስታውስበት፤ ፈጣሪን በመፍራት ለክብር የተሰጠውን ታላቅ መስዋዕትነት የምናስብበት ዕለት ነው። ይህ ዕለት የእርስ በርስ መተሳሰብ፣ መደጋገፍና የመካፈል በዓል ነው።

​የአዴት ከተማ የሙስሊም ማህበረሰብ ከተማችን ከተመሰረተችበት ጊዜ ጀምሮ ለሀገርና ለከተማችን ሁለንተናዊ እድገት፣ ሰላምና ልማት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ የመጣ የሰላምና የፍቅር ማህበረሰብ ነው። የአዴት ሙስሊም ማህበረሰብ ካሉት በርካታ መልካም እሴቶች መካከል፦
• ​የመደጋገፍና የመረዳዳት ባህል፦ አቅም የሌላቸውን ወገኖች በመደገፍ፣ የታረዘውን በማልበስ እና የተራበውን በማብላት የታወቀው የከተማችን ሙስሊም ማህበረሰብ፣ ይህንን በዓል ሲያከብርም የተለመደውን የደግነት እጁን በመዘርጋት እንደሚሆን ሙሉ እምነት አለን።

• ​የአብሮነትና የሰላም ተምሳሌትነት፦ በአዴት ከተማ ለዘመናት የዘለቀውን የሃይማኖቶች መከባበር፣ የወንድማማችነት እና የአብሮነት እሴት ጠብቆ በማቆየት ረገድ የሙስሊሙ ማህበረሰብ ሚና ታሪካዊና የማይተካ ነው።

​በአሁኑ ወቅት ከተማችን አዴት ወደ ላቀ የኢንቨስትመንት፣ የመሰረተ ልማት እና የንግድ እድገት እየተሻገረች ትገኛለች። ይህንን የከተማችንን የብልጽግና ጉዞ ይበልጥ ለማፋጠን የሙስሊሙ ማህበረሰብ እያደረገ ያለው ንቁ ተሳትፎ ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ፅኑ እምነታችን ነው።

​በዓሉን ስናከብር የተቸገሩትን በመጠየቅ፣ የተጣሉትን በማስታረቅ፣ ሰላማችንን እና አንድነታችንን ይበልጥ በማጥበቅ እንዲሆን ጥሪያችንን እያስተላለፍን፤ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የጤና እና የብልጽግና እንዲሆንላችሁ እንመኛለን።

ኢድ ሙባረክ!
ግንቦት 19/2018 ዓም (አዴት ከተማ ኮሙኒኬሽን)

በማከላዊ ጎንደር ዞን ጭልጋ፣ ነባሩ ጭልጋ ወረዳና አይከል ከተማ አስተዳደር 7ተኛውን ሀገራዊ ምርጫ አስመልክቶ  የብልፅግና ፓርቲ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።
26/05/2026

በማከላዊ ጎንደር ዞን ጭልጋ፣ ነባሩ ጭልጋ ወረዳና አይከል ከተማ አስተዳደር 7ተኛውን ሀገራዊ ምርጫ አስመልክቶ የብልፅግና ፓርቲ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።

ኢትዮጵያ በሁለት ታሪካዊ ምዕራፎችሀገራችን ኢትዮጵያ በሁለት ወሳኝ ታሪካዊ ምዕራፎች ውስጥ ትገኛለች። በአንድ በኩል ሁሉንም የኢኮኖሚ አቅሞችና ዘርፈ ብዙ አማራጮች አሟጣ በመጠቀም ብልጽግናዋን...
26/05/2026

ኢትዮጵያ በሁለት ታሪካዊ ምዕራፎች
ሀገራችን ኢትዮጵያ በሁለት ወሳኝ ታሪካዊ ምዕራፎች ውስጥ ትገኛለች። በአንድ በኩል ሁሉንም የኢኮኖሚ አቅሞችና ዘርፈ ብዙ አማራጮች አሟጣ በመጠቀም ብልጽግናዋን ለማረጋገጥ ያላሰለሰ ጥረት እያደረገች ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ ጠንካራና ዘላቂ ሀገረ መንግሥት ለመገንባት ቁርጠኛ እርምጃዎችን እየወሰደች መሆኗ ይታወቃል።
ለእነዚህ ሁለት የማይነጣጠሉ ሀገራዊ ሂደቶች ስኬታማነት የምልኣተ ህዝብ የነቃ ተሳትፎና ጠንካራ ድጋፍ ወሳኝነት አለው።
ከቅርብ ቀናት በሗላ የምናካሂደውና ከ50 ሚሊዮን ህዝብ በላይ ለመራጭነት የተመዘገበበት ሀገራዊ ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ተቋማትና የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሂደታችንን የምናሳልጥበት ቁልፍ መሳሪያ ነው። ይህም ብቻ ሳይሆን የህዝብ ቅቡልነት አግኝቶ ኢኮኖሚያዊ ሉኣላዊነታችንን ማረጋገጥ የሚችል መንግሥት የምንመሰርትበት ወሳኝ ምዕራፍ ነው።
በምርጫ ሂደት ውስጥ ካርድ መውሰድ በራሱ የመጨረሻ ግብ አይደለም። ካርድ የወሰዱ ዜጎች በሙሉ በድምጽ መስጫ እለት በነቂስ ወጥተው የሚፈልጉትን ፓርቲ ከመምረጥ ባሻገር ሁሉም ቀጣይ ሂደቶች ሰላማዊ፣ ነጻና ዴሞክራሲያዊ ሆነው ምርጫው ለሁለቱ የኢትዮጵያ ታሪካዊ ምዕራፎች መሸጋገሪያ ድልድይ ይሆን ዘንድ ሀገራዊ ሃላፊነታቸውን በንቃት መወጣት ይጠበቅባቸዋል!!
"ያስታውሱ! የሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ የድምጽ መስጫ እለት በጣት የሚቆጠሩ ቀናት ብቻ ይቀሩታል! የወሰዱት ካርድ ሀገር የሚገነቡበት፣ የዴሞክራሲ ባህልን የሚያሰርጹበት ነው!!"

ልማትን ለማረጋገጥ የሕዝብን ፍላጎት መሠረት ያደረገ  አሳታፊ እቅድ በማቀድ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ ተገለፀበሰሜን ጎጃም ዞን ይልማና ዴንሳ ወረዳ የህዝብን ፍላጎት መሠረት ያደረገ እቅድ ...
26/05/2026

ልማትን ለማረጋገጥ የሕዝብን ፍላጎት መሠረት ያደረገ አሳታፊ እቅድ በማቀድ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ ተገለፀ

በሰሜን ጎጃም ዞን ይልማና ዴንሳ ወረዳ የህዝብን ፍላጎት መሠረት ያደረገ እቅድ በማቀድ ልማትን ማረጋገጥ እንደሚገባ የወረዳው ፕላንና ልማት ጽ/ቤት አስታወቀ

ግንቦት 18/2018 ዓ.ም (ይልማና ዴንሳ ኮሙኒኬሽን)

ጽ/ቤቱ ከሔልቬታዝ ፕሮጀክት ጋር በመተባበር ለአመቻቾች ፣ለቴክኒክ ቡድኖችና ለባለድርሻ አካላት በተቀናጀ ማህበረሰብ አቀፍ አሰራር እቅድ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል።

የስልጠና ሠነዱን ያቀረቡት የጽ/ቤቱ የእቅድ ዝግጅት ክትትልና ግምገማ ቡድን መሪ አቶ ደረጀ አሰፋ የተቀናጀ የማህበረሰብ አቀፍ አሳታፊ እቅድ ዋነኛ ዓላማ የልማት ፍላጎቶችን ከራሱ ከማህበረሰቡ በመነጨ መረጃ ላይ መሠረት ማድረግ የሚታቀድ መሆኑን ገልፀዋል።

አመቻቾችና የቴክኒክ ቡድኑ ከስልጠናው ያገኙትን ግንዛቤ ተጠቅመው የቀበሌያቸውን ዕቅድ ከተጨባጭ የህዝብ ጥያቄዎች ጋር ለማቀናጀትና የክትትል ስራውን ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ በትጋት ሊንቀሳቀሱ እንደሚገባ አቶ ደረጀ አሳስበዋል።

በስልጠናው ላይ ተሳታፊዎቹ ሰፊ ውይይት ያደረጉ ሲሆን የተለያዩ ጥያቄዎችንና አስተያየቶችንም አንስተዋል።

ይህ የተቀናጀ አሰራር በየደረጃው ያሉ ባለድርሻ አካላትን በኃላፊነት የሚያሳትፍ በመሆኑ በተግባር ሲተረጎም የሚታዩ የልማት ክፍተቶችን በዘላቂነት ለመፍታት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

የወረዳው ፕላንና ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ይበልጣል ታረቀኝ በማጠቃለያ ንግግራቸው የተሰጠው ስልጠና በተግባር ተተርጉሞ የወረዳውን የልማትና የመልካም አስተዳደር እቅዶች በላቀ ደረጃ ለማገዝ ሰልጣኞቹ በቁርጠኝነት መስራት ይኖርባቸዋል ብለዋል።

የተቀናጀ ማህበረሰብ አቀፍ አሳታፊ እቅድ ማህበረሰቡ በራሱ ልማት ላይ ቀጥተኛ ተሳትፎ እንዲያደርግና የሀብት አጠቃቀምን ውጤታማ ለማድረግ ትልቅ ሚና ያለው መሆኑን ኃላፊው ተናግረዋል።

ልማት ሊረጋገጥ የሚችለው የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች በጥናት ላይ ተመስርቶ በቅደም ተከተል መመለስ ሲቻል መሆኑን የገለፁት ደግሞ የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የህዝብ ግንኙነትና የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ መለሰ ታፈረ ናቸው።

የወረዳውን ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ እምቅ ሃብቶች በአግባቡ ለመጠቀም ሕዝቡን ያሳተፈ የተቀናጀ እቅድ ማቀድ እንደሚገባም አቶ መለሰ ተናግረዋል

በደቡብ ወሎ ዞን በደላንታና ወገልጤና ከተማ 7ኛውን ጠቅላላ ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫን አስመልክቶ የብልጽግና ፓርቲ የድጋፍ ሰልፍ ተካሄደ ።
26/05/2026

በደቡብ ወሎ ዞን በደላንታና ወገልጤና ከተማ 7ኛውን ጠቅላላ ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫን አስመልክቶ የብልጽግና ፓርቲ የድጋፍ ሰልፍ ተካሄደ ።

ሀገራዊ አንድነትን በማፅናት የጋይንት  ህዝብ ድርሻው የጎላ ነው  ሲሉ የደቡብ ጎንደር ዞን መንገድ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክ መምሪያ ሀላፊ አቶ ዳግም ጥሩነህ ተናገሩበደቡብ ጎንደር ዞን የላይ ...
26/05/2026

ሀገራዊ አንድነትን በማፅናት የጋይንት ህዝብ ድርሻው የጎላ ነው ሲሉ የደቡብ ጎንደር ዞን መንገድ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክ መምሪያ ሀላፊ አቶ ዳግም ጥሩነህ ተናገሩ

በደቡብ ጎንደር ዞን የላይ ጋይንት ወረዳና የነፋስ መውጫ ከተማ አስተዳደር በጋራ በተዘጋጀ የብልፅግና ፓርቲ ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ ተካሂዷል።

በድጋፍ ሰልፉ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የደቡብ ጎንደር ዞን መንገድ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክ መምሪያ ሀላፊ አቶ ዳግም ጥሩነህ ሀገራዊ አንድነትን በማፅናት የጋይንት ህዝብ ድርሻው የጎላ ነው ሲሉ ተናግረዋል። የለውጡን መንግስት እንደሚደግፍና ብልፅግናን እንደሚመርጥ ህዝቡ በነቂስ በመውጣት በድጋፍ ሰልፍ አረጋግጧል ያሉት አቶ ዳግም ለተደረገው የድጋፍ ሰልፍ ምስጋና አቅርበዋል።

በድጋፍ ሰልፉ ላይ የዞን ደጋፊ አመራሮች ፣ የሁለቱም ወረዳ አስተባባሪና ጠቅላላ አመራሮች ፣ የነፋስ መውጫ ከተማና በዙሪያው የሚገኙ ኗሪዎች በነቂስ በመውጣት ተሳትፈዋል።

ዜጎች ያለምንም ግፊት፣ ማስገደድ፣ ጉቦ ወይም ጥቅማጥቅም ድምፃቸውን በነፃነት መስጠት ይኖርባቸዋል።🌿🌿🌿🌿🌿ይህ ለአንድ ነፃ፣ ፍትሃዊ እና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ መሰረታዊ እና ወሳኝ መርህ ነው።ዜ...
26/05/2026

ዜጎች ያለምንም ግፊት፣ ማስገደድ፣ ጉቦ ወይም ጥቅማጥቅም ድምፃቸውን በነፃነት መስጠት ይኖርባቸዋል።
🌿🌿🌿🌿🌿

ይህ ለአንድ ነፃ፣ ፍትሃዊ እና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ መሰረታዊ እና ወሳኝ መርህ ነው።

ዜጎች ያለምንም ስጋት፣ የሃይል ግፊት፣ የማስገደድ ሙከራ ወይም በገንዘብና በጥቅማጥቅም ሳይደለሉ የራሳቸውን እውነተኛ ፍላጎትና ውሳኔ በነፃነት በድምፃቸው መግለጽ መቻላቸው የምርጫ ሥነ-ምግባር ዋናው መገለጫ ነው።

መርሁም የሚከተሉትን ወሳኝ እሴቶች ያረጋግጣል፦

👉የህዝብ ሉዓላዊነት፦ የስልጣን ባለቤትነቱ የእውነተኛው የህዝብ ፍላጎት ብቻ ይሆናል።
👉ታማኝነትና ተአማኒነት፦ የምርጫው ሂደት በህዝብና በዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ዘንድ ቅቡልነት እንዲኖረው ያደርጋል።
👉የሙስና መከላከል፦ ድምጽን በገንዘብ ወይም በጥቅማጥቅም ለመግዛት የሚደረጉ ጥረቶችን (የፖለቲካ ሙስናን) በማስቀረት የሀገርን ታማኝነት ይጠብቃል።

ይህን መሰረታዊ መብት ለማስከበር የዜጎች የነቃ ተሳትፎና የሥነ-ምግባር ግንዛቤ፣ እንዲሁም የገለልተኛ አስፈፃሚ አካላት ቁርጠኝነት ትልቅ ድርሻ አለው።

ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ የልማት ሥራዎችን ለመመረቅ ደሴ ገቡ።የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ የልማት ሥራዎችን መርቀው ሥራ ለማስጀመር ደሴ ከተማ ገብተዋል። ርእሰ መሥተዳድሩ...
26/05/2026

ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ የልማት ሥራዎችን ለመመረቅ ደሴ ገቡ።

የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ የልማት ሥራዎችን መርቀው ሥራ ለማስጀመር ደሴ ከተማ ገብተዋል።

ርእሰ መሥተዳድሩ ወሎ ኮምቦልቻ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱም የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፣ የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የፖለቲካ እና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኀላፊ ዘሪሁን ፍቅሩን (ዶ.ር) ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኀላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ በደሴ ከተማ አሥተዳደር ተገንብተው የተጠናቀቁ የልማት ሥራዎችን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት እንደሚያደርጉ ተገልጿል።

በግንባታ ላይ የሚገኙ የልማት ሥራዎችንም እንደሚጎበኙ እና የቀጣይ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ይጠበቃል።

የሰሜን ጎጃም ዞን የሰላምና ፀጥታ የህግ ማስከበር ተግባራት አፈፃፀምን ገመገመ።      ✔️✔️✔️✔️✔️      ‎ግንቦት 18/2018 ዓ/ም ባሕር ዳር በዞኑ የሰላምና የፀጥታ የህግ ማስከበ...
26/05/2026

የሰሜን ጎጃም ዞን የሰላምና ፀጥታ የህግ ማስከበር ተግባራት አፈፃፀምን ገመገመ።
✔️✔️✔️✔️✔️
‎ግንቦት 18/2018 ዓ/ም ባሕር ዳር
በዞኑ የሰላምና የፀጥታ የህግ ማስከበር፣የምርጫ ሥራዎች አፈፃጸም ተገምግሞ መልካም ሥራዎች እንዲቀጥሉና ክፍተቶች እንዲስተካከሉ በግምገማው አቅጣጫ ተቀምጧል።

በቀጣይም ከመደበኛ የሰላምና ፀጥታ ተግባራት በተጨማሪ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ፍፁም ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፀጥታ ተቋማት ተቀናጅተው መሥራት እንዳለባቸው ተመላክቷል።

‎በግምገማውም የክልል፣የዞን፣የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣የወረዳና የከተማ አስተዳደር፤እንዲሁም የፀጥታ መዋቅር አመራሮች ተግኝተዋል።

በምዕራብ ጎንደር ዞን ገንዳውኃ ከተማ አስተዳደር የብልፅግና ፓርቲ  የምርጫ ቅስቀሳና ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ነውገንዳውኃ ፤ ግንቦት 18/2018(ምዕራብ ጎንደር ዞን ኮሙኒኬሽን ) ...
26/05/2026

በምዕራብ ጎንደር ዞን ገንዳውኃ ከተማ አስተዳደር የብልፅግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳና ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ነው
ገንዳውኃ ፤ ግንቦት 18/2018(ምዕራብ ጎንደር ዞን ኮሙኒኬሽን ) ፦ዛሬ ከማለዳው ጀምሮ የብልፅግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳና ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ በደመቀ ሁኔታ በገንዳውኃ እየተካሄደ ይገኛል።
የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችም ከማለዳው ጀምሮ በገንዳውኃ መስቀል አደባባይ በመገኘት ቃሉን በተግባር ለተረጎመው ብልፅግና ፓርቲ ድጋፋቸውን በመግለፅ ላይ ይገኛሉ። See less

Address

Bahir Dar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Yilmana Densa Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share