Yilmana Densa Communication

Yilmana Densa  Communication በማህበራዊ፣በኢኮኖሚያዊ፣ፖለቲካዊ እና በታሪካዊ ጉዳዮች ወቅታዊ መረጃ ለህዝብ ማድረስ።

በድል የታጀበ ህዝባዊ ተሳትፎ ለዘላቂ ሰላምና ልማት መረጋገጥ"በሚል መሪ ሀሳብ ከወረዳው አመራር ጋር ውይይት እየተካሔደ ነውነሀሴ 12/2018 ዓ.ም (ይልማና ዴንሳ ወረዳ  ኮሙኒኬሽን‎‎በሰሜ...
18/08/2026

በድል የታጀበ ህዝባዊ ተሳትፎ ለዘላቂ ሰላምና ልማት መረጋገጥ"በሚል መሪ ሀሳብ ከወረዳው አመራር ጋር ውይይት እየተካሔደ ነው

ነሀሴ 12/2018 ዓ.ም (ይልማና ዴንሳ ወረዳ ኮሙኒኬሽን

‎‎በሰሜን ጎጃም ዞን ይልማና ዴንሳ ወረዳ "በድል የታጀበ ህዝባዊ ተሳትፎ ለዘላቂ ሰላምና ልማት መረጋገጥ" በሚል መሪ ሀሳብ ከወረዳው አመራር ጋር ውይይት እየተካሔደ ነው።
‎የመድረኩ ዋና ዓላማ የሰላምና የልማት ስራዎችን በህዝብ ተሳትፎ የበለጠ ማጠናከር ላይ ያተኮረ ሲሆን፤ በዕለቱም የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ሃላፊ አቶ መለሰ ታፈረ የመነሻ ሰነድ ለተሳታፊዎች እያቀረበ ይገኛል።

በሰሜን ጎጃም ዞን ይልማና ዴንሳ ወረዳ  ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት  ነሀሴ 13/2018 ከቀኑ 7;30  ጀምሮ በሰንቀኛ ቀበሌ እቮላ ተራራ ላይ  የደብረ ታቦር በዓል የተለያዩ ሀይማኖታዊ...
18/08/2026

በሰሜን ጎጃም ዞን ይልማና ዴንሳ ወረዳ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት ነሀሴ 13/2018 ከቀኑ 7;30 ጀምሮ በሰንቀኛ ቀበሌ እቮላ ተራራ ላይ የደብረ ታቦር በዓል የተለያዩ ሀይማኖታዊ ክዋኔወችን ባሟላ ሁኔታ በድምቀት እንደሚያከበር ገልፃል።
የጽ/ቤቱ ኃላፊ ወ/ሮ ጥሩ መላክ ባደረጉት መግለጫ "ባህላችን ድልድያችን ፣አንድነታችን መዳረሻችን " በሚል መሪ ቃል በወረዳ ደረጃ ለ8ኛ ጊዜ በአቮላ ተራራ ላይ በልዩ ድምቀት ይከበራል ብለዋል።
በበዓሉ ላይ ሀይማኖታዊ እና ባህላዊ ይዘቱን የጠበቀ አለባበስን በሀይማኖት አባቶች እንዲሁም በልጃገረዶች ፣ በወጣት ወንዶችና በምዕመናን እንደሚኖር ገልፀው በተሟላ ሁኔታ የሀይማኖት አባቶች ወረብ፣ መንፈሳዊ መዝሙሮች እና በወረዳው የባህል ቡድን የባህላዊ ጭፈራ ፣ ጭውውቶች እና የጅራፍ ማጮህ ሁነትን ጨምሮ ይቀርባል።
በበዓሉ ላይ ጥሪ የተደረገላቸው የዞንና የወረዳ አመራሮች ፣ የቤተክርስቲያን መምህራን ፣አባቶች ፣ ካህናት እና በርካታ ምዕመናን ይገኛሉ
ወ/ሮ ጥሩ በመግለጫቸው ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በቦታው ተገኝቶ የበዓሉ ታዳሚ እንዲሆን እና በዓሉን ወጉን እሴቱንና ሀይማኖታዊ ትውፊቱን በጠበቀ መልኩ በሰላም አክብሮ እንዲጠናቀቅ የበኩሉን አስተዋፅኦ እንዲያደርግ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

በሞሰቦ ቀበሌ "ዘላቂ ሰላም ለታላላቅ የልማት ስራዎች መሰረት ነው" በሚል መሪ ሃሳብ የወጣቶች ውይይት ተካሄደ። ነሀሴ 12/3018 ዓ.ም ይልማና ዴንሳ ወረዳ ኮሙኒኬሽን​ በሰሜን ጎጃም ዞን ...
18/08/2026

በሞሰቦ ቀበሌ "ዘላቂ ሰላም ለታላላቅ የልማት ስራዎች መሰረት ነው" በሚል መሪ ሃሳብ የወጣቶች ውይይት ተካሄደ።
ነሀሴ 12/3018 ዓ.ም ይልማና ዴንሳ ወረዳ ኮሙኒኬሽን

​ በሰሜን ጎጃም ዞን በይልማና ዴንሳ ወረዳ በሞሰቦ ቀበሌ ዘላቂ ሰላም ለታላለቅ የልማት ስረዎች መሰረት ነው በሚል መሪ ቃል ከሞሰቦ ወጣቶች ጋር የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው።

​የሕብረተሰቡን ሰላም እና ፀጥታ በማረጋገጥ የልማት ተጠቃሚነትን ለማሳደግ በሚደረጉ ጥረቶች ውስጥ የወጣቶች ሚና የላቀ መሆኑ የይልማና ዴንሳ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገበያው ሙላት ገልጸዋል።

ወጣቶች የሰላም እጦት ከሚያስከትሏቸው ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውሶች ራሳቸውን በመጠበቅ የአካባቢያቸውን ሰላም በንቃት መጠበቅ እንዳለባቸው የይልማና ዴንሳ ወረዳ ምኒሻ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አበረ መሌ መልከታቸውን አስተላልፈዋል።

​ ወጣቶች ከየትኛውም የጥፋት ሃሳብና ጎጂ ድርጊቶች ራሳቸውን አግልለው በዕውቀት፣ በስራ እና በህብረት በማደግ የነገ ሀገር ተረካቢነታቸውን ማረጋገጥ እንደሚገባቸው ኢ/ር ተሾመ አለማይ የይልማና ዴንሳ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ኃላፊ ገልጸዋል።
​የውይይት ተሳታፊ ወጣቶች ለሰላም ግንባታ እና ለአካባቢያቸው ልማት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ማበርከት እንዳለበቸው ሀሳባቸውን ገልጸዋል።

ገቢ የመሰብሰብ አቅምን በማሳደግና ዘመናዊ አሰራሮችን ተግባራዊ በማድረግ የህብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ማረጋጋጥ እንደሚገባ ተገለፀበሰሜን ጎጃም ዞን ይልማና ዴንሳ ወረዳ ገቢ የመሰብሰብ አ...
16/08/2026

ገቢ የመሰብሰብ አቅምን በማሳደግና ዘመናዊ አሰራሮችን ተግባራዊ በማድረግ የህብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ማረጋጋጥ እንደሚገባ ተገለፀ

በሰሜን ጎጃም ዞን ይልማና ዴንሳ ወረዳ ገቢ የመሰብሰብ አቅምን በማሳደግና ዘመናዊ አሰራሮችን ተግባራዊ በማድረግ የህብረተሰቡን የመልማት ፍላጎት ማረጋገጥ እንደሚገባ የወረዳው ገቢዎች ተጠሪ ጽ/ቤት አስታወቀ

ነሐሴ 10/2018 ዓ.ም (ይልማና ዴንሳ ኮሙኒኬሽን)

ሁለንተናዊ ልማትን ለማፋጠን የገቢ አቅምን ማጠናከር እና የንግድ ስርዓቱን ፍትሃዊና ህጋዊ ማድረግ ወሳኝ ነው።

ይህንኑ ተጨባጭ ሁኔታ መሰረት በማድረግም የወረዳው ገቢዎች እና ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤቶች በጋራ በመሆን "የህግ ተገዥነት ለገቢ ዕድገት"በሚል መሪ ቃል ከባለድርሻ አካላት ጋር ባለፈው በጀት ዓመት አፈፃፀምና በ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ውይይት አካሂደዋል።

የውይይቱን የመነሻ ሪፖርት ያቀረቡት የወረዳው ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዘውዱ ገሠሠ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከተለያዩ የገቢ አርዕስቶች 190 ሚሊየን 882 ሺህ 460 ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ በተደረገው ከፍተኛ ጥረት 192 ሚሊየን 521 ሺህ 779 ብር መሰብሰቡን ተናግረዋል።

የተሰበሰበው ገቢ ከ2017 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ71 ሚሊየን 306 ሺህ 412 ብር ብልጫ ያለው መሆኑንና
የ56 በመቶ ዕድገት ማሳየቱን የተናገሩት አቶ ዘውዱ በተሰበሰበው ገቢ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ በርካታ የልማት ስራዎች ተከናውነዋል ብለዋል።

በተያዘው በጀት ዓመትም ገቢ የመሰብሰብ አቅምን የበለጠ በማሳደግና ዘመናዊ አሰራሮችን ተግባራዊ በማድረግ የህብረተሰቡን የመልማት ፍላጎት ለማረጋገጥ በልዩ ትኩረት እንሰራለን ያሉት አቶ ዘዉዱ የዲጅታል ክፍያ አማራጮችን ማስፋፋት፣የአገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻያዎችን ወይም ፈጣንና ቀልጣፋ አሰራሮችን ተግባራዊ ማድረግ እንዲሁም ሌሎች ለተግባሩ ውጤታማነት የሚያግዙ አሰራሮችን መከተል ይገባል ብለዋል።

የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ከፀጥታ ችግሩ ጋር ተያይዞ በሚፈለገው መንገድ ተንቀሳቅሶ መስራት አለመቻል፣ ህገወጥ ነጋዴዎች መበራከት፣ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችና የግብር ፍትሃዊነት ችግሮችን አንስተው በሚመለከታቸው አካላት ማብራሪያ ተሰጥቷል።

የህዝቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ወረዳው በራሱ አቅም ሁሉንም የገቢ አማራጭች ሁሉ አሟጦ በመጠቀም የሚፈለገውን ገቢ መሰብሰብ ይኖርበታል ያሉት የሰሜን ጎጃም ዞን ገቢዎች መምሪያ የታክስ ኦዲትና ህግ ማስከበር የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ አትንኩት ይበልጣል የሚስተዋለውን ህገ ወጥ የንግድ እንቅስቃሴ በጋራ መከላከል፤ በአገልግሎት አሰጣጥ የሚስተዋሉ ጉድለቶችንም ማረም ይገባል ብለዋል።

የግብር ከፋዮችን እንግልት ለመቀነስ እና አሰራርን ለማዘመን በቴክኖሎጅ የታገዙ አሰራሮችን ማስፋፋት ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ የገለፁት የወረዳው ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ እይልኝ ጥላሁን ህገወጥ ንግድ፣ደረሰኝ አለመስጠትና አለመቀበል ፣ግብርን በአግባቡ ከአለመክፈል ጋር የተያያዙ ችግሮችን ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ማረም እንደሚገባ ተናግረዋል።

ባለፈው በጀት ዓመት የተሻለ ገቢ በመሰብሰባችን በርካታ የልማት ፕሮጀክቶችን ማከናወን ችለናል ያሉት የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዘመኑ ፈንታሁን በበኩላቸው በወቅቱና በትክክል የሚሰበሰብ ግብር መንግስት ለልማት ስራዎች በጀት እንዲያሟላ ትልቅ ድርሻ ያለው በመሆኑ ሁላችንም ትኩረት ሰጥተን ልንሰራ ይገባል ብለዋል።

በመጨረሻም የንግዱ ማህበረሰብና አጠቃላይ የወረዳው ነዋሪዎች ግብር መክፈል የዜግነት ግዴታ መሆኑን ተገንዝበው ህጋዊ ደረሰኝ የመስጠትና የመቀበል ልምድን እንዲያዳብሩ እንዲሁም ግብራቸውን በወቅቱ እንዲከፍሉ ጥሪ ተላልፏል።

የገቢ አሰባሰብና የንግድ ስራን በተቀናጀና ውጤታማ በሆነ መንገድ መምራት እንደሚገባ ተገለፀ በሰሜን ጎጃም ዞን የይልማና ዴንሳ ወረዳ ገቢዎች እና ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤቶች በጋራ የ2018...
16/08/2026

የገቢ አሰባሰብና የንግድ ስራን በተቀናጀና ውጤታማ በሆነ መንገድ መምራት እንደሚገባ ተገለፀ

በሰሜን ጎጃም ዞን የይልማና ዴንሳ ወረዳ ገቢዎች እና ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤቶች በጋራ የ2018 ዕቅድ አፈፃፀምና የ2019 ዕቅድ ከንግዱ ማህበረሰብና ከሌሎች አጋር አካላት ጋር "የህግ ተገዥነት ለገቢ ዕድገት" በሚል መሪ ቃል የግብር የንቅናቄ ውይይት እየተካሄደ ነው

ነሐሴ 10/2018 ዓ.ም (ይልማና ዴንሳ ኮሙኒኬሽን)

የወረዳው የገቢ አቅም አድጎ የልማት ፕሮጀክቶች በባለቤትነት እንዲጠናቀቁ የሁለቱ ጽ/ቤቶች ትብብር የማይተካ ሚና አለው።

በውይይቱ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዘመኑ ፈንታሁን ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር የንግድ እና የገቢ አሰባሰብ ስራን በተቀናጀና ውጤታማ በሆነ መንገድ መፈፀም ያስፈልጋል ብለዋል።

የንግድና ገቢ አሰባሰብ ስራዎች እርስ በርሳቸው የተሳሰሩ በመሆኑ ጤናማ የንግድ ስርዓትና የገቢ አሰባሰብ እንዲኖር በትኩረት መስራት እንደሚገባ አቶ ዘመኑ ተናግረዋል።

የወረዳው ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዘዉዱ ገሠሠ ያለፈውን በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እያቀረቡ ሲሆን ዘመናዊ አሰራሮችን በማጠናከርና ገቢ የመሰብሰብ አቅምን በማሳደግ የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄዎች መመለስ እንደሚገባም አመላክተዋል።

ለዘላቂ ሰላም የወጣቶች ሚና  በሚል መሪ ቃል የወጣቶች ውይይት ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው። በሰሜን ጎጃም ዞን በይልማና ዴንሳ ወረዳ በክልልት ቀበሌ ከወጣቶች ጋር ሰላምን፣ ልማትን፣ መልካም አ...
16/08/2026

ለዘላቂ ሰላም የወጣቶች ሚና በሚል መሪ ቃል የወጣቶች ውይይት ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው።

በሰሜን ጎጃም ዞን በይልማና ዴንሳ ወረዳ በክልልት ቀበሌ ከወጣቶች ጋር ሰላምን፣ ልማትን፣ መልካም አስተዳደርን እና ወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታዎችን አስመልክቶ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

​በመድረኩ የተሰታፎ ወጣቶች ለህዝብ ሰላምና ደህንነት ቅድሚያ በመስጠት በሁሉም የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ላይ ያላቸውን ንቁ ተሳትፎ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።

በውይይቱ ላይ የይልማና ዴንሳ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ /ጽ/ኃላፊ አቶ ገበያው ሙላት እና ሌሎች የፀጥታ አመራሮች ተገኝተዋል
ነሀሴ 10/2018 ዓ.ም ይልማና ዴንሳ ወረዳ ኮሙኒኬሽን።

በፀጥታ ችግር ምክንያት ላለፉት ሶስት ዓመታት ተቋርጦ የቆየውን የመማር ማስተማር ስራ ሙሉ በሙሉ በሁሉም ትምህርት ቤቶች ለማስጀመር የሁሉም አካላት ትብብር እንደሚያስፈልግ ተገለፀበሰሜን ጎጃም...
14/08/2026

በፀጥታ ችግር ምክንያት ላለፉት ሶስት ዓመታት ተቋርጦ የቆየውን የመማር ማስተማር ስራ ሙሉ በሙሉ በሁሉም ትምህርት ቤቶች ለማስጀመር የሁሉም አካላት ትብብር እንደሚያስፈልግ ተገለፀ

በሰሜን ጎጃም ዞን ይልማና ዴንሳ ወረዳ በፀጥታ ችግር ምክንያት ተቋርጦ የቆየው የመማር ማስተማር ስራ ሙሉ በሙሉ እንዲጀመር ሁሉም የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ እንደሚገባ የወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት አስታወቀ

ነሐሴ 08/2018 ዓ.ም (ይልማና ዴንሳ ኮሙኒኬሽን)

የወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማና የ2019 የትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባ የትምህርት ባለድርሻ አካላት በተገኙበት የንቅናቄ ውይይት አካሂዷል።

ትምህርት ለሰላም፣ ለማህበራዊ ልማትና ለሀገር ዕድገት መሠረት በመሆኑ በፀጥታ ችግር ሳቢያ ለረጅም ጊዜ ከትምህርት የራቁ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ተመላክቷል።

የጽ/ቤቱ የዕቅድና በጀት ዝግጅት ክትትል ግምገማ ቡድን መሪ አቶ ይስማው ፈጠነ ባቀረቡት የመወያያ ሰነድ በቀጣዩ የትምህርት ዘመን 83 ሽህ 313 ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር የቅድመ ዝግጅት ተግባራት እየተከናወኑ ናቸው ብለዋል።

ይህንን ለማሳካትም መምህራንና የትምህርት ባለሙያዎች ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ የሚጠበቅባቸውን ሙያዊ ኃላፊነት ሊወጡ እንደሚገባ አቶ ይስማው አስገንዝበዋል።

የሀይማኖት አባቶች እና የሀገር ሽማግሌዎች በማህበረሰቡ ዘንድ ያላቸውን እምነትና ተቀባይነት በመጠቀም ለሰላም ግንባታ ፣ለውይይትና ለመቻቻል የሚያበረክቱትን ሚና በማጠናከር ትምህርት እንዲጀመር የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ በውይይቱ ተጠቁሟል።

የወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ የሽዋስ አናጋው በመጪው የትምህርት ዘመን በሁሉም ትምህርት ቤቶች የመማር ማስተማር ስራውን ለማስጀመር ትምህርት ቤቶችን ማዘጋጀትና ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ቤት መመለስ የሁሉም የጋራ ኃላፊነት ሊሆን ይገባል ብለዋል።

የተማሪዎች የወደፊት ብሩህ ተስፋ በመምህራን እጅ ላይ መሆኑን ያሰመሩበት አቶ የሽዋስ የቀጣዩ የትምህርት ዘመን የፊታችን ነሐሴ 15/2018 ዓ.ም በአስር ትምህርት ቤቶች የተማሪዎች የሙከራ ምዝገባ እንደሚጀመርና ነሐሴ 18/2018 ዓ.ም ደግሞ በሁሉም ትምህርት ቤቶች መደበኛ የተማሪዎች ምዝገባ እንደሚካሄድ ተናግረዋል።

የአዴት ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የህዝብ ግንኙነትና የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ልመንህ ምህረት ትምህርት እንዲጀመር የሁሉም ባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ ተሳትፎ ወሳኝ ነው ብለዋል።

ባለፉት ዓመታት በትምህርት ዘርፍ የጋጠመውን ስብራት ጠንቅቆ በመረዳት የጋራ መፍትሄ ማበጀትና የሰው ሀብት ልማት ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባም አቶ ልመንህ አሳስበዋል።

ትምህርት የዕውቀት ማስተላለፊያ ብቻ ሳይሆን ለሰው ሀብት ልማት ትልቅ አስተዋፅኦ የሚያበረክት ፣የሀገር ኢኮኖሚን የሚያሳድግ ፣ሰላምን የሚያጠናክርና ዘላቂ የሀገር ልማትን የሚያረጋግጥ በመሆኑ ከየትኛውም ፖለቲካዊ አመለካከት ነፃ ሆኖ የመማር ማስተማር ስራው ሙሉ በሙሉ በሁሉም ትምህርት ቤቶች እንዲጀመር በማድረግ የነገ ሀገር ተረካቢ ዜጎችን ማፍራት የሁሉም ኃላፊነት ሊሆን ይገባል ያሉት ደግሞ የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዘመኑ ፈንታሁን ናቸው።

የትኛውም ዓይነት የፖለቲካ ልዩነት ቢኖርም በትምህርት ጉዳይ ላይ መግባባት እንደሚገባ የገለፁት አቶ ዘመኑ ሁሉም በባለቤትነትና በተቆርቋሪነት ሊሰራ እንደሚገባ አቶ ዘመኑ አሳስበዋል።

የይልማና ዴንሳ ወረዳ ትምህርት /ጽ/ቤት የ2018ዓ.ም በጀት አመት አፈፃፀም ግምገማ እና የ2019  በጀት አመት የትምህርት አጀማመርና የተማሪ ምዝገባ የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው።በሰሜ...
14/08/2026

የይልማና ዴንሳ ወረዳ ትምህርት /ጽ/ቤት የ2018ዓ.ም በጀት አመት አፈፃፀም ግምገማ እና የ2019 በጀት አመት የትምህርት አጀማመርና የተማሪ ምዝገባ የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው።

በሰሜን ጎጃም ዞን ይልማና ዳንሳ ወረዳ በ2019 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ስራው በሁሉም ትምህርት ቤቶች በሚጀመርበት ሁኔታ ላይ የንቅናቄ ውይይት እየተካሄደ ነው

ነሀሴ 08/2018 ዓ.ም (ይልማና ዴንሳ ኮሙኒኬሽን)

በዉይይቱ የወረዳ አመራሮች፣ርዕሰ መምህራን የትምህርት ሱፐርቫይዘሮች የትምህርት ባለሙያዎችና ሌሎች የትምህርት ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ የሽዋስ አናጋው በእንኳን ደህና መጣችሁ ባስተላለፉት መልዕክት የትምህርት ዘመኑ በተሳካ ሁኔታ እንዲጀመር ከወዲሁ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን በማጠናቀቅና የትምህርት ቤቶችን ዝግጁነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ተናግረዋል።

ትምህርት ሙሉ በሙሉ እንዲጀመርና ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ የሁሉንም አካላት ርብርብ እንደሚጠይቅም ኃላፊው ጠይቀዋል።

የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዘመኑ ፈንታሁን ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር በፀጥታ ችግር ምክንያት ተቋርጦ የቆየው ትምህርት ሙሉ በሙሉ እንዲጀመር በቅንጅት በትብብርና በጋራ መስራት ይገባል ብለዋል

የወረዳው ትምህርት ጸ/ቤት የዕቅድና በጀት ክትትልና ግምገማ ቡድን መሪ አቶ ይስማው ፈጠነ የ2018 በጀት አመት አፈፃፀምና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ እያቀረቡ ይገኛሉ።

ለክቡራን የክልላችን ግብር ከፋዮችየአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ በ2018 በጀት ዓመት እንዲሰበሰብ በክልላችን ም/ቤት ከፀደቀለት የገቢ ዕቅድ ውስጥ ከ93 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ሰብስቦ የእቅዱን...
14/08/2026

ለክቡራን የክልላችን ግብር ከፋዮች

የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ በ2018 በጀት ዓመት እንዲሰበሰብ በክልላችን ም/ቤት ከፀደቀለት የገቢ ዕቅድ ውስጥ ከ93 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ሰብስቦ የእቅዱን 92.66% በማሣካት የክልሉን ተቋማት ያቀዱትን እቅድ እንዲያሣካ የፋይናንስ ምንጭ በመሆን ስኬታማ ውጤት አስመዝግቧል።

በገጠር እና በከተሞቻችን እየተከናወኑ የሚገኙት የኮሪደር ልማቶች፣ አዳዲስ የትምህርት ተቋማት ግንባታዎች፣ ዘመናዊ የጤና ጣቢያዎች፣ እንዲሁም የመንገድና የድልድይ ግንባታዎች እርሰዎ የከፈሉት ታክስ ለልማት መዋሉን የሚያሣዩ ህያው ምስክሮች ናቸው።

ለዚህ የጋራ ስኬት ዋና መሠረቱ ለክልላችን እድገት በመቆም ግብር የመክፈል ኃላፊነትን በታማኝነት የተወጣችሁት እናንተው ታማኝ ግብር ከፋዮቻችንና የክልላችን የልማት አጋሮች ሁሉን አቀፍ ጥረት ነው።

በአሁኑ ወቅት በ2019 በጀት ዓመት ከክልላችንን የሚመጥን እና የህዝባችንን የመልማት ፍላጐት የሚያረካ የ166 ቢሊየን ብር የገቢ ግብ ሰንቀን እየሰራን እንገኛለን።

ይህ ግብ እውን የሚሆነው በጋራ ጥረታችንና በመተማመን ላይ የተመሠረተ የግብር አከፋፈል ስርዓት ሲረጋገጥ ብቻ ነው።

በአንዳንድ አካባቢዎች በግብር አሰባሰብ ሂደት ላይ የሚስተዋሉ የግብር ጭማሪ ቅሬታዎች ሊኖሩ ይችላሉ።

በግብር ውሣኔ፣ ስርጭትና አሰባሰብ ላይ የሚታዩ ችግሮች በውይይትና በምክክር እንዲሁም በተዘረጋው የቅሬታ ይግባኝ ስርዓት በየደረጃው ባለው አደረጃጀት እየፈታን መጥተናል፡፡ በቀጣይም በዚሁ ስርዓት የሚፈታ ይሆናል።

ስለሆነም ግብር ለሀገር ግንባታ እርስዎ የሚከፍሉት ታክስ የራስዎ፣ የቤተሰብዎ እና የህዝብዎ የነገ ተስፋ ነው፡፡

ዛሬ የምንገነባው ትምህርት የግብርና ልማት የምናደራጀው የጤና የመንገድ እና ድልድይ ግንባታ የምንዘረጋው የኮሪደር ልማት ለቀጣይ ትውልድ የምናወርሰው ቅርስ ነው፡፡ ስለዚህ ዛሬ ሆነን ነገን የምንገነባው በሚከፈለው ግብር ነውና ለስኬታማነቱ አሻራችንን እናሣርፋለን፡፡

የጋራ መድረክ በአወሣሰኑ፣ በአሰባሰቡና ወደ ልማት አዋዋሉ ላይ በተለያዩ አደረጃጀቶች በሚፈጠሩ መድረኮች በጋራ እየተነጋገርንና ምክክር እያደረግን ችግሮችን በዘላቂነት እንፍታ።

የሚሰበሰበው ገቢ በደጅዎ፣ በአካባቢዎ፣ የሚታይ ልማትን የሚያወጣ ወሣኝ የልማት ፋይናንስ ነውና ሁላችንም ልማት እንዲመጣ እንዲሁም እንደምንጠይቀሁ ሁሉ ለገቢ አሰባሰቡም የዜግነት ድርሻችንን እንወጣ!

ለጋራ ብልጽግና የክልላችን ልማት በሁሉም አቅጣጫ እንዲሰፋና በየደረጃው ያለው የማህበረሰብ ክፍል ተጠቃሚ እንዲሆን የክልላችን ኢኮኖሚ ያመነጨውን ገቢ በአግባቡ መሰብሰብ ይገባል፡፡ እንደ ክልል በራስ የገቢ ምንጭ ወጫችንን የመሸፈን ግባችንን ለማሣካት ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ ይገባል።

ዘላቂነት ያለው የሀገር ግንባታና ብልጽግና የሚረጋገጠው ከጥገኝነት የተላቀቀ ገቢ ማመንጨት ሲቻል ነው፡፡ እያንዳንዱ ተጠቃሚ የሚሆንበት ልማት የሚመጣው ከራሱ በሚመነጭና በራስ በሚሰበሰብ ገቢ ነው፡፡ ለዚህም ሁሉም የዜግነት ድርሻውንና ግዴተውን ሊወጣ ይገባል።

ውድ ግብር ከፋዮቻችን የያዝነውን ሀገራዊ ብልጽግናን የማረጋገጥ ታላቅ ራዕይ እውን ለማድረግ ሁላችንም የሚፈለግብንን ግብርና በአደራ የተሠጠንን በውክልና የምንሠበስበውን ታክስ በታማኝነትና በወቅቱ ለገቢ ሰብሣቢ ተቋማት ማሣወቅ ለነገ የማይገባ ግዴታችን ነው።

በውስጣችን፣ በአካባቢያችን፣ በገቢ ተቋሙና መሰል አካላት የምናያቸውን ብልሹ አሰራሮች በቁርጠኝተት በመታገልና በማጋለጥ ትውልዳዊ እዳችንን ልውጣ ይገባል።

በየደረጃ በመስጠትና መቀበል ዙሪያ የሚታዩ ችግሮችን በጋራ መካከልና በታማኝነት ደረሰኝ ማሰጠትና መቀበል ዋነኛ ተልዕኮና አደራ መሆኑን አውቀን ተጨባጭ ውጤት እናስመስግብ ወሣኙ መልዕክታችን ነው።

“ደረሰኝ በመስጠትና በመቀበል የዜግነት ግዴታችንን እንወጣ!”
መንገሻ ፈንታሁን (ዶ/ር)
የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ

በአዴት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የክረምት ስራዎች ጉብኝት ተካሄደበሰሜን ጎጃም ዞን ይልማና ዴንሳ ወረዳ የአዴት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ2019 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ስ...
13/08/2026

በአዴት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የክረምት ስራዎች ጉብኝት ተካሄደ

በሰሜን ጎጃም ዞን ይልማና ዴንሳ ወረዳ የአዴት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ2019 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ስራ ውጤታማ፣ጥራት ያለውና ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት የሚያበቃ እንዲሆን በክረምቱ ወቅት በበጎ ፈቃድ የተከናወኑ ስራዎችን የሚያሳይ የስራ ጉብኝት ተካሂዷል።

ነሀሴ 07/2018 ዓ.ም (ይልማና ዴንሳ ኮሙኒኬሽን)

ትምህርት ቤቱ በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ያከናወናቸው የልማትና የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ተጎብኝተዋል። ለሻወር አገልግሎት የሚውሉ መታጠቢያ ቤቶች ተገንብተዋ። "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ቃል በአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ለግቢው ውበትና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ተተክለዋል።

በትምህርት ቤቱ የውስጥ ገቢ የመምህራን ቢሮዎች የህንፃ ዕድሳት ተደርጓል፤ግቢውን ሳቢ፣ጽዱና ማራኪ ለማድረግ የፅዳት ስራዎች ተከናውነዋል። የክረምት የማጠናከሪያ ትምህርትና የቤተ መጽሃፍት አገልግሎት እየተሰጠ ሲሆን ዘላቂ የንፁህ መጠጥ ውሀ ተጠቃሚነትን የማረጋገጥ ስራዎች ተሰርተዋል። ለተማሪዎች የሻይ ቤት አገልግሎት የሚሰጡ ክፍሎች ተዘጋጅተዋል። የዲ ኤስ ቴቪ አገልግሎት መኖሩም ተገልጿል።

የወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ የሽዋስ አናጋው በጉብኝቱ ማጠቃለያ በተካሄደው ውይይት እንደተናገሩት በወረዳው 89 ትምህርት ቤቶች መኖራቸውን ጠቁመው የአዴት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን በአግባቡ ማስተዳደርና ውጤታማ ማድረግ ለሌሎች ትምህርት ቤቶችም መሠረት የሚጥል ነው ብለዋል።

ትምህርት ቤቱ ዘመኑን የሚመጥን፣ሀብት ማመንጨት የሚችልና በቀለም ትምህርት ብቻ ሳይሆን በሁለንተናዊ ዘርፍ ሞዴልና ተመራጭ እንዲሆን በትኩረት መስራት እንደሚገባ ያስገነዘቡት ኃላፊው በ2019 የትምህርት ዘመን የተማሪዎችን ውጤት በሚፈለገው ልክ ለማሻሻል ከወዲሁ በዕቅድ መስራት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።

በጉብኝቱ የታዩት የስራ እንቅስቃሴዎች የሚያበረታቱና ተስፋ ሰጭ መሆናቸውን የጠቆሙት የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የህዝብ ግንኙነትና የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ መለሰ ታፈረ በግቢው የተሰሩት ስራዎች ከመማር ማስተማር ባሻገር ለተማሪዎች ምቹ የመማሪያ አካባቢ በመፍጠር ለውጤታማነት እንደሚያግዙ ተናግረዋል።

ቀሪ ስራዎችንም በማጠናቀቅ ትምህርት ቤቱ ለሌሎች ትምህርት ቤቶች ሞዴልና አርዓያ እንዲሆን መስራት እንደሚገባ ያሳሰቡት አቶ መለሰ በተለይም ቤተ መጽሃፍቱ ሙሉ ዕድሳት እንዲደረግለትና የገቢ አቅምን ለማሳደግ ሀብት የማፍራት ስራዎች እንዲጠናከሩ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።

የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዘመኑ ፈንታሁን በበኩላቸው የትምህርት ቤቱ አመራሮች ፣መምህራንና ሰራተኞ የተሻለ ለመስራት የሚያስችሉ አዳዲስ ኃሳቦችን ይዘው መንቀሳቀሳቸውን ጠቁመው ይህ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል ሲሉም ተናግረዋል።

በተለይም ከፍተኛ የተማሪ ቁጥር ያለው ተቋም በመሆኑ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲዎች ሲሸጋገሩ በዉጤትም ሆነ በስነ ምግባር ጠንካራ መሠረት የሚኖራቸው እንዲሆኑ መስራት እንደሚገባ አቶ ዘመኑ አስገንዝበዋል ።

የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ይበልጣል ሙላቴ በበኩላቸው የትምህርት ቤቱ ስራ ከአንድ የበጎ ፈቃድ ዘመቻ በላይ በመሆኑ ተቋሙን በዘላቂነት የሚያሻሽል አመራርና ተቀናጅቶ የመስራት ባህል እንዲገነባ አሳስበዋል።

ትምህርት የሁሉም ዕድገት መሠረት በመሆኑ የትምህርት ቤቱ ጉዳይ የትምህርት ሠራተኞች ብቻ ሳይሆን የወረዳው አመራር ፣ የወላጆች ፣ የማህበረሰቡና የሁሉም አካላት የጋራ ኃላፊነት መሆኑን አሰተዳዳሪው አስምረውበታል።

የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር አቶ ይልቃል አያሌው በክረምቱ ወቅት በጊዜ የለኝም ስሜት በቁርጠኝነት መስራታቸውን ገልፀው በተለይም የትምህርት ቤቱ የንፁህ መጠጥ ውሀ ችግር በዘላቂነት መፈታቱን ተናግረዋል። በቀጣይም ትምህርት ቤቱ ለረጅም ጊዜ ያገለገለ በመሆኑ የህንፃዎች ዕድሳት ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ጠቁመዋል ።

በቀጣዩ የትምህርት ዘመን የተሻለ የመማር ማስተማር እንዲኖርችግሮችን በመለየት እና የትምህርት ቤቱ አስፈላጊ መሠረተ ልማቶች እንዲሟሉ እንዲሁም የትምህርት ጥራት እንዲረጋገጥ ትኩረት ሰጥተው እንደሚሰሩ የተናገሩት የአዴት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ጉድኝት ሱፐርቫይዘር አቶ ዳኛቸው ገናነው ሁሉም አካላት የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡም ጠይቀዋል።

Address

Bahir Dar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Yilmana Densa Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share