30/05/2026
የአማራ ክልል ጠበቆች ማህበር ፕሬዝዳንት ሰሎሞን ጎራው በሰሜን ሸዋ ዞን የጠበቆች ማህበር አመራሮች ጋር በደብረ ብርሃን ከተማ ውይይት አድርገዋል።
👇 👇 👇 ⛩️ 👇 👇 👇
የክልሉ ጠበቆች ማኅበር አመራሮች በሰሜን ሸዋ ዞን ደብረ ብርሃን ከተማ ከዞኑ ጠበቆች ተወካዮች ጋር ያደረጉትን ተራማጅና ፍሬያማ ውይይት አሳይተዋል።
❗️ ይህ መድረክ የጠበቆችን መብትና ጥቅምን ለማስከበር ብቻ ሳይሆን፣ የፍትህ ሥርዓቱን ተደራሽነትና ጥራት ለማረጋገጥ የተደረገ ታሪካዊ እርምጃ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል።
በውይይቱ ላይ የተነሱትን ዋና ዋና ነጥቦች ከዓለም አቀፍ መርሆች ጋር በማዛመድ እንደሚከተለው በዝርዝር ተተንትኖ ነበር፦
1ኛ:- የጠበቆች የሙያ ስነ-ምግባር እና የፍትህ ስርዓት ትስስር (Legal Ethics and the Administration of Justice)
❗️ የጠበቆችን የሙያ ስነ-ምግባር ማሻሻል ከፍትህ ስርዓቱ ጋር ያለውን የጋራ ግንኙነትና በፍትህ አካላት መካከል የሚኖረውን ሚና ማጠናከር አስፈላጊ መሆኑ፣
❗️ በዓለም አቀፍ የጠበቆች ማህበር (IBA) መርሆች መሰረት፣ ጠበቃ የደንበኛው ተሟጋች ብቻ ሳይሆን "የፍትህ ስርዓቱ መኮንን" (Officer of the Court) ናቸው። ጠበቆች ከፍተኛ ስነ-ምግባር ሲኖራቸው የህዝብ በፍትህ ስርዓቱ ላይ ያለው እምነት ይጨምራል። የሙያ ስነ-ምግባርን ማሻሻል የህግ የበላይነትን (Rule of Law) ለማስፈን መሰረት መሆኑ።
2ኛ. ጠንካራና ራሱን የቻለ የጠበቆች ማህበር መዋቅር (Independence of the Bar)
❗️ በአዋጅ ቁጥር 293/2017 (በአዲሱ አዋጅ) መሰረት የሚወጡ ደንቦች ላይ የጠቅላላ ጉባኤ አባላት በንቃትና በብቃት እንዲሳተፉ ማድረግ፣ የፋይናንስ አቅምን ማጠናከር እና የማህበሩን መዋቅር በዞን ደረጃ መዘርጋት እና እስከ ወረዳ ድረስ እንዲተሳሰር ምቹ ሁኔታ መፍጠር፣
❗️ የጠበቆች ማህበር ነጻና ራሱን የቻለ (Independent Bar Association) መሆን አለበት። ይህ ነጻነት የሚረጋገጠው ደግሞ ማህበሩ ጠንካራ የውስጥ መዋቅር፣ የውስጥ ዲሞክራሲ (የአባላት ንቁ ተሳትፎ) እና ራሱን የቻለ የፋይናንስ ምንጭ ሲኖረው ነው።
የተጠቀሱት የማጠናከሪያ ስራዎች ማህበሩ ተቋማዊ ነጻነቱን ጠብቆ አባላቱን በብቃት እንዲያገለግል ያስችለዋል በሚል ታምኖበታል።
3ኛ. የፍትህ ተደራሽነት እና የሰብአዊ መብቶች ጥበቃ (Access to Justice & Fair Trial)
❗️ የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት በቪዲዮ ኮንፈረንስ (በአይቲ መረብ) መዘርጋቱ የሰብአዊ መብትን፣ ፍትህ የማግኘት መብትን እና የውሳኔ ግልባጭን በፍጥነት የማግኘት ችግሮችን እንደሚቀርፍ መግባባት ላይ መደረሱ እና በክርክር ላይ ለጠበቆች ለአፈፃፀም አልመች የሚሉትን የአሰራር እንቅፋቶች ካሉ እየለዩ ችግሩን መፍታት ወሳኝ መሆኑና ይህንን ተከትሎ በሰበር የሚቀርቡ ጉዳዮች ለጠበቆች ወይም ለባለጉዳዮች ምቹ አሰራር እንዲኖረው ማድረግ፣
❗️ ፍትህ የማግኘት መብት (Access to Justice) መሰረታዊ የሰብአዊ መብት ነው። ቴክኖሎጂን በመጠቀም የሰበር ችሎትን ተደራሽ ማድረግ የደንበኞችን የጊዜና የገንዘብ ወጪ ከመቀነሱም በላይ፣ ጉዳዮች በአጭር ጊዜ ውሳኔ እንዲያገኙ (Right to a Speedy Trial) በማድረግ ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ስምምነቶችን በተግባር የሚተረጉም እጅግ ዘመናዊ አካሄድ መሆኑ ታምኖበታል።
4ኛ. የሙያ ነጻነት እና የግብር/ተርን ኦቨር ታክስ (TOT) ተግዳሮቶች (Financial Autonomy & Protection of Profession)
❗️ የጠበቆች ስራ ግብር ከደረጃ "ሐ" ወደ ደረጃ "ሀ" በመሸጋገሩ ምክንያት የመጣውን ከፍተኛ የግብር ጫና ከክልሉ ገቢዎች ቢሮ እና የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ምዝገባ ተግዳሮቶችን ከገንዘብ ሚንስቴር ጋር በጥናት ላይ የተመሰረተ ውይይትና መፍትሄ ፍለጋ ማድረግ እንደሚያስፈልግ እና ማህበሩ ከኋላ ሁኖ ጠበቆች በአንድ ላይ ሁነው ችግሩን ለዚህ አመት እንዲወጡ መደገፍ ማስፈለጉ ትኩረት ተሰጥቶታል።
❗️ እንደመነሻም የህግ ሙያ እንደ ማንኛውም ተራ የንግድ ስራ (Commercial Business) ሊታይ አይገባም። ጠበቆች ህዝባዊና ህጋዊ ግዴታን የሚወጡ የፍትህ አካላት በመሆናቸው፣ በላያቸው ላይ የሚጣሉ የኢኮኖሚና የግብር ጫናዎች ህብረተሰቡ የህግ ምክርና ጥበቃ እንዳያገኝ እንቅፋት መሆን የለባቸውም።
❗️ ማህበሩ የግብር ጉዳይ በጥናት አስደግፎ ከገቢዎች ባለስልጣን ጋር ለመደራደር ማቀዱ- የግብር ግደታን ላለመውወጣት የሚደረግ ጥረት ሳይሆን- የባለሙያዎችን መብት ለማስከበርና የህግ አገልግሎት ዋጋ እንዳይንር (ተመጣጣኝ ሆኖ እንዲቀጥል) ለማድረግ የሚጥሩ የዓለም አቀፍ ማህበራት ዋነኛ ተግባር (Advocacy for the Profession) ነጸብራቅ በመሆኑ ነው።
❗️❗️በአጠቃላይ የክልሉ ጠበቆች ማህበር የአባላቱን መብትና ጥቅም ከማስከበር ባለፈ፣ የፍትህ ሥርዓቱን ውጤታማነት፣ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን እና የሙያ ሥነ-ምግባርን ከፍ ለማድረግ የሚተጋ ንቁ፣ ተራማጅና ተቋማዊ ራዕይ ያለው ማኅበር መሆኑን በግልጽ እንዲያሳይ ተደርጎ ለመስራት እየተንቀሳቀሰ መሆኑን በደብረ ብርሐን በተደረገው ውይይት ተነስቷል።
የአማራ ክልል ጠበቆች ማህበር
ደብረ ብርሃን