ጋዲሎ ሸዋ- Gadilo Shewa tube

ጋዲሎ ሸዋ- Gadilo Shewa tube የኢትዮጵያን ህዝብ አጠቃላይ ባህላዊ፣ታሪካዊ፣ተፈጥሮአዊ እንዲሁም ሀይማኖታዊ እሴቶችን ፣ የመሥህብ ሀብቶችን ለአለም ህዝብ ማስተዋወቅ

መንዝ ጓሳመንዝ ጓሳ ከደብረ ብርሃን 152 ኪ.ሜ ከመንዝ ጌራ ምድር ወረዳ ዋና ከተማ መሃል ሜዳ 18 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኝ የማህበረሰብ አቀፍ ጥብቅ ስፍራ ነው፡፡ ጥብቅ ስፍራው ስያሜውን ...
26/05/2026

መንዝ ጓሳ

መንዝ ጓሳ ከደብረ ብርሃን 152 ኪ.ሜ ከመንዝ ጌራ ምድር ወረዳ ዋና ከተማ መሃል ሜዳ 18 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኝ የማህበረሰብ አቀፍ ጥብቅ ስፍራ ነው፡፡ ጥብቅ ስፍራው ስያሜውን ያገኘው በአካባቢው በብዛት ከሚበቅለው የጓሳ ሳር ሲሆን በውስጡም ቀይ ቀበሮ እና ጭላዳ ዝንጀሮን ጨምሮ የተለያዩ የዱር እንሰሳት፣ 14 የሚሆኑ ብርቅዬ አዕዋፍት እና በዛ ያሉ የዕፅዋት ዝርያዎችን ይገኙበታል፡፡

ድንቅ መልክዓ ምድራዊ ገጽታ ያለው የመንዝ ጓሳ ጥብቅ ስፍራ ብዝሃ ሕይወት ሀብት ከ400 ዓመታት በላይ የተጠበቀው እና ዛሬን የደረሰው በአካባቢው ማህበረሰብ ነው፡፡ ማህበረሰቡ አካባቢውን ከመጠበቅ ባሻገር ጎብኝዎችን የሚያስተናግድ የማህበረሰብ ሎጅ በጥብቅ ስፍራው ያለው ሲሆን ለእንግዶች ተወዳጅ ባህላዊ ምግቦች በማቅረብ ይታወቃል፡፡

ጣና ሐይቅ - የኢትዮጵያ ጌጥየጣና ሐይቅ ከተፈጥሯዊ ፋይዳና ውበቱ ባልተናነሰ በምስጢራዊነቱ እንዲሁም በታሪክና ሀይማኖት ማህደርነቱ ትልቅ ዋጋ የሚሰጠው ሐይቅ ነው፡፡ በእሳተ ገሞራ ፍንዳታ እ...
25/05/2026

ጣና ሐይቅ - የኢትዮጵያ ጌጥ

የጣና ሐይቅ ከተፈጥሯዊ ፋይዳና ውበቱ ባልተናነሰ በምስጢራዊነቱ እንዲሁም በታሪክና ሀይማኖት ማህደርነቱ ትልቅ ዋጋ የሚሰጠው ሐይቅ ነው፡፡ በእሳተ ገሞራ ፍንዳታ እንደተፈጠረ የሚታመነው ጣና በአማካኝ ከሰሜን ወደ ደቡብ 75 ኪ.ሜ፣ ከምስራቅ ወደ ምዕራብ ደግሞ 60 ኪ.ሜ ይረዝማል፡፡ አማካኝ ስፋቱ ደግሞ 3600 ስኩየር ኪሎ ሜትር ሲሆን ጥልቀቱ 9 ሜትር ነው፡፡ ጣና በአፈጣጠሩ እና ከባሕር ወለል በላይ 1830 ሜትር ከፍታ ላይ በመገኘቱ ከተራራ ላይ ሐይቆች የሚመደበው ሲሆን ከሰሜን ሰፋ ያለና ወደ ደቡብ እየጠበበ የሚመጣ በልብ ቅርጽ አምሳል የተፈጠረ አስገራሚ ሐይቅ ነው፡፡

ከክርስቶስ ልደት በፊት በ5ኛው ክፍለ ዘመን ስለጣና የጻፈው የአቴናው ድራማ ጸሐፊ ኤስኪለስ “መዳብ የተቀባው ሐይቅ፤ የኢትዮጵያ ጌጥ” ይለዋል፡፡ ኢትዮጵያዊያንም ስለ ጣና በአፈ-ታሪክ፣ በትውፊት እና በሀይማኖት ብዙ ብለዋል፡፡ ዘረ ደሸቶች የኢትዮጵያ ታሪክ መነሻ ይሉታል፡፡ አንዳንድ ምሁራን እና የሀይማኖት አባቶች ደግሞ የኩሽ ስልጣኔ መሰረት፣ የዮቶር ምድር፣ የኦሪት የመስዋዕት ቦታ፣ የታቦተ ጽዮንና የድንግል ማርያም ማረፊያ፣ የተሰወሩ ቤተ መቅደሶች መገኛ፣ የቅዱስ ያሬድ ምርጫ፣ በመንፈሳዊያን ለተጋድሎ እና ስብሃተ እግዚአብሔር ለማድረስ የተመረጠ ቅዱስ ሐይቅ ይሉታል፡፡

በኢትዮጵያ በስፋቱ ቀዳሚ በሆነው በዚህ ድንቅ ሐይቅ ላይ በሚገኙ ደሴቶች በዋጋ የማይተመኑ ውድ ሀይማኖታዊ እና ታሪካዊ ቅርሶችን የያዙ 45 የሚሆኑ ገዳማትና አብያተ ክርስቲያናት ይገኛሉ፡፡ ዓመቱን በሙሉም ሀይማኖታዊ ተጓዦችን እና ቱሪስቶች እነዚህን ገዳማት ለመጎብኘት በሐይቁ ላይ ጉዞ ያደርጋሉ፡፡ ጣና ባለው እምቅ የብዝሃ-ህይወት ሀብት የተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስና ባህል ድርጅት (UNESCO) በ2007 ዓ/ም “በዓለም ሕይወተ-ክልልነት” ተመዝግቧል፡፡

ይምጡና በጣና ሐይቅ ላይ የማይረሳ ጊዜን ያሳልፉ
https://www.youtube.com/@%E1%8C%8B%E1%8B%B2%E1%88%8E%E1%88%B8%E1%8B%8B

 #ኤፍራታ- #ግድም  ጋራና ሸንተረሩ💚መሀልወንዝ ከሰያት አባማዶ መንጠር💛ሳራባና አላላ ከፍ ሲል አንቦበር❤️ይምላዎና በርግቢ ጋዲሎ መስቀል በር❤️የነአይጠገቡ የሸጋዎች ሀገር😘😁💚💛❤
25/05/2026

#ኤፍራታ- #ግድም
ጋራና ሸንተረሩ💚
መሀልወንዝ ከሰያት አባማዶ መንጠር💛
ሳራባና አላላ ከፍ ሲል አንቦበር❤️
ይምላዎና በርግቢ ጋዲሎ መስቀል በር❤️
የነአይጠገቡ የሸጋዎች ሀገር😘😁💚💛❤

ሰንበቴ እግርኳስ ቡድን እንኳን ደስ አላችሁ!!!=======================ዛሬ በአጣዬ ሁለገብ ስታዲየም በተደረገው የA ቡድን እግርኳስ ጨዋታ በአጣዬ 02  እና በሰንበቴ መካከል የ...
24/05/2026

ሰንበቴ እግርኳስ ቡድን እንኳን ደስ አላችሁ!!!
=======================
ዛሬ በአጣዬ ሁለገብ ስታዲየም በተደረገው የA ቡድን እግርኳስ ጨዋታ በአጣዬ 02 እና በሰንበቴ መካከል የተካሄደው ጨዋታ በሰንበቴ 1 ለ 0 አሸናፊነት የተጠናቀቀ ሲሆን ሰንበቴ ለዋንጫ ማለፋን ያረጋገጠበት እንዲሁም ድጋሜ ከአጣዬ 03 በአንድ የውድድር ዘመን ሁለት ጊዜ ለዋንጫ የተገናኙበት መሆኑ የዋንጫው ጨዋታ የበለጠ ሳቢና ማራኪ እንደሚሆን በጉጉት እንዲጠበቅ አድርጎታል።

24/05/2026

አጣዬ 02 0_1 ሠንበቴ 45"

አጣዬ 02 ቀበሌ እና የሰንበቴ ከተማ የእግር ኳስ ቡድኖች ጨዋታቸውን ጀመሩ።ኤፍራታ፣ ግንቦት 16/2018 ዓ.ም (ኤፍራታ ኮሙኒኬሽን) – በኤፍራታና ግድም ወረዳ እና በአጣዬ ከተማ አዘጋጅነት...
24/05/2026

አጣዬ 02 ቀበሌ እና የሰንበቴ ከተማ የእግር ኳስ ቡድኖች ጨዋታቸውን ጀመሩ።

ኤፍራታ፣ ግንቦት 16/2018 ዓ.ም (ኤፍራታ ኮሙኒኬሽን) –

በኤፍራታና ግድም ወረዳ እና በአጣዬ ከተማ አዘጋጅነት የሚካሄደው የበጋ እግር ኳስ ውድድር በአጣዬ 02 ቀበሌ እና በሰንበቴ ከተማ የእግር ኳስ ቡድኖች ጨዋታ ተጀምሯል።

በውድድሩ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የኤፍራታና ግድም ወረዳ ተቀዳሚ አስተዳዳሪ አቶ አበራ መኮንንን ጨምሮ የወረዳና የከተማ አመራሮች ተሳትፈዋል።

በተጨማሪም የአጣዬ ከተማ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አበባው ገረመው እና የኤፍራታና ግድም ወረዳ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ትለፍ ወንደሰን በፕሮግራሙ ተገኝተዋል።

ጨዋታውን የፌደራል የእግር ኳስ ዳኛ ኢንስትራክተር አብዱራማን ይማም በዋና ዳኝነት የመሩ ሲሆን፣ ቢንያም ገድሉ እና ሚኪያስ ጌታነህ በረዳት ዳኝነት እንዲሁም አሸናፊ ተሰማ በአራተኛ ዳኝነት ጨዋታውን መርተዋል።

ውድድሩ የወጣቶችን ተሳትፎ፣ ስፖርታዊ መንፈስና ማህበራዊ ትስስር ለማጠናከር እንደሚያግዝ ተገልጿል።

24/05/2026

አጣዬ ሁለገብ ሥቴድየም

በቅዱስ ላሊበላ! የዓለማችን ዝነኛ የቲክቶክ ኮከብ ዲላን ፔጅ ከሀገር ወዳዱ አዶናይ ጋር በቅዱስ ላሊበላ!በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ተከታዮች ያሉት የዓለማችን ድንቅ የቲክቶክ ይዘት ፈጣሪ ዲላን ፔጅ...
24/05/2026

በቅዱስ ላሊበላ!

የዓለማችን ዝነኛ የቲክቶክ ኮከብ ዲላን ፔጅ ከሀገር ወዳዱ አዶናይ ጋር በቅዱስ ላሊበላ!

በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ተከታዮች ያሉት የዓለማችን ድንቅ የቲክቶክ ይዘት ፈጣሪ ዲላን ፔጅ (Dylan Page) በኢትዮጵያ እያደረገ ያለውን ታሪካዊ ጉብኝት ቀጥሏል።

በዛሬው ዕለትም በበጎ ተጽዕኖ ፈጣሪነቱ እና በሀገር ፍቅሩ የሚታወቀው ወጣቱ ቲክቶከር አዶናይ ብርሃነ (ሀገር ወዳዱ) አጅቦት ከዓለም ድንቆች አንዱ በሆነው በቅዱስ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት አስደናቂ ጉብኝት አድርገዋል።

ዲላን ፔጅ እና አዶናይ ለቦታው ያላቸውን ጥልቅ ክብር እና አክብሮት ባሳየ መልኩ፣ የቤተክርስቲያኗን ደንብና ሥርዓት ሙሉ በሙሉ በመከተል ነጭ ነጠላ ተጎናጽፈው የታዩበት ምስል በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኗል።

ይህ የሀገራችንን ባህል እና የሃይማኖት ሥርዓት ያከበረ አቀራረባቸው በኢትዮጵያውያን ዘንድ ትልቅ አድናቆትንና ልባዊ ምስጋናን አስገኝቶላቸዋል።

አዶናይ ብርሃነ (ሀገር ወዳዱ) የሀገሩን መልካም ገጽታ፣ ታሪክና ባህል ለዓለም አቀፍ እንግዶች በማስተዋወቅ ረገድ እያበረከተ ያለው በጎ ተጽዕኖ እና ያሳየው አቀባበል የሚደነቅ ነው። እንዲህ ያሉ የባህል ትስስሮች የሀገራችንን የቱሪዝም ዘርፍ ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ያላቸው ሚና በቀላሉ የሚገመት አይደለም።

በ12ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በጻድቁ ንጉሥ ላሊበላ አማካኝነት ከአንድ ወጥ ድንጋይ ተፈልፍለው የታነጹት 11ዱ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት፣ የኢትዮጵያ ጥንታዊ ስልጣኔ፣ የላቀ የምህንድስና ጥበብ እና ጥልቅ መንፈሳዊነት ማሳያ ናቸው።

በዩኔስኮ (UNESCO) የዓለም ቅርስነት የተመዘገበውና በተለይም በመስቀል ቅርጽ የታነጸው ቤተ ጊዮርጊስ፣ ዛሬም ድረስ መላውን ዓለም በግርማ ሞገሱ ማስደመሙን ቀጥሏል።

ላሊበላ ለኢትዮጵያውያን ቅዱስ የሃይማኖት ስፍራ ብቻ ሳይሆን፣ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብም ድንቅ የጥበብ ማህደር ነው።

ለአለም አቀፉ እንግዳችን ዲላን ፔጅ እና ለሀገር ወዳዱ አዶናይ መልካም የጉብኝት ጊዜ ይሁንላቸው! 🇪🇹

Visit Amhara

Address

Ataya

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00
Saturday 09:00 - 17:00
Sunday 09:00 - 17:00

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ጋዲሎ ሸዋ- Gadilo Shewa tube posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share