Arba Minch Zuria Woreda National Avocado Development Program

Arba Minch Zuria Woreda National Avocado Development Program Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Arba Minch Zuria Woreda National Avocado Development Program, Nonprofit Organization, Arba Minch, Arba Mintch.

ራዕይ፦በአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ የአቮካዶ ልማት ፕሮግራም ጥራት ያለው አቮካዶ በማምረት ለሀገር ውስጥና ለውጭ ገበያ ማቅረብ። አላማ- አርሶአደሮች በክላስተር አቮካዶ በማልማት ምርትና ምርታማነትን ማሳ

ብሔራዊ የአቮካዶ ልማት ችግኝ ተከላ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር  ተከናወነ።አርባ ምንጭ ፦ሐምሌ 13/2018 ዓ.ም (አርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት)፦በጋሞ ዞን አርባ...
20/07/2026

ብሔራዊ የአቮካዶ ልማት ችግኝ ተከላ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ተከናወነ።

አርባ ምንጭ ፦ሐምሌ 13/2018 ዓ.ም (አርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት)፦

በጋሞ ዞን አርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ደጋ ኦቾሎ ቀበሌ ብሔራዊ የአቮካዶ ልማት ችግኝ ተከላ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ተከናውኗል።

አቶ ገዛኸኝ ጋሞ የጋሞ ዞን ዋና የመንግሥት ተጠሪና የብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ፣ አቶ ማጌሶ ማሾሌ የዞኑ ግብርና መምሪያ ኃላፊ፣ አቶ አበበ ፔዣ የአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና የትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መርዶክዮስ ከርባ የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ፣ አቶ መኮንን ተስፋዬ የአቮካዶ ልማት ፕሮግራም ፎካል ፐርሰን እንዲሁም በቀበሌው በኩታ ገጠም የተደራጁ አርሶአደሮች ተሳታፊ ሆነዋል።

በወረዳው ብሔራዊ አቮካዶ ልማት ፕሮግራም በአራት ቀበሌያት በ 8 ክላስተር ለተደራጁ ለ240 አርሶ አደሮች በእያንዳንዱ ግለሰብ 20 እግር የተሻሻለ የሀስ የአቮካዶ ዝርያ ተከላ እንደሚደረግ ተገልጿል።

ቀበሌያቱም ደጋ ኦቾሎ፣ ጋንታ መይጨ፣ ደጋ ሻራ እና ደጋ ጨንጌ መሆናቸው ተብራርቷል።

በዛሬው ዕለትም በደጋ ኦቾሎ ቀበሌ 1,200 የሀስ የአቮካዶ ዝርያ ችግኝ ተከላ በተመረጡ 60 አርሶአደር ማሳ ላይ በኩታ ገጠም ተተክሏል።

የአቮካዶ አበባ በመራገፍ ምክንያቶችና መፍትሄዎቻቸውየአቮካዶ አበባ መርገፍ በተፈጥሮም ሆነ በተለያዩ አካባቢያዊ ምክንያቶች የሚከሰት በጣም የተለመደ ችግር ነው። እንዲያውም አንድ የአቮካዶ ዛፍ...
25/06/2026

የአቮካዶ አበባ በመራገፍ ምክንያቶችና መፍትሄዎቻቸው

የአቮካዶ አበባ መርገፍ በተፈጥሮም ሆነ በተለያዩ አካባቢያዊ ምክንያቶች የሚከሰት በጣም የተለመደ ችግር ነው። እንዲያውም አንድ የአቮካዶ ዛፍ ካወጣው አበባ ውስጥ ፍሬ የሚሆነው ከ 1% ያነሰው ብቻ ሲሆን፣ የተቀረው በተፈጥሮአዊ ሂደት ይረግፋል።
​ነገር ግን ከምጣኔው በላይ ከፍተኛ የባክነንት አበባ መርገፍ ካለ፣ ምክንያቶቹና መፍትሄዎቻቸው የሚከተሉት ናቸው፡

​1. የውሃ እጥረት ወይም መብዛት (Moisture Stress)
​አቮካዶ ለውሃ መለዋወጥ በጣም ተናካሽ ነው። አበባ በሚያወጣበት እና ፍሬ በሚይዝበት ወቅት የውሃ እጥረት ካጋጠመው ራሱን ለመከላከል አበባዎቹን ያረግፋል። በተቃራኒው ደግሞ ከመጠን በላይ ውሃ ማጠጣት ወይም መሬቱ ውሃ የሚያቆር ከሆነ ስሩ ታፍኖ ኦክስጅን ስለሚያጣ አበባና ፍሬ ያረግፋል።
​መፍትሄ፦ አፈሩ ሁል ጊዜ መጠነኛ እርጥበት እንዲኖረው ማድረግ እንጂ ውሃ ማቆር የለበትም። በደረቅ ወቅት ሳምንታዊ የውሃ መርሃ ግብር ማውጣት ይመረጣል።

​2. የአየር ንብረት መለዋወጥ (Temperature and Wind)
​ከፍተኛ ሙቀት እና ቅዝቃዜ፦ አበባ በሚያበቅልበት ወቅት የአየር ሙቀቱ በጣም ከጨመረ (በተለይ ከ 35°C በላይ ከሆነ) ወይም በጣም ከቀዘቀዘ አበባው ይደርቃል ወይም የአበባ ብናኝ (pollen) ስራውን በአግባቡ ሳይወጣ ይቀራል።
​ኃይለኛ ንፋስ፦ ሜካኒካዊ ጉዳት በማድረስ አበባዎችን በቀላሉ ያረግፋቸዋል።

​3. የማዳበሪያ (የንጥረ-ነገር) እጥረት
​አቮካዶ አበባ በሚያወጣበት ወቅት ከፍተኛ ጉልበትና ንጥረ-ነገሮችን ይፈልጋል። በተለይም የቦሮን (Boron), ዚንክ (Zinc) እና ናይትሮጅን (Nitrogen) እጥረት ካለ አበባው ሳይጸንስ የመርገፍ ዕድሉ ሰፊ ነው።

​መፍትሄ፦ አበባ ከመውጣቱ በፊትና በሂደቱ ወቅት ተስማሚ የሆኑ ጥቃቅን ንጥረ-ነገሮችን (Micronutrients) የያዙ ማዳበሪያዎችን በአግባቡ መጠቀም።

​4. የአበባ ብናኝ መሸጋገር (Pollination) ችግር
​የአቮካዶ አበባ ልዩ የሆነ የተፈጥሮ ባህሪ አለው (A እና B ተብለው የሚከፈሉ የአበባ ዓይነቶች አሉት)። አንዱ ክፍል ጠዋት ሲከፈት ሌላኛው ከሰዓት ይከፈታል። በዚህ ሂደት ውስጥ የአበባ ብናኝ የሚያሻግሩ እንደ ንቦች ያሉ ነፍሳት በአካባቢው ከሌሉ አበባው ሳይካሄድ (ሳይጸንስ) ይረግፋል።

​መፍትሄ፦ በንብ ማነብ ስራ ላይ የተሰማሩ ሰዎችን ማበረታታት ወይም ንቦችን የሚስቡ እፅዋትን በአቅራቢያው መትከል።

​5. የበሽታና የተባይ ጥቃት
​እንደ Anthracnose እና Powdery mildew ያሉ የፈንገስ በሽታዎች አበባውንና ግንዱን በማጥቃት አበባው ጠቆርቁሮ እንዲረግፍ ያደርጋሉ። እንዲሁም እንደ Thrips ያሉ ጥቃቅን ተባዮች የአበባውን ጭማቂ በመምጠጥ ያረግፉታል።

​መፍትሄ፦ ምልክቶቹን አስቀድሞ በመከታተል ተስማሚ የፈንገስ ወይም የተባይ ማጥፊያ ኬሚካሎችን በወቅቱ መርጨት።

​በመጨረሻም ዛፉ ወጣት ከሆነ (እድሜው ከ3-4 ዓመት በታች)፣ ፍሬ ለመሸከም አቅም ስለሌለው አበባ ቢያወጣም በብዛት መርገፉ የተለመደ ተፈጥሯዊ ሂደት ነው።

12/06/2026

👌 አቮካዶ ወንዴ እና ሴቴ እንዴት መለየት ይቻላል መሠላችሁ ?

​የአበባውን ባህሪ በመመልከት:
​በማለዳ የአቮካዶ ዛፎችን መመልከት።
​አበባዎች ክፍት ከሆኑ እና የሴቷ ክፍል (የአበባው መሀል ላይ ያለው ትንሽ ብልት) ጎልቶ ከታየ፣ Type A የመሆን እድሉ ከፍተኛ ነው።
​አበባዎች ክፍት ከሆኑ እና የወንዱ ክፍል (የአበባ ዘር የሚለቁት ብናኞች) ጎልቶ ከታየ፣ Type B የመሆን እድሉ ከፍተኛ ነው።
​ከዚያም ከሰዓት በኋላ አበባዎቹን እንደገና ይመልከት።
​ጠዋት ላይ እንደ ሴት የነበሩት አበባዎች አሁን እንደ ወንድ ከከፈቱ (Type A)፣ ወይም ጠዋት ላይ እንደ ወንድ የነበሩት አበባዎች አሁን እንደ ሴት ከከፈቱ (Type B) ይለያሉ።
​ይህንን ለማድረግ ጊዜ እና ትዕግስት ሊጠይቅ ይችላል፣ በተለይም ዛፉ ብዙ አበባዎች ካሉት። በአንድ ጊዜ ላይ ክፍት የሆኑ የአበባዎችን ሁኔታ በጥንቃቄ መመልከት ያስፈልጋል።
🌱​የአቮካዶ ዝርያውን በማወቅ: ብዙ የአቮካዶ ዝርያዎች አስቀድሞ Type A ወይም Type B እንደሆኑ መለየት ይቻላል። 🌱ሌላው ደግሞ ችግኞችን ከገዙበት ቦታ መጠየቅ ወይም የዛፉን ዝርያ ካወቁ በሚከተሉት የተለመዱ ዝርያዎች መለየት ይችላሉ፦
🌱​የተለመዱ Type A ዝርያዎች:
​ሃስ (Hass): በጣም የተለመደው እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቀው። ሲበስል ቆዳው ጥቁር ወይንጠጃማ ይሆናል።
​ሪድ (Reed): ትልቅ፣ ክብ እና አረንጓዴ ሆኖ የሚቆይ አቮካዶ ነው።
​ሜክሲኮላ (Mexicola): ለቅዝቃዜ ታጋሽ፣ ትንሽ እና ለስላሳ ቆዳ ያለው።
​ግዌን (Gwen)
​ላምብ ሃስ (Lamb Hass)
​ፒንከርተን (Pinkerton)
​የተለመዱ
🌱Type B ዝርያዎች:
​ባኮን (Bacon): አረንጓዴ ሆኖ የሚቆይ፣ ቀዝቃዛ የአየር ጠባይ ታጋሽ።
​ፉርቴ (Fuerte): የፒር ቅርጽ ያለው፣ ለስላሳ አረንጓዴ ቆዳ ያለው።
​ዙታኖ (Zutano): የፒር ቅርጽ ያለው፣ የሚያብረቀርቅ ቢጫ አረንጓዴ ቆዳ ያለው።
​ሻርዊል (Sharwil)
​ኤቲንገር (Ettinger)
​ሰር ፕራይዝ (Sir Prize)
​ 🌱🌱🌱በነዚህ ነጥቦችን በመለየት ችግኝ ማዘጋጀት ይቻላል
​የአቮካዶ ዛፎች ፍሬ እንዲሰጡ፣ Type A እና Type B ዝርያዎችን በአቅራቢያ መትከል ይመከራል። ምንም እንኳን አንድ ነጠላ የአቮካዶ ዛፍ ብቻውን ፍሬ ሊሰጥ ቢችልም (በተለይ አየሩ ከፍላጎታቸው ያነሰ ሲሞቅ የአበባ ክፍት ጊዜያቸው ሊደራረብ ስለሚችል)፣ የተሻለ እና ብዙ ፍሬ ለማግኘት ሁለቱንም አይነቶች ጎን ለጎን መትከል የአበባ ዘር ስርጭትን (cross-pollination) በእጅጉ ያሳድጋል። ይህ የሆነው የType A አበባ ሴት ሲሆን Type B ወንድ ስለሚሆን እና በተቃራኒው ስለሆነ ነው

09/06/2026

አቮካዶ እና የአመራረት ሂደቱ✍️

ሀስ (Hass) አቮካዶ በአሁኑ ጊዜ በዓለም ላይ በብዛት የሚመረተውና ለኢትዮጵያም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እያስገኘ ያለ ዝርያ ነው። ይህ ዝርያ ከሌሎች የአቮካዶ አይነቶች የሚለዩት ልዩ ባህሪያት አሉት።

ስለ ሀስ አቮካዶ ማወቅ የሚገቡህ ዋና ዋና ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው፦

1. የሀስ አቮካዶ ለይቶ ማወቂያ ባህሪያት
•ቆዳው፦ እንደ ሌሎች ዝርያዎች ለስላሳ ሳይሆን ሸካራ ነው።
•ቀለሙ፦ ፍሬው ገና በዛፍ ላይ እያለ አረንጓዴ ሲሆን፣ እየበሰለ ሲሄድ ግን ወደ ጥቁር ወይም ጥቁር ሐምራዊ ይለወጣል። ይህ ባህሪው ፍሬው መበሰሉን በቀላሉ ለማወቅ ይረዳል።
•ጣዕሙ፦ በውስጡ ከፍተኛ የቅባት መጠን ስላለው እንደ ቅቤ የመለስለስና በጣም ጣፋጭ የመሆን ባህሪ አለው።

2. ለምን ለኤክስፖርት (ለውጭ ገበያ) ተመረጠ?
ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ይህንን ዝርያ በስፋት እንድታመርት የምታበረታታበት ዋና ምክንያቶች፦
•የመቆየት አቅም (Shelf Life)፦ ቆዳው ወፍራም ስለሆነ በሚጓጓዝበት ወቅት በቀላሉ አይሰነጠቅም ወይም አይበላሽም። ይህም ለረጅም ጉዞ (ለምሳሌ በአውሮፓ ገበያ) ተመራጭ ያደርገዋል።
•ከፍተኛ ምርታማነት፦ በአንድ ዛፍ ላይ ብዙ ፍሬ የማፍራት አቅም አለው።
•ዓለም አቀፍ ተፈላጊነት፦ በአውሮፓና በአሜሪካ ገበያ 80% የሚሆነው የአቮካዶ ፍላጎት የሀስ ዝርያ ነው።

3. የአመራረት ሂደት (መከተብ)
የሀስ አቮካዶ የሚመረተው በመከተብ (Grafting) ዘዴ ነው።
•የአገር በቀል አቮካዶ ዘር ይበቅልና ግንዱ ጠንካራ ሲሆን፣ የሀስ አቮካዶ ቅርንጫፍ (Scion) ተወስዶ በላዩ ላይ ይከተባል።
•ጥቅሙ፦ ተክሉ በሽታን የመቋቋም አቅሙ ይጨምራል፤ እንዲሁም በ 2 ወይም 3 ዓመት ውስጥ ፍሬ መስጠት ይጀምራል። (ተራው አቮካዶ እስከ 7 ዓመት ሊፈጅ ይችላል)።

4. በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ
በኢትዮጵያ በተለይም በደቡብ፣ በኦሮሚያና በሲዳማ ክልሎች በስፋት እየተመረተ ይገኛል። መንግስት "የአረንጓዴ አሻራ" አካል አድርጎ አርሶ አደሮች ይህንን ዝርያ እንዲተክሉ በማድረጉ፣ አገሪቱ አሁን ላይ በአነስተኛ ባቡርና በመርከብ አቮካዶን ወደ አውሮፓ መላክ ጀምራለች።

የሀስ አቮካዶ ተክል ሲንከባከቡ ማወቅ ያለብዎት፦

#ጥንቃቄ፦ የሀስ አቮካዶ ቅዝቃዜን አይወድም። በጣም በረዶማ በሆኑ የደጋ አካባቢዎች ላይ ምርታማነቱ ሊቀንስ ይችላል። እንዲሁም አፈሩ ውሃ የሚያቆር ከሆነ ሥሩ ቶሎ ስለሚበሰብስ ጥንቃቄ ይፈልጋል።

ተስማሚ የአየር ንብረትና አፈር

•ሙቀትና ከፍታ፦ አቮካዶ ሞቃታማና ከፊል ደጋማ (ከባህር ጠለል በላይ 1500 - 2200 ሜትር) ቦታዎችን ይመርጣል።
•አፈር፦ ውሃ የማያቆር፣ ጥልቅና ለም አፈር (Loamy soil) ይፈልጋል። የአፈሩ የ አሲዳማነት መጠን (pH) ከ 5.5 እስከ 6.5 ቢሆን ይመረጣል።
•ውሃ፦ አቮካዶ ከፍተኛ ውሃ ይፈልጋል፣ ነገር ግን ሥሩ አካባቢ ውሃ ከቆመ ቶሎ ይበሰብሳል።

ምርት አሰባሰብና ድህረ-ምርት አያያዝ

•አቮካዶ ከዛፍ ላይ እንደወረደ አይበስልም፤ የሚበስለው ከተቀጠፈ በኋላ ነው።
•ሲቀጠፍ ግንዱን (Stalk) ጨምሮ መቆረጥ አለበት፤ አለበለዚያ ባክቴሪያ ገብቶ ቶሎ እንዲበሰብስ ያደርገዋል።
•ብክነትን መቀነስ፦ ፍሬው እንዳይሰነጣጠቅ በጥንቃቄ መሰብሰብና በቀዝቃዛ ቦታ ማከማቸት ያስፈልጋል።

‎ #ብሔራዊ የአቮካዶ ልማት ፕሮግራም ( ) ሥራ በይፋ ተጀምሯል! #ለ15 አመታት የሚተገበረውን ይህን ፕሮግራም በውጤታማነት በመከወን ከግለሰብ እስከ ሀገር ለመለወጥ እንተጋለን!! #በጸጋ  ...
29/05/2026

‎ #ብሔራዊ የአቮካዶ ልማት ፕሮግራም ( ) ሥራ በይፋ ተጀምሯል!
#ለ15 አመታት የሚተገበረውን ይህን ፕሮግራም በውጤታማነት በመከወን ከግለሰብ እስከ ሀገር ለመለወጥ እንተጋለን!!
#በጸጋ #ብዙ #ምድር #ወደባለጠግነት!
#ቆላ+ #ሙዝ፣
#ደጋ #እፕል፣
#ወ/ደጋ+ #አቮካዶ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ግብርና ቢሮ እና በክልሉ ብሔራዊ የአቮካዶ ልማት ፕሮግራም (NADP) ትብብር በአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ በሚገኙ አራት ቀበሌያት ላይ ለአርሶ አደሮች በአቮካዶ...
25/05/2026

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ግብርና ቢሮ እና በክልሉ ብሔራዊ የአቮካዶ ልማት ፕሮግራም (NADP) ትብብር በአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ በሚገኙ አራት ቀበሌያት ላይ ለአርሶ አደሮች በአቮካዶ አመራረት ዙሪያ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።

ግንቦት 17/2018 ዓ.ም

በወረዳዉ ለመጀመሪያ ዙር በፕሮግራሙ ለታቀፉ 200 አልሚ አርሶ አደሮች ሰለአቮካዶ አመራረት እና ኩታ ገጠም እርሻ በንድፈ ሃሳብ እና በተግባር የተደገፈ ሥልጠና በወረዳና ቀበሌ ባለሙያዎች ተሰጥቷል።

የአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት የፕሮጀክቱ ፎካል አቶ መኮንንን ተስፋዬ ስልጠናዉ ለአከባቢው አርሶ አደር በጣም ጠቃሚና ለወደፊት የአቮካዶ ምርትን ለተለያዩ ለዓለም ገበያ በበቂ መጠን እንድናቀርብ እድል የሚሰጥ ነዉ ብለዋል።

በፕሮግራሙ የታቀፉ አርሶ አደሮች ስልጠናዉን በትክክል በመከታተልና አስልጣኞች የምሰጡትን ስልጠና ትኩረት በመስጠት በማዳመጥ መተግበር ከቻሉ ትልቅ ደረጃ እንደሚደርሱ አስረድተዋል።

በወረዳዉ በክላስተር ላይ የተመሰረተ ጥራት ያለዉ አአቮካዶ በማምረት ለሀገር ዉስጥና ለዉጪ ገበያ በዛላቂነት በማቅረብ ጠንካራና ተወዳዳሪ የአቮካዶ እንዱስትሪ ለመመስረት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

በአቮካዶ እሴት ዙሪያ ለአርሶ አደሮች የተዘጋጀ መድረክ መሆኑንም ጠቅሰዋል።

ከማምረት_በላይ_ነው!!

🥑ብሔራዊ የአቮካዶ ልማት ፕሮግራም🌳 *********** 🌳ውድ የገፃችን ተከታታይ ቤተሰቦቻችን፡- በዛሬው የፕሮግራም እና ፕሮጀክቶች ዝርዝር ገላጭ ፅሁፋችን ብሔራዊ የአቮካዶ ልማት ፕሮግራም/N...
22/05/2026

🥑ብሔራዊ የአቮካዶ ልማት ፕሮግራም🌳

***********

🌳ውድ የገፃችን ተከታታይ ቤተሰቦቻችን፡- በዛሬው የፕሮግራም እና ፕሮጀክቶች ዝርዝር ገላጭ ፅሁፋችን ብሔራዊ የአቮካዶ ልማት ፕሮግራም/National Avocado Development Program (NADP) ይዘንላችሁ ቀርበናል፡፡🥑

🇪🇹🥑ኢትዮጵያ አቮካዶን ለማልማት ከፍተኛ አቅም ያላት ብትሆንም ይህ ንዑስ ዘርፍ እንዳያድግ ማነቆ ከሆኑት ተግዳሮቶች መካከል ዝቅተኛ ምርታማነት፣ ጥራት ያላቸው የግብዓቶች እጥረት፣ የድህረ-ምርት ብክነት እና ደካማ የገበያ ትስስር በዋናነት ይጠቀሳሉ፡፡🌳🇪🇹

🌳እነዚህ ችግሮችን ለመቅረፍ ብሔራዊ የአቮካዶ ልማት ፕሮግራም ተቀርፆ ወደ ስራ ተገብቷል፡፡ እ.ኤ.አ ከጥቅምት 2025 እስከ ጥቅምት 2040 ተግባራዊ የሚደረገው ይህ ፕሮግራም ዋና ዓላማውም የአቮካዶ ምርታማነትን በማሻሻል፣ የድህረ-ምርት-ብክነትን በመቀነስና የገበያ ትስስርን በማጠናከር የአቮካዶ ንዑስ ዘርፍን ትራንስፎርም ማድረግ ነው፡፡ የገንዘብ ምንጩም መንግስት ነው፡፡🥑

🥑ፕሮግራሙ 4 ዋና ዋና ክፍሎች ያሉት ሲሆን እነዚህም፡- የአቮካዶ ምርትና ምርታማነትን ማሻሻል፣ የድህረ-ምርት ብክነትን መቀነስና ጥራትን መጠበቅ፣ የግብይት ስርዓትንና መሰረተ-ልማትን ማጠናከር እንዲሁም አቅም ግንባታና ተቋማዊ አሰራርን ማጠናከር ናቸው፡፡🌳

🌳ይህ ፕሮግራም የሚተገበረው ዋና ዋና የአቮካዶ አምራቾች እና እምቅ አቅም ባላቸው ኦሮሚያ፣ አማራ፣ ደቡብ ኢትዮጵያ፣ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች፣ ሲዳማ፣ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ ትግራይ፣ ሀረሪ እና ጋምቤላ ክልሎች ላይ ነው። በ157 ወረዳዎች ውስጥ በመንግስት በጀት ድጋፍ ይተገበራል።🥑

🥑በፕሮግራሙ ሰፊ ተጠቃሚዎች ያሉት ሲሆን አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች ወደ 3 ሚሊዮን የሚደርሱ፣ የአግሮ-ፕሮሰሲንግ ኢንተርፕራይዞች/ኢንዱስትሪዎች ወደ 700 የሚደርሱ፣ በእሴት ሰንሰለት ውስጥ የሚሳተፉ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት፣ የምርቱ ተጠቃሚዎች፣ ወጣቶችና ሴቶች 977,182 ለሚሆኑ፣ የመንግስት ተቋማት እንዲሁም በምርምር፣ በስልጠናና ኤክስቴንሽን አገልግሎት ላይ የተሰማሩ ባለሙያዎች ናቸው፡፡🌳

🌳🇪🇹በአጠቃላይ ሀገራችን የምርምር እንዲሁም የስልጠናና ኤክስቴንሽን ስርዓትን አቅም በማሳደግ፣ የገቢና የሥራ ዕድልን በማሳደግ፣ የምግብ ዓይነትና ስርዓተ-ምግብን በማሻሻል፣ ዘላቂ አካባቢያዊ ደህንነትን በማጠናከር፣ ብቁ የሰው ኃይል ልማትን በመገንባት እና የውጭ ምንዛሬ ገቢን በመጨመር ከፕሮግራሙ ተጠቃሚ ትሆናለች።🥑🇪🇹

#ከማምረትበላይ

-------------------------
በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ስለግብርና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት👇

📌ድረ-ገጽ፦ www.moa.gov.et
***********
📌ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/MoAEthiopia
***********
📌ዩቲዩብ፦ https://youtube.com/-ethiopia
***********
📌ቴሌግራም፦ https://t.me/MoAEthiopianews
***********
📌ቲዊተር፦ https://x.com/MoA_Ethiopia
***********
📌ሊንክድኢን፡- https://shorturl.at/7O6cs
***********
📌ቲክቶክ፦ http://www.tiktok.com/
***********
📌ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/moa_ethiopia/

22/05/2026

የአቮካዶ ምርት ለቤተሰብ የምግብ እና የስነ-ምግብ ዋስትና: እንዲሁም ለገጠርና ለከተማ ወጣቶች የሥራ ዕድል በመፍጠር ለኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማት ጉልህ አስተዋፅኦ የሚያበረክትና ከፍተኛ ትኩረት የሚፈልግ የግብርና ዘርፍ ነው፦ ክቡር ዶክተር መሪሁን ፍቅሩ

የክልሉ ብሔራዊ የአቮካዶ ልማት ፕሮግራም -ስቲሪንግ ኮሚቴን በበይኔ-መረብ ስብሰባ አካሂደዋል።

.

የአቮካዶ ምርት ለቤተሰብ የምግብ እና የስነ-ምግብ ዋስትና:እንዲሁም ለገጠርና ለከተማ ወጣቶች የሥራ ዕድል በመፍጠር ለኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማት ጉልህ አስተዋፅኦ የሚያበረክትና ከፍተኛ ትኩረት የሚፈልግ የግብርና ዘርፍ ነው ሲሉ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት በምክትል ርዕሰ-መስተዳድር ማዕረግ የዲላ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ ክቡር ዶክተር መሪሁን ፍቅሩ ገለጹ።

ኃላፊው ይህንን የተናገሩት የአቮካዶ ሀብት ልማት ላይ የሚመክር የክልሉን ብሔራዊ የቮካዶ ልማት ፕሮግራም ስቲሪንግ ኮሚቴ ጋር በበይኔ-መረብ ያካሄዱትን ስበሰባ በመሩበት መድረክ ነው።

ኮሚቴው ክልሉ ያለውን የአቮካዶ ፖቴንሽያል ወይም የማምረት አቅም አሟጦ መጠቀም በሚያስችሉ አሠራሮችና ልያጋጥሙ በሚችሉ ተግዳሮቶችና መፍትሄዎች በጥልቀት ተወያይቷል፤ አስቻይ አቅጣጫዎችንም አስቀምጧል ።

አቮካዶን ከሀገር ውስጥ ፍጆታ ባሻገር ዋነኛ የውጭ ምንዛሬ ምንጭ ማድረግና ለዚህም ዓላማ ስኬት የውጭ ገበያ ፍላጎትና ደረጃን በሚያሟላ ጥራትና ብዛት ማምረት እንዲሁም የእሴት ሠንሠለት መፍጠር፣ መጠነ-ሰፊ ምርጥ ዘር ማቅረብ የዘርፉ ቀጣይ ትኩረቶች እንዲሆኑ የወሰነው ስቲሪን ኮሚቴው የበጀት ድልድልም አጽድቋል ።

በበይኔ-መረብ በተካሄደው ክልላዊ የአቮካዶ ስቲሪንግ ኮሚቴ ስብሰባ የደቡብ ኢትዮጵያዊ ክልል ምክትል ርዕሰ-መስተዳድርና የአርባምንጭ ክላስተር አስተባባሪ እንዲሁም የሥራና ክሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር ዶክተር አበባየሁ ታደሠን ጨምሮ ሁሉም የኮሚቴው አባላት መሣተፋቸው ተዘግቧል።

''በየተሠማራንበት ዘርፍ አንድነትና አብሮነታችንን አጠናክረን ለሃገራችን ዴሞክራሲ እድገትና ሁለንተናዊ ብልጽግ ያለመታከት እንትጋ ‼️'' ክቡር ዶክተር መሪሁን ፍቅሩ

Address

Arba Minch
Arba Mintch
0000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Arba Minch Zuria Woreda National Avocado Development Program posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share