Kingdom First Youth Ministry

  • Home
  • Kingdom First Youth Ministry

Kingdom First Youth Ministry ይህ ፔጅ የመንግስቱ ወንጌል ስራዎችን በፅሑፋና በምስል ቆይታችንን የምንገልፅበት ፔጅ ነው። ጌታ የሰጠንን ራይ ከትውልድ አብረን እንሰራለን

Awasa  campus
26/12/2025

Awasa campus

ፀጋን ይካፈሉ
18/10/2025

ፀጋን ይካፈሉ

ዋዜማ ላይ ነን !!175 ገፅ 9 ምዕራፎች ዋዜማ ዋናውን የበአሉን እለት ሙሉ በሙሉ ሊተካም ሆነ ሊገልጥ አቅም የለውም ። ዋዜማ እድል ነው ። ዋዜማውን በቅጡ ያልተጠቀመ ደጋሽ በእለቱ ላይ በ...
19/08/2025

ዋዜማ ላይ ነን !!
175 ገፅ
9 ምዕራፎች

ዋዜማ ዋናውን የበአሉን እለት ሙሉ በሙሉ ሊተካም ሆነ ሊገልጥ አቅም የለውም ። ዋዜማ እድል ነው ። ዋዜማውን በቅጡ ያልተጠቀመ ደጋሽ በእለቱ ላይ በሚታየው ክፍተቶችና ጉድለቶች ሳቢያ በታዳሚው ዘንድ የሚወቀስ እና የሚነቀፍ ይሆናል ።
ምስክርነት
ምስክርነት ማለት መስዋትነት ማለት ነው ።
ምስክርነት የራስ ወዳዶች ህይወት አይደለም ። ራሱን የሚወድ ሰው ለምስክርነት ብቁ መሆን አይችልም ። ለምን ቢባል ምስክርነት ራስን ስለ ሌላው ለጉዳት አሳልፎ መስጠትን ይጠይቃልና። ስለሆነ አንድ አማኝ በምክርነት ህይወት ውስጥ ካልተገኘ መገኛ አድራሻው ራስ ወዳድነት ሰፈር ውስጥ ነው ።
ወደ ጌታ ለመሄድ መናፈቅ ከእግዚአብሔርም ሆነ ከሰው ጋር ላሉብን ግጭቶች መፍትሔና ፍቱን መድሃኒት ነው።
መሄድ ለሚናፍቅ ሰው አሁን ስላለበት ክብርም ሆነ ውርደት ሁኔታ ዘገባና ትንታኔ ከመስጠት ይልቅ ጊዜያዊ መሆኑ በመረዳት ዘላለማዊው ላይ ያተኩራል ።
" በራሴ ቋንቋ የፃፍኩት የፅሀፊውን ሀሳብ "
በምንጠብቀው ሪቫይቫል በእኛ ሰዎችን ይፈውሳል ማለት ብቻ ሳይሆን እኛንም ይፈውሳል ማለትም ጭምር ነው ።
ብዙ ግዜ መንፈስ ቅዱስ አስለወጠኝ እያሉ ለሚያገለግሉ ጥሩ ምላሽን ሰጦናል ቤታችን ለፕሮግራሙ ከፀለይን ጌታ ጉባኤውን ስለሚያውቀው ይነግረናል ግን ሳንፀልይ በልምድ መጠን ከሆነ እቤት ስላጣን ጉባኤ ላይ ሊነግረን ይችላል ብሎናል ተስማምቻለሁ ።
" ተስፋ ማለት የጀመርነውን የምንፈፅምበት ያልጀመርነውን ደግሞ የምንጀምርበት ጉልበት ነው " ይለናል
አንድ ሰው ጸልዮም ሆነ ተጸልዮለት ከሚቀበለው የጸሎት መልስ ይልቅ በግሉ ከእግዚአብሔር ጋር ሕብረት ማድረጉ ነው ትልቅ ።
እግዚአብሔር ለማወቅ በግል ከእርሱ ጋር ህብረት ማድረግን የሚጠይቅ ሲሆን ስለ እግዚአብሔር ለማወቅ ግን መረጃን ማሰባሰብ ብቻ የሚጠይቅ ነው ።
እግዚአብሔር ለጥያቄዎቻችን መልስ ለመስጠት የሚኖር አምላክ ሳይሆን ከልጆቹ ጋር ህብረት ማድረግን የሚናፍቅ አምላክ ነው ።
ወደ እግዚአብሔር ስንቀርብ ከሚያማምሩ ቃላቶች ይልቅ ንፁህ ልብን ይሻል።
ሐዋርያው ጳውሎስ በወንጌል ያልወለደውን ልጅ ወንድም ብሎ እንጂ ልጄ ብሎ አይጠራም ። ዘመናችንስ ምን እያለን ይሆን
ከራሴ ❤.ስጨምር ዛሬ ዛሬ በርቀት እንኳን እንዴት እንደሆና ባይታወቅም ተዋልደዋል ??
ዛሬ ዛሬ የቤተክርስቲያን መሪዎች ለመንጋዎቻቸው የሚሆን ግዜ የላቸውም ለሁሉም መንጋ አይደለም ለድሆች ማለቴ ነው ።
ሰው ፈጣሪ አምላክ ያለው ፍጡር ብቻ ሳይሆን የተፈጠረበት አላማ ያለው ፍጡር ጭምር ነው ።
እግዚአብሔር እንደሆነ ሆደ ቡቡ አባት ልጆቹ ምንም እንዳየነካበት ጥግ ጥጉን የሚያስኬድ ብቻ ሳይሆን በመከራም ውስጥ እንዲያልፉ በመፍቀድ አብሮ የሚሆን ጭምር ነው ።
መንፈሳዊ ትምህርት የህይወትን ለውጥ ካላስከተለ የመረጃ ልውውጥ ብቻ ነው የሚሆነው። እግዚአብሔር የሚለፍፍ አፍ ሳይሆን የሚታዘዝ ልብ ነው የሚፈልገው ።
መታዘዝ ከሌለበት ሩጫ መታዘዝ ያለበት እርምጃ ይበልጣል ። በእግዚአብሔር ዘንድ የሚሸለመው የሮጠ ሁሉ ሳይሆን መስመሩን ጠብቆ የሮጠ ነው። እግዚአብሔር በሰጠው እድል ደህና አድርጎ ከማገልገል ይልቅ ከዝግጅት ማነስ እና መድረኮችን ከመለማመድ የተነሳ የብዙ ሰው አገልግሎት ደህና ሳይሆን መናኛ ሆኖ የሚቀርብበት ሁኔታ ብዙ ነው።
በጥንቃቄ ካልተመለከቱት በቀር ምልክት ወደ ዋናው መልዕክት ለማድረስ በማንደርደር ከማገልገል ይልቅ እንቅፋት ሆኖ ይከላከላል።
ምልክቱን ያለፈ ብቻ መልዕክቱን ያገኛል ።
እምነት በራሱ ኃይል ሣይሆን ከኃይል ምንጭ ጋር መገናኛ ነው። ከእምነት ውጪም ከእግዚአብሔር ጋር መገናኛ ሌላ የለም።
አንድ ሰው ከእግዚአብሔር ዘንድ የሆነ ነገር ማግኘት እንደ ሚፈልግ ሁሉ እግዚአብሔርም ከዛ ሰው እምነት ይፈልጋል ።

መጋቢ ኃይሉ ጌታሁን
መልካም መለክቶችን የያዘ መፅሐፍ ስለፃፍክልን እናመሰግናለን !!

Tilahun Mamo:ዛሬም ለትውልድ ባለን ሸክም የቻልነውን እያደረግን ነው ወዳጆቼ እናንተስ የምትችሉትን ለማድረግ ብትዘረጉ !!ስጦታ ለልህቀት !!❤ለልህቀት የንባብ ማዕከል የሚችሉትን ይለግ...
11/03/2025

Tilahun Mamo:
ዛሬም ለትውልድ ባለን ሸክም የቻልነውን እያደረግን ነው ወዳጆቼ እናንተስ የምትችሉትን ለማድረግ ብትዘረጉ !!

ስጦታ ለልህቀት !!❤
ለልህቀት የንባብ ማዕከል የሚችሉትን ይለግሱ !!
በገንዘባችሁ መደገፍ የምትፈልጉ
Telebirr +251911502867
CBE 1000360229158
Dashen bank 0012102344011
Abyssinia 79067377
Awash bank 01308867863500
Berhan bank 1601610043561

የምትችሉትን
አንድ ኩንታል ሲምንቶ 1200 ብር
ቴራዞ በካሬ 500 ብር
ነው ታዲያ በሚችሉት አብረውን ቢቆሙስ !!
ከቻሉ መጠው ይጎብኙ !!

ዛሬ ከሰዓት ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ በጎተራ ማሳለጫ  ክረምቱን እና በቆሎውን እየተሰናበትን ንባባችንን ግን እንቀጥል ብለን ልንመክር ነው ታዲያ እርስዎ የት ነዎት?? በምክንያት የሚያምን ትውል...
12/10/2024

ዛሬ ከሰዓት ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ በጎተራ ማሳለጫ ክረምቱን እና በቆሎውን እየተሰናበትን ንባባችንን ግን እንቀጥል ብለን ልንመክር ነው ታዲያ እርስዎ የት ነዎት??

በምክንያት የሚያምን ትውልድ ለመፍጠር ብቸኛው መንገድ አንባቢ ትውልድ መገንባት ነው ታዲያ አንዱ መፍትሔ ልህቀትን መደገፍ ነው ።
" ሃምሳ ሎሚ ለአንድ ሰው ሸክም ለሃምሳ ሰው ግን ጌጥ ነው " ይባላል በሉ ጌጥ አድርጉልን በምትችሉት አቅም ።

በገንዘባችሁ መደገፍ የምትፈልጉ
Telebirr +251911502867
CBE 1000360229158
Dashen bank 0012102344011
Abyssinia 79067377
Awash bank 01308867863500
Berhan bank 1601610043561

20/09/2024



እግዚአብሔር ሁልጊዜ ለአገር ለቤተክርስቲያን ለቤተሰብ መሪን ይሰጣል። እግዚአብሔር መሪዎችን በመስጠት በረከትን ይሰጣል። እግዚአብሔር መሪዎችን በመስጠት የሚታወቅ አምላክ ነው። እግዚአብሔር ሲባርክህ ትክክለኛ መሪን ይሰጠናል። እግዚአብሔር የሚመራን በሚሰጠን መሪዎች ጭምር ነው። ጤናማ መሪ ያላት ቤተክርስቲያን እና ሃገር የተባረከች ናት።

መሪ የራሱ ስነ ምግባር አለው። መሪ ከእግዚአብሔር የተገኘ ምንም ቢሆን እንኳ መሪዎች ስነ ምግባር ሊኖረው ይገባል። መሪ የስነ ምግባር መርሆችን ካልተከተለ የሚመራው ተቋም ላይ መከፋፈልና፣ አለማደግን ይመጣል።

የመሪ ስነ ምግባር ከሌለ ውጤት የለም። በጸጋ ብቻ የሚመጡ ውጤቶች ዘላቂ አይሆኑም ጸጋውን ይዘን የምንቀጥልበት የበሰለ መሪነት ያስፈልገናል፣ ስነ ምግባር ከሌለ እውነተኛ ለውጥ የለም። መሪነት ከእግዚአብሔር የሚሰጥ ጸጋ ሲሆን፣ ራሳችን ላይ በመስራት የምናሳድገው ጭምር ነው። የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን አንደኛው ተግዳሮች በስነ ምግባር የታነጹ መሪዎች ጉድለት ነው። ስነ ምግባር ማለት እግዚአብሔር ለሰጠን የመሪነት አደራ ራሳችንን በእግዚአብሔር ቃልና በበሰለ አመራር የምናበቃት መንገድ ማለት ነው።

እንከን አልባ መሪ የለም። አይኖርምም። አንድ እንከን አልባ መሪ ኢየሱስ ብቻ ነው። ነገር ግን ዕለት ዕለት ራሳችን ላይ በመስራት በተሰጠንን አደራ ራሳችንን በማብቃት ከሰራን፤ ጥሪው ካለንና ጥሪያችንን ካሳደግን ውጤታማ መሪ እንሆናለን።

መሪ ስነ ምግባር አለው ስንል ከመሪ የሚጠበቁ መሰረታዊ ነገሮች አሉ ማለታችን ነው። መሪ ቀዳሚ እንደመሆኑ ምሳሌ መሆንና ለሚመራቸው ትክክለኛ መሪ መሆን አለበት። እስቲ በጥቂቱ የመሪ ስነ ምግባር የሆኑትን እንመልከት።

የመሪ ስነ ምግግባር

1፣ መሪ ይቅርታ አይራጊ ነው። መሪ ምሬትና ጥላቻ የተሞላ መሆን የለበትም። መሪ በተለያዩ ሰዎች ከቅርብም ከሩቅም፣ በውሸት፣ በመከዳት ጥለውት በሚሄዱ ሰዎች፣ በተለያዩ መንገድ ውስጥ ሊያልፍ ይችላል። መሪ በይቅርታ ለመመላለስ ራሱን ማዘጋጀት አለበት። መሪነት ሰዎች ብዙ በደል በመሪው ላይ የሚፈጽሙበት ስፍራ ነው፣ ይቅርታ ለማድረግ ካልፈቀደ መሪነቱን ቢለቅ ይሻለዋል። ስለዚህ ከመሪ መለየት የሌለበት ይቅርታ ማድረግ ነው።

2፣ አመስጋኞች መሆን አለብት። መሪ እግዚአብሔር ስለ ሰጠው ሰዎች፣ ስለ ተሰራው ስራ፣ በአገልግሎቱ ወይም በሚያስፈልገው ነገር አብረውት ስለቆሙ ሰዎች ተገቢ ምስጋና መስጠት አለበት፣ ከምንም በላይ አምላኩን አመስጋኝ መሆን አለብት። ማጉረምረምና መሳበብ መሞላትም የለበትም። ሰዎች ስላደሰጉለት ጥቂት ነገር አመስጋኝ የሆነ መሪ ውጤታማ መሪ ነው።

3፣ ትሁት መሆን አለበት። ከመሪ ህይወት የሚጠቀቀው ሌላኛው ነገር ትህትና ነው። ሁለቱ መሪዎች ማለትም ኢየሱስ እና ሙሴ ትሁቶች ነበሩ። ትህትና ለመሪነትን ሞገስ የሚጨምር በንግግር እና በስብከት ብቻ የማይገለጥ ነገር ግን በመኖር የሚታይ ህይወት ነው ትህትና። እግዚአብሔር ትሁት መሪዎችን ይስጠን።

4፣ አማኝ መሆን መቻል አለበት። መሪ በምንም መንገድ ውስጥ ቢያልፍ በእግዚአብሔር ማመን እና ለሚመራቸው እምነቱን ማጋራት አለበት። መሪው ያላመነውን ነገር ሌላው እንዲያምነው አይጠበቅም። ማለትም መሪው ያልኖረውን ህይወት ሌሎች እንዲኖሩት ግድ አይባልም።

5፣ የጸሎት ሰው መሆን አለበት። መንፈሳዊ መሪ የጸሎት ሰው፣ የራሱም ለሚመራት ቤተ ክርስቲያን እና ለምዕመናን፣ ለአገልግሎቱ ጭምር የሚጸልይ መሆን አለበት። መሪ የምዕመኖቹን መንፈሳዊ ህይወት በጸሎት ወደ እግዚአብሔር የሚያቀርብ፣ በድምጽ ምዕመናኑን የሚመራ ነው። የማይጸልይ መሪ አገልግሎቱን በትግልና በሰው ምድራዊ ጥበብ ይመራል።

6፣ መሪ ሰጪ ነው። የመጽሐፍ ቅዱሱ መሪ የምናውቀው ሰጪ ነው። ንፉግነት የመሪ መገለጫ አይደለም። መሪ ገንዘቡን፣ ጊዜውን ያለውን ነገር ሁሉ የሚሰጥ ነው። መቀበል ላይ የተመሰረተ አስተምህሮ መጽሐፍ ቅዱሳዊ አይደለም፣ በመስጠት ውስጥ ያለ መቀበል እንጂ። መሪ ሰጪ ሲሆን እግዚአብሔር በሚሰጡት ሰዎች ይባርከዋል።

7፣ መሪ ትጉህ ነው!! መሪ ብሎ ሰነፍ ከሆነ አረም የሞላበት ተክል የሚጠብቅን ጠባቂ ይመስላል። መሪ ትጉህ ካልሆነ በመንጋው መካከል፣ አረም፣ ያልተገባ ነገር ይኖራል። ስንፍና ምንባቸው ይሆናል። ምክንያት እየፈጠረ ከሐላፊነት የሚሸሽ መሪ አይደለም። መሪ ትጉህ ነው፣ በተሰጠው ነገር በመትጋፍ ፍሬያማ ነው። የመሪ ሐብቱ ያቀደውን ነገር ለማስፈጸም መትጋቱ ነው። ምክንያት ደርዳሪነትና ስንፍና የመሪ መገለጫዎች አይደሉም።

8፣ መሪ የፍቅር ሰው ነው። መሪ የፍቅር ሰው መሆን ይጠበቅበታል። መንፈሳዊ መሪ ሲሆን ደግሞ ዋናው መሪ ኢየሱስ የፍቅር ሰው እንደ መሆኑ የእርሱ ፈለግ የተከተለ መሪ መሆን አለበት። መሪ ሁሉም ሰው ሊወደው አይችልም፣
ነገር ግን ሁሉን የመውደድ ግዴታ ግን አለብን። መሪ ከፍቅር ከጎደለ አመራሩ ሁሉ የወደቀ ይሆናል። የመሪነት ዋነኛው ቁልፉ ፍቅር ነው።

9. ሌሎችን የሚያነሳሳ ነው። መሪ የሚመራቸውን አካላት ለተሻለ ስራና አገልግሎት የሚያነሳሳ መሆን አለበት። ሌሎች መሪዎች ወደ መሪነት እንዲመጡ የሚያነሳሳ፣ ምዕመናኑን ለተለያዩ መንፈሳዊ ሐላፊነቶች እንዲበቁ የሚያነሳሳ መሆን አለበት። ትክክለኛ መሪ ሌሎች ለስራ ሲነሳሱ ደስተኛ ነው።

10፣ መሪ ሌሎችን አክባሪ ነው!! የማያከብር ሰው አይከብርም፣ ሌሎችን የሚያጣጥልና የሚያናንቅ መሪ ነገ በተከታዮቹ ያ ዕጣ ይደርሰዋል። መሪ የሚቀበለው ሁሌም የሰጠውን ነውና። ሰዎችን ባወቅን ቁጥር ማክበር ይበልጣል። ማክበር የመሪ ባህሪ ነው። የሚያከብር መሪ የሚከባበሩና፣ የሚያከብሩት ምዕመናንን ያበዛል። አገልጋዮችን ላይ የሚቀልዱ፣ በመንፈሳዊ ነገር የሚሳለቁ መሪዎች ልቅ ትውልድ ያፈራሉ። መሪ አክባሪ ነው።

11፣ መሪ መልካም ምክር ሰጪም ተቀባይም ነው። መሪ ለሚመራቸው መልካም ምክርን ይሰጣል። ምክርን በተገቢው ቦታ ለተገቢው ሰው ይሰጣል። ከሌሎች ምክርን ይቀበላል። ምክርን ላለመቀበል ግትር አይደለም። ጠቃሚ ምክሮችን ለመቀበል ትሁት ነው።

12 መሪ ገበና ሸፋኝ ነው!! መሪ በሚመራቸው ምዕመናን ህይወት የሰማውን ነገር ለስብከት ማጣፈጫ አያደርግም፣ ለሌሎች ለማይመለከታቸው የሰዎችን ማንኛውን ገመና አደባባይ አያሰጣል። መሪ ገመና ሸፋኝ ነው።

13, መሪ አንባቢ ነው፣ መሪ ራሱን ላይ በንባብ እና በትምህርት የሚሰራ ነው። ትናንት የተረዳውን ሰምቶ የመጣን ትውልድ የትናንቱን ስብከት በመደጋገም አያጸናውም። ከዚያ ይልቅ ቃሉን ያነባል ይቆፍራል። ያስተምራል፣ ይመራል።

"ቤተ ክርስቲያን ቴአትር ቤት፣ እኛም ኮሜዲያን ሆነናል!"ብዙ አማኝ ወደ ቤተ ክርስቲያን የሚመጣው ለመዝናናት ነው። ሌላውም ሰው ጆክ ሲያምረው፣ መሳቅ ሲፈልግ የእኛን ቪዲዮዎች ነው የሚያየው።...
01/08/2024

"ቤተ ክርስቲያን ቴአትር ቤት፣ እኛም ኮሜዲያን ሆነናል!"

ብዙ አማኝ ወደ ቤተ ክርስቲያን የሚመጣው ለመዝናናት ነው። ሌላውም ሰው ጆክ ሲያምረው፣ መሳቅ ሲፈልግ የእኛን ቪዲዮዎች ነው የሚያየው። በኢየሱስ ስም፣ በልሳን፣ በጸሎት ከት ከት ብሎ ይስቃል። እኛም አብረን እንስቃለን። ምንም ስለማይመስለን ቪዲዮውን እየተቀባበልን እንስቃለን። የእግዚአብሔር ስም መቀለጃ ስለሆነ የሚያየው አይፈራው፣ የሚሰማን አይፈራው። እኛም አላከበድነው በሚገባ አላሳየነው፣ አልገለጥነው፣ አላመጣነው...።

የአብዛኞቻችን አገልጋዮች ዓላማ ራሱ ሰውን ማዝናናት ነው፤ "ምን ብናገር አዝናናዋለሁ ነው።" የብዙ ምዕመናን የቤተ ክርስቲያን፣ የስብከትና የአገልግሎት ምርጫ "የት ብሄድ ያልተካበደ ነገር እሰማለሁ"፣ "መዝናናት አገኛለሁ" የሚል ነው። ቤተ ክርስቲያን ቴአትር ቤት፣ እኛም ኮሜዲያን ሆነናል።

ተዉ እንጂ ብዙም ሩቅ ባልሆኑ ዓመታት፣ የዛሬ ሰልሳ ዓመት ወደ ኃላ "ሪዋይንድ" ብታደርጉ አማኞች የሚፈራ ምገስ ነበራቸው። ሰዎቹ ዛሬም በሕይወት ስላሉ ሄዳችሁ ጠይቋቸው። በቤተ ክርስቲያናቸው ደጃፍ ማለፍ እንኳ ያስፈራ ነበር። ሕይወታቸው ግርማ ነበረው። መልዕክታቸው አስደንጋጭ ነበር። ለማስደንገጥ ብለው ሳይሆን እግዚአብሔር በመካከላቸው ነበር።

እዚያ ለመቀለድ አትሄድም፤ ንሰሐ እንጂ ጆክ ትዝ አይልህም። አጋንንት ይወጣል፣ ሰዎች ይፈወሳሉ። የእግዚአብሔር ቃል፣ የክርስቶስ ወንጌል ይሰበካል። ይኼ ሁሉ የሚሆነው ፐርፌክት [ፍጹማን] ክርስቲያኖች ስለሆኑ አይደለም። ግን የኢየሱስን ስም አስከባሪዎች ነበሩ።

አሁን ቢያንስ ስሙ በሆነ መንገድ ይከበር ዘንድ ብንጸልይስ? ቢያስፈልግ ኮሜዲያኖቹን በጊዜ ቢወስደን፤ ይኼም እኮ አንዱ መንገድ ነው። ወይም ደግሞ ጥግ አስይዞን የሆኑ ሌሎች ሰዎች ቢያመጣ፣ እኛ ዕድሉን አልጠቀም ስላልን ሌላን ትውልድ ቢያስነሳልን፣ ስላላየናቸው እንጂ እግዚአብሔር ስሙን የሚያስከብሩለት ልጆች አሉታ!...

በዚህ ዘመን ወንጌል የምንሰብክበት ብዙ መድረክ አግኝተን፣ ሚዲያ ተመቻችቶልን አልተጠቀምንበትም። በየሰዉ ቤት የጌታን ስም ተሸክመን ለመግባት እንደዚህ ዘመን ዕድል ተሰጥቶን ያውቃል እንዴ? እኛ ግን ጆካችንን ይዘን ገባንበት፤ እግዚአብሔርን መሳለቂያ አደረግነው። ስለዚህ ወገኖቼ በአሕዛብ መካከል የተነቀፈው ማንነቱ የቀለለው ስሙ መልሶ እንዲከብድ በየትኛውም መንገድ ምክንያት ለመሆን መጸለይ አለብን።

ዶ/ር ማሙሻ ፈንታ

ሰላም ወዳጆቼ ልህቀት የሚያዘጋጀው የመፅሐፍ ዳሰሳ ዘወትር አርብ ከምሽቱ 3::0ዐ ሰአት ጀምሮ በቀጥታ በቴሌግራም ይከታተሉ !! እርግጠኞች ነን እንደሚጠቀሙ ደግሞ ለሌላው እንዲደርስ ደግሞ በ...
11/04/2024

ሰላም ወዳጆቼ ልህቀት የሚያዘጋጀው የመፅሐፍ ዳሰሳ ዘወትር አርብ ከምሽቱ 3::0ዐ ሰአት ጀምሮ በቀጥታ በቴሌግራም ይከታተሉ !! እርግጠኞች ነን እንደሚጠቀሙ ደግሞ ለሌላው እንዲደርስ ደግሞ በመልካም ፍቃድዎ ሼር ያድርጉት ።

በዱባይ ያላችሁ ወዳጆቼ ጌታ ቢፈቅድ የፊታችን ቅዳሜ የእግዚአብሔር ፀጋ እንድትካፈሉ በአክብሮት ጋብዣለሁ !!
21/03/2024

በዱባይ ያላችሁ ወዳጆቼ ጌታ ቢፈቅድ የፊታችን ቅዳሜ የእግዚአብሔር ፀጋ እንድትካፈሉ በአክብሮት ጋብዣለሁ !!

በአዋሳ ላላችሁ ቅዱሳን ዛሬን ከእኛ ጋር ይሁኑ !! እንማራለን ደግሞም እንፀልያለን ጌታ መልካም ያደርጋል !!
04/01/2024

በአዋሳ ላላችሁ ቅዱሳን ዛሬን ከእኛ ጋር ይሁኑ !! እንማራለን ደግሞም እንፀልያለን ጌታ መልካም ያደርጋል !!

ዛሬ ማታ እለተ አርብ እንደተለመደው ከምሽቱ 3:00 ጀምሮ ይህን ድንቅ መፅሐፍ እንወያይበታለን  ስለዚህ በሰአቱ በቴሌግራም በቀጥታ በመግባት ይከታተሉ። https://t.me/Lihket_Read...
29/12/2023

ዛሬ ማታ እለተ አርብ እንደተለመደው ከምሽቱ 3:00 ጀምሮ ይህን ድንቅ መፅሐፍ እንወያይበታለን ስለዚህ በሰአቱ በቴሌግራም በቀጥታ በመግባት ይከታተሉ።

https://t.me/Lihket_Reading
join

ልህቀት ቤተ መፅሐፍ

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kingdom First Youth Ministry posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

  • Want your organization to be the top-listed Non Profit Organization?

Share