Gununo Ketema Stadium KHC Youth Ministry

Gununo Ketema Stadium KHC Youth Ministry Youth ministry

02/08/2026

ኤፌሶን 2:8፤ ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፤

ይጠቅማል ይነበብ #የመጽሐፍ ቅዱስ 66 መጻሕፍት – አጭር ማብራሪያ #ብሉይ ኪዳን (39) #ዘፍጥረት – የፍጥረት፣ የሰው ውድቀት እና የአባቶች ታሪክ። #ዘጸአት – እግዚአብሔር እስራኤልን ከ...
23/07/2026

ይጠቅማል ይነበብ
#የመጽሐፍ ቅዱስ 66 መጻሕፍት – አጭር ማብራሪያ
#ብሉይ ኪዳን (39)
#ዘፍጥረት – የፍጥረት፣ የሰው ውድቀት እና የአባቶች ታሪክ።
#ዘጸአት – እግዚአብሔር እስራኤልን ከግብፅ ነፃ አወጣ፤ ሕጉንም ሰጠ።
#ዘሌዋውያን – የአምልኮ፣ የቅድስና እና የመሥዋዕት ሕጎች።
#ዘኍልቍ – በምድረ በዳ የእስራኤል ጉዞና ቆጠራ።
#ዘዳግም – ሙሴ ሕጉን እንደገና ለሕዝቡ ያስተምራል።
#ኢያሱ – የተስፋይቱን ምድር መውረስ።
#መሳፍንት – የእስራኤል ፈራጆች ታሪክ።
#ሩት – የታማኝነትና የቤዛነት ታሪክ።
#1 ሳሙኤል – ሳሙኤል፣ ሳኦል እና ዳዊት።
#2 ሳሙኤል – የንጉሥ ዳዊት አገዛዝ።
#1 ነገሥት – ሰሎሞንና የመንግሥቱ መከፈል።
#2 ነገሥት – የእስራኤልና የይሁዳ ውድቀት።
#1 ዜና መዋዕል – የዳዊት ዘመን ታሪክ።
#2 ዜና መዋዕል – የይሁዳ ነገሥታት ታሪክ።
#ዕዝራ – ከምርኮ መመለስና ቤተ መቅደስ መልሶ መገንባት።
#ነህምያ – የኢየሩሳሌምን ቅጥር መልሶ መገንባት።
#አስቴር – እግዚአብሔር ሕዝቡን ያድናል።
#ኢዮብ – በመከራ ውስጥ ያለ እምነት።
#መዝሙር – የምስጋና፣ የጸሎት እና የአምልኮ መዝሙሮች።
#ምሳሌ – የጥበብ ትምህርቶች።
#መክብብ – ያለ እግዚአብሔር ሕይወት ከንቱ ነው።
#መኃልየ መኃልይ – የፍቅር መዝሙር።
#ኢሳይያስ – ስለ መሲሑ የተሰጡ ትንቢቶች።
#ኤርምያስ – ወደ ንስሐ ጥሪ።
#ሰቆቃወ ኤርምያስ – በኢየሩሳሌም ውድቀት ላይ ልቅሶ።
#ሕዝቅኤል – የፍርድና የተስፋ ራእዮች።
#ዳንኤል – በምርኮ ውስጥ ያለ ታማኝነትና ትንቢት።
#ሆሴዕ – የእግዚአብሔር ታማኝ ፍቅር።
#ኢዮኤል – ወደ ንስሐ ጥሪ፤ የመንፈስ ቅዱስ ተስፋ።
#አሞጽ – ፍትሕን እና ጽድቅን ይጠራል።
#አብድዩ – በኤዶም ላይ ፍርድ።
#ዮናስ – የንስሐና የምሕረት ታሪክ።
#ሚክያስ – መሲሑ በቤተልሔም እንደሚወለድ ትንቢት።
#ናሆም – በነነዌ ላይ ፍርድ።
#ዕንባቆም – በእግዚአብሔር መታመን።
#ሶፎንያስ – የጌታ ቀንና ተስፋ።
#ሐጌ – ቤተ መቅደስን እንደገና መገንባት።
#ዘካርያስ – ስለ መሲሑ ብዙ ትንቢቶች።
#ሚልክያስ – ለጌታ ታማኝ መሆንን ያስተምራል።
#አዲስ ኪዳን (27)
#ማቴዎስ – ኢየሱስ የተስፋው መሲሕ ነው።
#ማርቆስ – ኢየሱስ ኃይለኛ አገልጋይ ነው።
#ሉቃስ – ኢየሱስ የዓለም አዳኝ ነው።
#ዮሐንስ – ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው።
#የሐዋርያት ሥራ – የመጀመሪያዋ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ።
#ሮሜ – በእምነት መጽደቅ።
#1 ቆሮንቶስ – የቤተ ክርስቲያን ሥርዓትና አንድነት።
#2 ቆሮንቶስ – በድካም ውስጥ የክርስቶስ ኃይል።
#ገላትያ – ድነት በጸጋ እንጂ በሕግ አይደለም።
#ኤፌሶን – በክርስቶስ ያለው አዲስ ሕይወት።
#ፊልጵስዩስ – በጌታ ደስታ።
#ቆላስይስ – የክርስቶስ በላይነት።
#1 ተሰሎንቄ – ለጌታ መምጣት መዘጋጀት።
#2 ተሰሎንቄ – ስለ ጌታ ዳግም ምጽአት።
#1 ጢሞቴዎስ – ለቤተ ክርስቲያን መሪዎች መመሪያ።
#2 ጢሞቴዎስ – በእምነት ጸንቶ መቆም።
#ቲቶ – ጥሩ አመራርና መልካም ሥራ።
#ፊልሞና – ይቅርታና እርቅ።
#ዕብራውያን – ክርስቶስ ከሁሉ ይበልጣል።
#ያዕቆብ – እምነት በሥራ ይገለጣል።
#1 ጴጥሮስ – በመከራ ውስጥ ተስፋ።
#2 ጴጥሮስ – ከሐሰተኛ አስተማሪዎች ተጠንቀቁ።
#1 ዮሐንስ – በፍቅርና በእውነት መኖር።
#2 ዮሐንስ – በእውነት መጽናት።
#3 ዮሐንስ – እንግዳ መቀበልና ታማኝነት።
#ይሁዳ – ለእምነት መታገል።
#ራእይ – የክርስቶስ ድል፣ የመጨረሻ ፍርድ እና አዲስ ሰማይና አዲስ ምድር።
ከኦቻ ቃ/ህ/ቤ/ን
Share&Follow

21/07/2026

ሮሜ 1:16፤ በወንጌል አላፍርምና፤ አስቀድሞ ለአይሁዳዊ ደግሞም ለግሪክ ሰው፥ ለሚያምኑ ሁሉ የእግዚአብሔር ኃይል ለማዳን ነውና።

ከእግዚአብሔር አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ሠላም እና ፀጋ ይብዛላችሁ እያልን ዛሬ ማክሰኞ 14/11/2018 ዓ.ሚ ከቀኑ 10:00-1:00 ድረስ በቤተ/ችን አምልኮ አዳራሽ በመጋቢ  #ትእግስቱ  ...
21/07/2026

ከእግዚአብሔር አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ሠላም እና ፀጋ ይብዛላችሁ እያልን ዛሬ ማክሰኞ 14/11/2018 ዓ.ሚ ከቀኑ 10:00-1:00 ድረስ በቤተ/ችን አምልኮ አዳራሽ በመጋቢ #ትእግስቱ #ጊያ የሚሰጠውን መንፈሳዊ #ሥልጠና በጉኑኖ ከተማ እና አከባቢ ያላችሁ ሁላችሁም በአካል መጥታችሁ እንድትካፈሉ በጌታ ፍቅር እናሳስባለን
ፀጋው ከሁላችሁ ጋር ይሁን!
Share

18/07/2026

ማቴዎስ 7:7፤ “ለምኑ፥ ይሰጣችሁማል፤ ፈልጉ፥ ታገኙማላችሁ፤ መዝጊያን አንኳኩ፥ ይከፈትላችሁማል።

18/07/2026

ኢያሱ 1:8፤ የዚህ ሕግ መጽሐፍ ከአፍህ አይለይ፥ ነገር ግን የተጻፈበትን ሁሉ ትጠብቅና ታደርግ ዘንድ በቀንም በሌሊትም አስበው፤ የዚያን ጊዜም መንገድህ ይቀናልሃል ይከናወንልሃልም።

14/07/2026

ኤፌሶን 1:3፤ በክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ።

  (Vision)ኢትዮጵያዊያንና ሌሎች ሕዝቦች የክርስቶስን ወንጌል ሰምተው ያመኑና እግዚአብሔርን በሚያከብር ለክርስቶስ በተሰጠ ሕይወት በማህበረሰባቸው ውስጥ የጽድቅ ተጽዕኖ የሚያመጡ የአጥቢያ...
13/07/2026



(Vision)

ኢትዮጵያዊያንና ሌሎች ሕዝቦች የክርስቶስን ወንጌል ሰምተው ያመኑና እግዚአብሔርን በሚያከብር ለክርስቶስ በተሰጠ ሕይወት በማህበረሰባቸው ውስጥ የጽድቅ ተጽዕኖ የሚያመጡ የአጥቢያ ቤተክርስቲያን አባላት ሆነው ማየት።

(Mission)

የክርስቶስን ወንጌል ለኢትዮጵያውያንና ለሌሎች ሕዝቦች በመስበክ ያመኑትን ወደ ቤተክርስቲያን ኅብረት በማምጣትና በማስተማር የተሰጡ የክርስቶስ ተከታዮች በማድረግ በስጦታቸው ሁለንተናዊ አገልግሎት እንዲሰጡ በማብቃት እግዚአብሔርን ማክበር ነው።

(Values)

1. በእግዚአብሔር ቃል የበላይነት ማመንና መገዛት፤
2. መንፈሳዊ አንድነትን መጠበቅ፤
3. ባለአደራነት፤
4. ተተኪ አገልጋዮችን ማፍራት፤
5. ጸሎት።

11/07/2026

ዳንኤል 1:8፤ ዳንኤልም በንጉሡ መብልና በሚጠጣው ጠጅ እንዳይረክስ በልቡ አሰበ፤ እንዳይረክስም የጃንደረቦቹን አለቃ ለመነ።

Address

Ethiopia Wolaita
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gununo Ketema Stadium KHC Youth Ministry posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share