Mary Joy Ethiopia

Mary Joy Ethiopia Mary Joy Ethiopia charity that works to empower vulnerable and underserved community groups through integrated development programs.
(1)

18/06/2026

❇️ዛሬ የሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ የኩላሊት ጤና አባል ይሁኑ!

አባልነት የራስዎን ጤና ብቻ መጠበቅ አይደለም፤ ለቤተሰብዎ እና ለማህበረሰብዎም ተስፋ እና ድጋፍ መሆን ነው።

የሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ የኩላሊት ጤና አባልነት ፕሮግራም በኩላሊት ህመም የሚጎዱ ወገኖችን ለመደገፍ፣ የኩላሊት ጤና ግንዛቤን ለማሳደግ እና ጤናማ ማህበረሰብ ለመገንባት የታለመ ፕሮግራም ነው።

አባል ሲሆኑ ፤
✅በቂ መረጃ በማግኘት የራስዎን እና የቤተሰብዎን ጤና ይጠብቃሉ
✅በኩላሊት ህመም የሚጎዱ ወገኖችን በመርዳት ይሳተፋሉ
✅አባል በመሆንዎ ለእርስዎና ለቤተሰብዎ የሚያስገኙ ጥቅሞችን ያገኛሉ
✅ጤናማ ማህበረሰብ ለመገንባት ድርሻዎን ይወጣሉ

ዛሬ የሚወስዱት አንድ እርምጃ የነገውን የኩላሊት ጤና ዋስትና ሊሆን ይችላል!
ስለ አባልነት ዝርዝር መረጃ ለማግኘት እና ለመመዝገብ አሁኑኑ በቴሌግራም ያናግሩን። https://t.me/+tHZMvhjtAqk5Y2Y0

#የሜሪጆይኢትዮጵያ
#ዛሬአባልይሁኑ
#የኩላሊትጤና
#ጤናማሕይወት!!

ፓልም ሪል እስቴት ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ “ኩላሊት ጤና ህይወት ተስፋ” በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ ከተማ ባዘጋጀው ታላቅ የእግር ጉዞ ላደረጉት የላቀ አስተዋጽኦ የምስጋና እና የእውቅና ሰርተፍ...
18/06/2026

ፓልም ሪል እስቴት ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ “ኩላሊት ጤና ህይወት ተስፋ” በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ ከተማ ባዘጋጀው ታላቅ የእግር ጉዞ ላደረጉት የላቀ አስተዋጽኦ የምስጋና እና የእውቅና ሰርተፍኬት ተሰጧል።
ይህን ሰርተፍኬት የሰጡት የሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ መስራችና ዋና ስራ አስኪያጅ ሲ/ር ዘቢደር ናቸው።
👉 ፓልም ሪል እስቴት ለማህበረሰብ ጤና ያበረከታችሁትን ዋጋ ያለው ድጋፍ እናመሰግናለን!
#ሜሪጆይኢትዮጵያ #ኩላሊትጤና #ምስጋና #ትብብር #አዲስአበባ

👏👏ምስጋና እና እውቅና 👏👏ጊፍት ሪል እስቴት በሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ "ኩላሊት ጤና ህይወት ተስፋ" በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ ከተማ በተዘጋጀው ታላቅ የእግር ጉዞ ላይ ላደረጉት ከፍተኛ አስተ...
18/06/2026

👏👏ምስጋና እና እውቅና 👏👏

ጊፍት ሪል እስቴት በሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ "ኩላሊት ጤና ህይወት ተስፋ" በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ ከተማ በተዘጋጀው ታላቅ የእግር ጉዞ ላይ ላደረጉት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የምስጋና እና የእውቅና ሰርተፍኬት በሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ መስራችና ዋና ስራ አስኪያጅ ሲ/ር ዘቢደር ዘውዴ ተሰጥቷል።
🙏 ጊፍት ሪል እስቴት ለማህበረሰባችን የምታደርጉት ድጋፍ እና ተሳትፎ እጅግ ከፍ ያለ ነው።
ከልብ እናመሰግናለን!

18/06/2026

ዛሬ አንድ አባት ከልባቸው ምርቃት አድርገዋል።
ይህ በጎ ተግባር ለሌሎች ብርሃን እንዲሆን እንጠራችኋለን።
ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ከ6 በላይ ክልሎች ውስጥ በጤና፣ በትምህርት፣ በገቢ ማስገኛ እና በኑሮ ማሻሻያ ዘርፎች ላይ ትልቅ ስራ በመስራት ለማህበረሰባችን ብርሃን ሆኗል።
“ኢትዮጵያዊያን ለኢትዮጵያዊያን” በሚል መሪ ቃል የሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ ያሉ ኢትዮጵያዊያን ህፃናትን በመደገፍ፣ የወላጆቻቸውን ፍቅር ያጡ ህፃናትን እና ድጋፍ የሌላቸውን አረጋዊያንን እየደገፈ ይገኛል።
👉 እርስዎም የአንድ ህፃን ወይም የአንድ አረጋዊ ሕይወት መቀየር ይችላሉ
👉 በመስጠት ደስታን ያግኙ
❤️ እንተባበር… እንረዳ… እንቀይር!
#ኢትዮጵያዊያንለኢትዮጵያዊያን

ክረምቱ እየቀረበ ነው… እነርሱ ግን እገዛዎን ይጠብቃሉ?በሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ ያሉ አረጋዊያንን ከብርድ ለመጠበቅ የተለያዩ አልባሳት ያስፈልጋሉ። ዛሬ የእርስዎ ድጋፍ እጅግ አስፈላጊ ነው!👉 የክ...
17/06/2026

ክረምቱ እየቀረበ ነው… እነርሱ ግን እገዛዎን ይጠብቃሉ?

በሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ ያሉ አረጋዊያንን ከብርድ ለመጠበቅ የተለያዩ አልባሳት ያስፈልጋሉ።
ዛሬ የእርስዎ ድጋፍ እጅግ አስፈላጊ ነው!
👉 የክረምት አልባሳት (ጃኬት፣ ሸሚዝ፣ ብርድልብስ እና የተለያዩ ከብርድ የሚጠብቁ ልብሶች) በመስጠት አለኝታ ይሁኑ
👉 አንድ አረጋዊ ከብርድ ያድኑ
👉 ትንሽ ድጋፍዎ ትልቅ ሙቀት ይሰጣል

👉 ዛሬ ይሳተፉ፤ ሕይወት ያሙቁ!

አንድ ትንሽ እገዛ… ትልቅ ለውጥ****አንድ ህፃን ትምህርት ሲያጣ፣አንድ አረጋዊ እገዛ ሲያጣ…ሕይወት እጅግ ይከብዳል።ነገር ግን እርስዎ በቀላሉ ልዩነት ማመጣት ይችላሉ።👉 1000 ብር ብቻ በ...
15/06/2026

አንድ ትንሽ እገዛ… ትልቅ ለውጥ
****
አንድ ህፃን ትምህርት ሲያጣ፣
አንድ አረጋዊ እገዛ ሲያጣ…
ሕይወት እጅግ ይከብዳል።

ነገር ግን እርስዎ በቀላሉ ልዩነት ማመጣት ይችላሉ።
👉 1000 ብር ብቻ በመደገፍ
✔️ አንድ ህፃን ለ1 ወር ያስተምራል
✔️ አንድ አረጋዊ ለ1 ወር ይጦራል

ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ
“ኢትዮጵያዊያን ለኢትዮጵያዊያን”
“ሁሌም ስሰጥ የምቀበለው አለ”
📍 ፒያሳ ገዳም ሰፈር ወረዳ 05
📞 0987626262 / 0983636363
👉 ዛሬ ይሳተፉ፤ አንድ ሕይወት ይቀይሩ!

የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ ሜሪጆይ ኢትዮጵያ በኩላሊት እጥበት ህክምና አገልግሎት እጦት ለሚቸገሩ ታማሚዎች በዝቅተኛ እና በነፃ የእጥበት አገልግሎት እየሰጠ ያለውን ማዕ...
11/06/2026

የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ ሜሪጆይ ኢትዮጵያ በኩላሊት እጥበት ህክምና አገልግሎት እጦት ለሚቸገሩ ታማሚዎች በዝቅተኛ እና በነፃ የእጥበት አገልግሎት እየሰጠ ያለውን ማዕከል ጎበኙ።

ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ የኩላሊት ዕጥበት አገልግሎቱን ለማስፋፋትና ለማጠናከር በሐዋሳ ከተማ እያስገነባ የሚገኘው ሆስፒታል በሚቀጥሉት 4 ወራት ውስጥ ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት እንዲጀምር የሁሉም ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል እና የኩላሊት ዕጥበት ህክምና በዝቅተኛ ክፍያ እና በነፃ አገልግሎት ለመስጠት በቀየሰው ስልት መሠረት ሁሉም ዜጋ ወርሐዊ የአባልነት ክፍያ በመፈፀም የማዕከሉ አባል በመሆን አገልግሎት ማግኘት ያልቻሉ ህሙማን እንዲደግፍም አቶ ጥራቱ ጥሪ አቅርበዋል።

የሜሪጆይ መስራችና ዋና ሰራ አስኪያጅ ሲስተር ዘቢደር ዘውዴ በጤናው ዘርፍ ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቀውን የኩላሊት እጥበት ማዕከል በራሱ ገቢ ማስገንባቱ እና አገልግሎት መስጠት መጀመሩ የማዕከሉን አቅም የሚያጎለብት ከመሆኑም ባሻገር ታካሚዎች እንግልትና ስቃይ የሚታደግ መሆኑን እና ማዕከሉ አቅም ላጡት ታማሚዎች በቅናሽ ህክምናውን እንዲያገኙ ጭምር መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግላቸውም ጠይቀዋል።

የሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ የበጎ አድራጎት አምባሳደርና በኢትዮጵያ የመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የደቡብ ኢትዮጵያ ክላስተር አስተባባሪ እና የሐዋሳ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ዘመን ለገሠ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከሉን ለማስፋፋትና ለማጠናከር ለ1ወር የህዝብ ንቅናቄ እንደሚካሄድ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የማዕከሉ አባል በመሆን በገንዘብ ዕጦት ምክንያት የኩላሊት ዕጥበት አገልግሎት አጥተው ለሚቸገሩ ህሙማን መፍትሄ እንዲሆን እንዲሁም የማዕከሉ አባልነት በሚያስገኘው ጥቅም የኩላሊታቸውን ጤና እንዲጠብቁ ስል ጥሪ አቅርበዋል።

 ! #የወ/ሮ  5ኛ ሙት አመት መታሰቢያ በማድረግ፣ በሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ ለሚገኙ ከ 100 በላይ አረጋዊያን እና አቅመ ደካሞች ማዕድ አካፍለዋል።ነብስ ይማር! በአረጋውያኑ እና በህፃናቱ ስም ...
09/06/2026

!
#የወ/ሮ
5ኛ ሙት አመት መታሰቢያ በማድረግ፣ በሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ ለሚገኙ ከ 100 በላይ አረጋዊያን እና አቅመ ደካሞች ማዕድ አካፍለዋል።ነብስ ይማር! በአረጋውያኑ እና በህፃናቱ ስም ከልብ እናመሰግናለን።
በጎነት የሚቀጥል ትውልድ እንገንባ!
#በጎነት #መታሰቢያ #ማዕድ #አረጋዊያን

08/06/2026


“የተሰጠ እጅ… ወደ በረከት ተመለሰ”
በሜሪ ጆይ ድጋፍ የእናት ምርቃት ተቀበልን 🙏

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ስደተኞች እና ተመላሾች አገልግሎት ለሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ የተለያዩ የህክምና እና የቢሮ ቁሳቁሶችን ድጋፍ አድርገዋል።በድጋፍ ስነ-ስርዓቱ ላይ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ ጤይባ ...
04/06/2026

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ስደተኞች እና ተመላሾች አገልግሎት ለሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ የተለያዩ የህክምና እና የቢሮ ቁሳቁሶችን ድጋፍ አድርገዋል።

በድጋፍ ስነ-ስርዓቱ ላይ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ ጤይባ ሀሰን ድጋፉን ለሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ መስራችና ዋና ስራ አስኪያጅ ሲ/ር ዘቢደር ዘውዴ አስረክበዋል።
ይህ ድጋፍ የጤና አገልግሎታችንን ጥራት ለማሻሻል እና ለማህበረሰባችን የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት ትልቅ አስተዋፅኦ ያበረከተ ነው።
🙏 ለቀና ትብብራችሁ እና ለሰጣችሁ ድጋፍ ከልብ እናመሰግናለን!
በጎነት በተግባር
አብረን ሕይወት እንቀይር

Address

ፒያሳ ገዳም ስፍር 3ኛ ፖሊስ ጣቢያ ፊት ለፊት ኣራዳ ወረዳ 5 ግቢ
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mary Joy Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Mary Joy Ethiopia:

Share