16/06/2026
🏆 ከስፖርትም በላይ—አንድነታችን እና ድምጻችን! 🏆
ባለፉት ሳምንታት በደመቀ ሁኔታ ሲካሄድ ሰንብቶ፣ ባሳለፍነው እሁድ ሰኔ 07/2018 ማጠናቀቂያውን ባገኘው የመጀመሪያው የኬር ሊቨርስ ማህበራት ስፖርት ፌስቲቫል (Care Leavers Associations Sport Festival) ላይ የ የቀድሞ ኤስ .ኦ . ኤስ ወጣቶች ማህበር ኢትዮጲያ / SOS Almuni Youth Association Ethiopia አባላት በመሳተፋችን እጅግ ታላቅ ኩራት ይሰማናል!
"Forward Together Leave No Youth Behind" በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው በዚህ ታሪካዊ መድረክ ላይ፣ ማህበራችንን የወከሉ ወጣቶቻችን በወንዶች እግር ኳስ እና በሴቶች ቮሊቦል ውድድሮች ላይ አስደናቂ ፉክክር፣ ድንቅ ክህሎት እና ከፍተኛ ስፖርታዊ ጨዋነትን በማሳየት ደምቀው ውለዋል።
ይህ ስፖርታዊ ውድድር ጨዋታ ብቻ ሳይሆን፣ ለኬር ሊቨርስ ወጣቶቻችን ትስስር፣ ለአድቮኬሲ (ጥበቃ እና መብት ማስከበር) ንቅናቄያችን እና ስፖርት ሰዎችን የማገናኘት ስላለው ታላቅ ሃይል በተግባር ያሳየ መድረክ ነው።
🙌 ምስጋና 🙌
ይህን ውብ እና ታሪካዊ ውድድር ላዘጋጀው ለ National Care Leaver's Associations Coalition Ethiopia (NCLACE) አጋርነታችንን እያረጋገጥን፣ ልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን።
በተጨማሪም፣ ከዚህ አይነት ትልልቅ እና ተፅዕኖ ፈጣሪ ስራዎች ጀርባ በመሆን ማህበራቱን እና ጥምረቱን በብቸኝነት እየደገፈ ለሚገኘው ለ SOS Children's Villages in Ethiopia እንዲሁም ለ "Leave No Youth Behind" ፕሮጀክት የገንዘብ ድጋፍ ለሚያደርገው ለዴንማርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር Ministry of Foreign Affairs of Denmark 🇩🇰 (DANIDA) የላቀ ምስጋናችን ይድረስልን።
💪 መልእክታችን 💪
በዚህ ውድድር ላይ የተሳተፋችሁ የሁሉም ማህበራት ወጣቶች—ሁላችሁም አሸናፊዎች ናችሁ! ይህ ከስፖርትም በላይ የሆነ ድንቅ ፌስቲቫል ለነገው ትልቅ ጉዞዋችን አዲስ መነቃቃትን የፈጠረብን መድረክ ነው።
አንድነታችንን ይበልጥ በማጠናከር፣ በኢትዮጵያ ውስጥ የኬር ሊቨሮችን ድምፅ ከፍ አድርገን ለማሰማት እና በጋራ አስደናቂ ለውጥ ለማምጣት ከመቼውም ጊዜ በላይ ቁርጠኞች ነን! ጉዟችን ወደፊት ነው!
# # # # # # # # # # # # # # # #
🏆 More Than Just a Game—Our Unity and Our Voice! 🏆
We are immensely proud to announce that the SOS Alumni Youth Association Ethiopia actively participated in the first-ever Care Leavers Associations Sport Festival, which successfully concluded with a vibrant closing ceremony this past Sunday, June 14, 2026!
Under the powerful motto "Forward Together, Leave No Youth Behind," our incredible youth represented our association in both Men’s Football and Women’s Volleyball, showcasing remarkable competitiveness, outstanding talent, and exemplary sportsmanship throughout the weeks-long tournament.
This sports festival has proven to be much more than a tournament; it highlighted the incredible power of sports as a tool for advocacy, connection, and empowerment for care-experienced youth across the nation.
🙌 Deepest Gratitude 🙌
We extend our heartfelt appreciation to the National Care Leaver's Associations Coalition Ethiopia (NCLACE) for organizing this historic and impactful event.
Our special thanks also go to SOS Children's Villages Ethiopia for their unwavering and exclusive backbone support to the associations and the coalition. We also express our profound gratitude to the 🇩🇰 (DANIDA) for funding the "Leave No Youth Behind" project, which makes such milestone achievements possible.
💪 Our Commitment 💪
👉 To all the youth from the various associations who participated: Every single one of you is a winner! This phenomenal festival has ignited a renewed sense of energy and purpose within us.
Moving forward, we are more committed than ever to strengthening our unity, amplifying the voices of care leavers across Ethiopia, and driving sustainable, positive change. The future is ours to shape!
Embassy of Denmark in Ethiopia SOS Children's Villages Eastern and Southern Africa SOS Børnebyerne SOS Children's Villages International የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር Ministry of Women and Social Affairs SELAM Fruits Association