11/07/2026
# ሳምንታዊዉ የሰንበት_ገበያ ተጠናክሮ ቀጥሏል!!! 🍊🍎🍏🍌🍉🍓🍇🍍🍑🍒🍅🥬🥒🥕🥔
የቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 04 አስተዳደር አዘጋጅነት እየተሰራ ያለው የሰንበት ገበያ በተለያዩ 3 ሶስት ቦታወች ተከፍቶ ለወረዳው ህብረተሰብ አገልግሎት መስጠቱን ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡
በወረዳ ደረጃ ተከፍተው አገልግሎት እየሰጡ ያሉ 3 የሰንበት ገበያወች ላይ ማለትም 22ዘሪሁን ህንፃ፣ለም ሆቴል ድልድይ ወደ 24 በሚወስደው እና አርሴማ ቤተክርስቲያን አጠገ ይገኛሉ ፡፡
በእነዚህ የገበያ ቦታወች ለተጠቃሚው የሚቀርበው የምርት አቅርቦት ጥራቱን የጠበቀና ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ በመምጣቱ ህብረተሰቡ የመግዛት ፍላጎቱ ከመቸውም በላይ እየጨመረ መቷል።
የወረዳ አስተዳደሩም ህገወጥ የዋጋ ጭማሪ እንዳይደረግ የንግድ እና የህብረት ስራ ጽ/ቤት ባለሙያወቹ በየተመደቡበት የገበያ ቦታ በመገኘት የተሰጣቸውን ተልኮ እየተወጡ መሆናቸው ተገልጿል፡፡
በዚህ መሰረት የአካባቢው ነዋሪና ማህበረሰብ ይህን እድል በመጠቀም እና የሚፈልጉትን አትክልትም ሆነ ሌሎች የኢንዱስትሪ የፍጆታ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በአንድ ቦታ እንዲያገኙ ያደረገ የገበያ ማዕከል ነው፡፡
ቦሌ ወረዳ 04 ኮሙኒኬሽን
ሀምሌ 04/2018 ዓ.ም