Bole 04 communicatiion

Bole 04 communicatiion ለአንድ ተቋም መረጃ ሀብት ነው፡፡

 # ሳምንታዊዉ የሰንበት_ገበያ ተጠናክሮ ቀጥሏል!!! 🍊🍎🍏🍌🍉🍓🍇🍍🍑🍒🍅🥬🥒🥕🥔የቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 04  አስተዳደር አዘጋጅነት እየተሰራ ያለው የሰንበት ገበያ በተለያዩ 3 ሶስት ቦታወች ተከ...
11/07/2026

# ሳምንታዊዉ የሰንበት_ገበያ ተጠናክሮ ቀጥሏል!!! 🍊🍎🍏🍌🍉🍓🍇🍍🍑🍒🍅🥬🥒🥕🥔

የቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 04 አስተዳደር አዘጋጅነት እየተሰራ ያለው የሰንበት ገበያ በተለያዩ 3 ሶስት ቦታወች ተከፍቶ ለወረዳው ህብረተሰብ አገልግሎት መስጠቱን ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡
በወረዳ ደረጃ ተከፍተው አገልግሎት እየሰጡ ያሉ 3 የሰንበት ገበያወች ላይ ማለትም 22ዘሪሁን ህንፃ፣ለም ሆቴል ድልድይ ወደ 24 በሚወስደው እና አርሴማ ቤተክርስቲያን አጠገ ይገኛሉ ፡፡
በእነዚህ የገበያ ቦታወች ለተጠቃሚው የሚቀርበው የምርት አቅርቦት ጥራቱን የጠበቀና ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ በመምጣቱ ህብረተሰቡ የመግዛት ፍላጎቱ ከመቸውም በላይ እየጨመረ መቷል።

የወረዳ አስተዳደሩም ህገወጥ የዋጋ ጭማሪ እንዳይደረግ የንግድ እና የህብረት ስራ ጽ/ቤት ባለሙያወቹ በየተመደቡበት የገበያ ቦታ በመገኘት የተሰጣቸውን ተልኮ እየተወጡ መሆናቸው ተገልጿል፡፡

በዚህ መሰረት የአካባቢው ነዋሪና ማህበረሰብ ይህን እድል በመጠቀም እና የሚፈልጉትን አትክልትም ሆነ ሌሎች የኢንዱስትሪ የፍጆታ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በአንድ ቦታ እንዲያገኙ ያደረገ የገበያ ማዕከል ነው፡፡

ቦሌ ወረዳ 04 ኮሙኒኬሽን
ሀምሌ 04/2018 ዓ.ም

የአንድ ማዕከል የጽዳት ዘመቻ ተካሄደ።በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 04 አስተዳደር የ2019 በጀት አመት  የፅዳት ንቅናቄ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር  ተካሄደ።​ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 04 አስተ...
11/07/2026

የአንድ ማዕከል የጽዳት ዘመቻ ተካሄደ።
በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 04 አስተዳደር የ2019 በጀት አመት የፅዳት ንቅናቄ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሄደ።
​ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 04 አስተዳደር «የፍሳሽ ማስተላለፊያ መስመሮች የውሀ መውረጃ እንጂ የቆሻሻ መጣያ አይደሉም» በሚል መሪ ቃል የ2019 በጀት አመት የፅዳት ንቅናቄማስጀመሪያ በዛሬው ዕለት (ሀምሌ 04ቀን 2018 ዓ.ም) በቀጠና 16ልዪ ስሙ መክሊት ህንጻ አካባቢ ተካሄደ።
​በማስጀመሪያ መርሃግብሩ ላይ የተገኙት የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ገነሞ በዳኔ እንደገለጹት፤ ቀጣይነት ያላቸው የፅዳት ስራዎችን በማከናወን ከተማችንን ፅዱ፣ ውብ እና ለነዋሪዎቿ ምቹ ማድረግ እየተቻለ ይገኛል። በመሆኑም ከተማዋን ከአለም ግንባር ቀደም ከተሞች ተርታ ለማሰለፍ የፅዳት ስራን የሁልጊዜም ባህል ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
የክፍለ ከተማው ጽዳት አስተዳደር ጽ/ቤት ሀላፊው አቶ ተስፋዬ ታደሰ በበኩላቸው የፍሳሽ ማስተላለፊያ መስመሮች የውሀ መውረጃ እንጂ የቆሻሻ መጣያ እንዳልሆኑ ገልጸው፤ ፅዳት የአንድ ወቅት ስራ ሳይሆን የዘወትር ተግባር ሊሆን እንደሚገባ ገልጸዋል።

በመሆኑም ንጹህ አካባቢን ለመፍጠር እያንዳንዱ ዜጋ የፅዳት አርበኛ ሆኖ መንቀሳቀስ እንዳለበት በአፅንኦት አሳስበዋል።

​በዚህ ማለዳ በተካሄደው የፅዳት ዘመቻ ንቅናቄ ላይ የወረዳው አመራሮች፣ ባለሙያዎች፣ የፅዳትና ውበት አስተዳደር ባለሙያዎች እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪዎች በንቃት መሳተፋቸው ታውቋል።

ሀምሌ 04/11/2018 ዓ.ም

የባህር በር ተደራሽነት፡ የኢትዮጵያ የልማት ቁልፍ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የባህር በር ተደራሽነት በዘመናችን ከኢኮኖሚ እድገት፣ ከብሔራዊ ደህንነት፣ ከንግድ እና ከክ...
10/07/2026

የባህር በር ተደራሽነት፡ የኢትዮጵያ የልማት ቁልፍ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የባህር በር ተደራሽነት በዘመናችን ከኢኮኖሚ እድገት፣ ከብሔራዊ ደህንነት፣ ከንግድ እና ከክልላዊ ትስስር ጋር በጥብቅ የተያያዘ ጉዳይ ሆኗል።

በተለይም ከ120 ሚሊየን በላይ ሕዝብ ላላት ኢትዮጵያ የባህር በር ተደራሽነት የቀን ፖለቲካ ክርክር ሳይሆን የረጅም ጊዜ የልማት ስትራቴጂ ሊሆን ይገባዋል።

ለብዙ ዘመናት ከቀይ ባህር ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት የነበራት ኢትዮጵያ ከ1983 ዓ.ም ወዲህ ባልተገባ መንገድ ተገፍታ የባህር በር አልባ ለመሆን ተገድዳለች።

ከዚያ ወዲህ አብዛኛው የውጭ ንግዷን በጎረቤት ሀገሮች ወደቦች፣ በተለይም በጅቡቲ ወደብ ትጠቀማለች።

ይህ ሁኔታ የንግድ ወጪ እንዲጨምር፣ የሎጂስቲክስ ፈተናዎች እንዲፈጠሩ እና በአንድ ዋና የመጓጓዣ መስመር ላይ ከፍተኛ ጥገኝነት እንዲኖር አድርጓል።

በዓለም አቀፍ ሥርዓት የአንድ ሀገር ሉዓላዊነት በአክብሮት የሚጠበቅ ሲሆን፤ ባህር የሌላቸው ሀገራትም በስምምነትና በሕጋዊ መንገድ ወደ ባህር የመድረስ መብቶችን የሚያገኙበት ዕድል አለ።

በባህር በር ጉዳይ ከሁለት አንጻር የሚታይ ሲሆን፤ እነሱም የ"ባለቤትነት" እና የ"ተደራሽነት" ጽንሰ ሐሳቦችን ናቸው።

የባህር በር ባለቤትነት ከአንድ ሀገር ሉዓላዊ ግዛት ጋር የተያያዘ ሲሆን የባህር ተደራሽነት ግን ባህር የሌላት ሀገር በዓለም አቀፍ ሕግና በሁለትዮሽ ወይም በክልላዊ ስምምነቶች መሠረት ወደ ባህር የምትደርስበትን መብት ያመለክታል።

ስለዚህ ዋናው ጥያቄ "ባህሩ የማን ነው?" የሚለው ሳይሆን፣ "ኢትዮጵያ ዘላቂ፣ አስተማማኝ፣ ወጪ ቆጣቢ እና ሕጋዊ የባህር ተደራሽነትን እንዴት ታረጋግጣለች?" የሚለው ነው።

ኢትዮጵያ ኢንዱስትሪዋን ለማሳደግ፣ የግብርና ምርቶቿን ወደ ውጭ ገበያ በተወዳዳሪ ዋጋ ለማቅረብ፣ የማዕድን ሀብቷን ለማልማት እና የውጭ ንግዷን ለማስፋፋት ቀልጣፋ እና ውጤታማ የባህር መዳረሻ ያስፈልጋታል።

የመጓጓዣ ወጪ በቀነሰ መጠን የምርት ዋጋ ይቀንሳል፤ የኢንቨስትመንት ፍላጎት ይጨምራል፤ የሥራ ዕድሎች ይፈጠራሉ፤ የውጭ ምንዛሬ ገቢም ያድጋል። በዚህ መልኩ የባህር በር ተደራሽነት የልማት አስፈላጊ መሠረት ይሆናል።

በሌላ በኩል ለባህር በር ተደራሽነት ቀጣናዊ ትብብር ወሳኝ ጉዳይ ነው፡፡

በዚህም የአፍሪካ ቀንድ ከጂኦፖለቲካዊ አቀማመጡ የተነሳ በዓለም የንግድ መስመሮች ውስጥ ከፍተኛ ስትራቴጂያዊ ዋጋ አለው። ይህን አቅም ወደ ዘላቂ እድገት መቀየር የሚቻለው በፉክክር ሳይሆን በትብብር ነው።

ወደቦችን፣ የባቡር መስመሮችን፣ የመንገድ አውታረ መረቦችን፣ የኃይል ትስስሮችን እና የንግድ ኮሪደሮችን በጋራ ማልማት ለሁሉም ሀገራት ተጠቃሚ የሆነ የጋራ እድገትን ያመጣል።

የተረጋጋ ሰላም እና የንግድ ነጻነት ካለ የባህር በር ጥያቄም ከግጭት ይልቅ በጋራ ጥቅም መንፈስ የማይመለስበት ምንም ምክንያት የለም፡፡

ኢትዮጵያ አስተማማኝ የባህር ተደራሽነትን ማግኘት የልማቷ አስፈላጊ አካል ሲሆን በተመሳሳይ የጎረቤት ሀገራት ሉዓላዊነትና ደህንነት መከበር የክልሉ መረጋጋት መሠረት ነው።

ስለሆነም የወደፊቱ አቅጣጫ ግጭትን ሳይሆን ድርድርን፣ ፉክክርን ሳይሆን ትብብርን፣ አንድን ወገን ማሸነፍን ሳይሆን የጋራ ብልጽግናን ያበረታታል።

በአመለወርቅ ደምሰው

የእድገትና የስኬት ምዕራፍን እየጻፈች ያለችው ኢትዮጵያበጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር አርቆ አሳቢ አመራር እየተመራች፣ ኢትዮጵያ ዛሬ የውድቀትን አዙሪት ሰብራ የብልጽግናዋን አዲስ ም...
10/07/2026

የእድገትና የስኬት ምዕራፍን እየጻፈች ያለችው ኢትዮጵያ

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር አርቆ አሳቢ አመራር እየተመራች፣ ኢትዮጵያ ዛሬ የውድቀትን አዙሪት ሰብራ የብልጽግናዋን አዲስ ምዕራፍ በታላቅ ቁርጠኝነት እየጻፈች ትገኛለች። በጠቅላይ ሚኒስትሩ የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም አማካኝነት ኢትዮጵያ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ 1.3 ቢሊዮን ኩንታል እህል ወደ ጎተራዋ በማስገባት፣ የቱሪዝምና የአየር መንገድ አገልግሎቷን በማዘመን፣ እንዲሁም የኢንዱስትሪ ምርቶችን በአገር ውስጥ በመተካት 5 ቢሊዮን ዶላር በመቆጠብ አስደናቂ የስኬት ጉዞ እያደረገች ነው። ባለፉት ሰባት ዓመታት የተገነቡት 1.2 ሚሊዮን ቤቶች እና በቀጣይ የታቀዱት ተጨማሪ 1.5 ሚሊዮን ቤቶች የሀገሪቱን የልማት ጥማት የሚያሳዩ ሲሆን፣ ይህ የለውጥ ጉዞ ኢትዮጵያን "ከራሷ አልፋ ለሌሎች የምትተርፍ" ብርቱ ሀገር የማድረግ ራዕይን በተግባር እያረጋገጠ፣ ለቀጣዩ ትውልድ ደማቅ ተስፋን እየዘራ ይገኛል።

የአፍሪካ ትልቁ አውሮፕላን ማረፊያ ሜጋ-ፕሮጀክት በቁጥሮች****************👉🏽12.5 ቢሊዮን ዶላርየፕሮጀክቱ አጠቃላይ የግንባታ ወጪ👉🏽110 ሚሊዮን መንገደኞች በዓመትከለንደን፣ ዱባይ...
09/07/2026

የአፍሪካ ትልቁ አውሮፕላን ማረፊያ ሜጋ-ፕሮጀክት በቁጥሮች
****************

👉🏽12.5 ቢሊዮን ዶላር
የፕሮጀክቱ አጠቃላይ የግንባታ ወጪ

👉🏽110 ሚሊዮን መንገደኞች በዓመት
ከለንደን፣ ዱባይ እና አሜሪካ ታላላቅ አውሮፕላን ማረፊያዎች የበለጠ

👉🏽35 ካሬ ኪ.ሜ
ከለንደኑ ሂትሮው በእጥፍ ይሰፋል

👉🏽4 ሚሊዮን ቶን
በዓመት የሚያስተናግደው የካርጎ መጠን

👉🏽4 (Code 4E)
ግዙፍ አውሮፕላኖች ማስተናገድ የሚችሉ መንደርደሪያዎች

👉🏽80 በመቶ
አውሮፕላን ማረፊያውን እንደ መሸጋገሪያ የሚጠቀሙ መንገደኞች ድርሻ

👉🏽1 ሺህ 900 ሜትር
ከባህር ወለል በላይ ያለው ከፍታ

ለቀጣናው ዋስትና እየሆነች ያለች ሀገርየኢትዮጵያ የፀጥታና የደኅንነት ተቋማት ዘመናዊ ቴክኖሎጂንና ሰብአዊ አቅምን በማስተባበር በቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ለማስፈን የጎላ ሚና እየተጫወቱ ይገኛ...
09/07/2026

ለቀጣናው ዋስትና እየሆነች ያለች ሀገር

የኢትዮጵያ የፀጥታና የደኅንነት ተቋማት ዘመናዊ ቴክኖሎጂንና ሰብአዊ አቅምን በማስተባበር በቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ለማስፈን የጎላ ሚና እየተጫወቱ ይገኛሉ።

በሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ በብሔራዊ መረጃና ደኅንነት እና በፌደራል ፖሊስ የተገነባው ይህ አስተማማኝ አቅም ቀጣናዊ የሽብር አደጋዎችን እና ሕገ-ወጥ የሰዎችና የጦር መሳሪያ ዝውውርን በመከላከል ረገድ ለአፍሪካ ቀንድ የማይተካ የደኅንነት ዋስትና ሆኗል።

የአፍሪካ ቀንድ ቀጣና በጂኦ-ፖለቲካዊ አቀማመጡ፣ በተለዋዋጭ የደኅንነት ምኅዳር እና በተለያዩ የድንበር ተሻጋሪ አደጋዎች የተከበበ ነው።

በእነዚህ ፈተናዎች መካከል ኢትዮጵያ ታሪካዊ ክብሯን እና የሕዝቦቿን ሰላም ለማስጠበቅ የገነባቻቸው የደኅንነትና የፀጥታ ተቋማት፤ በማንኛውም ዓይነት የውስጥም ሆነ የውጭ ሤራ የማትበገር ጽኑ ሀገር መሆኗን በተግባር እያሳዩ ይገኛሉ።

ተቋማቱ በሰው ኃይልና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ አቅም በመገንባታቸው ተልዕኳቸውን በብቃት እየተወጡ ይገኛሉ።

ባለፉት ሀገራዊ የለውጥ ዓመታት ውስጥ መንግሥት ከተገበራቸው የሪፎርም አምዶች አንዱ ጠንካራና ገለልተኛ የፀጥታና የደኅንነት ተቋማትን መገንባት ነበር።

የሀገር መከላከያ ሠራዊት በቴክኖሎጂ፣ በመረጃና በሳይበር ሥርዓት የዘመነ አቅም በመገንባት ላይ ይገኛል።

ሰራዊቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅናን ያተረፈ ሲሆን፣ ኢትዮጵያን ለቀጣናው ሀገራት መከታና የሰላም ምሰሶ አድርጓታል።

የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት በበኩሉ የቀጣናውን የፀጥታ ሁኔታ በጥልቀት በመተንተን አሸባሪ ቡድኖችና አደገኛ አውታረ መረቦችን ቀድሞ በመምታት ሀገራዊና ቀጣናዊ ሰላምን በማስጠበቅ ግንባር ቀደም ሚና እየተጫወተ ይገኛል፡፡

የኢፌዴሪ አየር ኃይል ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ስልታዊ ድሮኖችን በመታጠቅ የአየር ክልሉን ፍፁም የማይደፈር አድርጎታል።

የኢትዮጵያ የባሕር ኃይል ደግሞ ኢትዮጵያ በግፍ ወደ ተነጠቀችው የባህር በር ለመመለስና የኢትዮጵያን የወደፊት የኢኮኖሚና የደኅንነት ጥቅም ለመጠበቅ በንቃት ራሱን አደራጅቶ ለተልእኮ እየተዘጋጀ ይገኛል።

በአጠቃላይ የአፍሪካ ቀንድ ለዓለም አቀፍ የሽብር ቡድኖች፣ ለሕገ-ወጥ የጦር መሳሪያና የሰዎች ዝውውር ተጋላጭ ነው።

የኢትዮጵያ የፀጥታ ተቋማት መረጃዎችን በወቅቱ በመለዋወጥ እና በማክሸፍ በቀጣናው ላይ ሊደርሱ የሚችሉ አደጋዎችን አስቀርተዋል።

የኢትዮጵያ አቪዬሽን ሴኪዩሪቲ አሰራሮች ምንም ዓይነት የስጋት ደረጃ እንደሌለባቸው የዓለም አቀፉ ሲቪል አቪዬሽን ድርጅት ያረጋገጠው፣ ተቋማቱ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ መሆናቸውን አሳይቷል።

አዳዲስ ጦርነቶች በሳይበር ሥርዓት እና በፈጣን መረጃ ልውውጥ ላይ በተመሰረቱበት በዚህ ዘመን፣ የሀገሪቱ የሳይበር ደኅንነት ተቋማት ሀገራዊና ቀጣናዊ መሠረተ ልማቶችን ከአደጋ በመጠበቅ አስተማማኝ ዋስትና ሆነዋል።

የኢትዮጵያ የደኅንነትና የፀጥታ ተቋማት ሁለንተናዊ አቅም የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት፣ ሰላምና ልማት ከማረጋገጥ ባለፈ ለቀጣናው አፍሪካ ቀንድ የሰላምና መረጋጋት ትልቅ ዋስትና ናቸው።

ተቋማቱ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ፣ በሰለጠነ የሰው ኃይል እና በብቃት በመታገዛቸው ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላትን የፖለቲካና የደኅንነት አጋርነት አጠናክረው የሚያስቀጥሉ ናቸው፡፡

በጎነት ለማህበራዊ ትስስርና አብሮነት መጠናከር…አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ልበ ቀናዎች ያለ ምንም ክፍያ ለሌሎች በመራራት ወይም ለማሕበረሰብ በመቆርቆር የሚያደርጉት መል...
09/07/2026

በጎነት ለማህበራዊ ትስስርና አብሮነት መጠናከር…

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ልበ ቀናዎች ያለ ምንም ክፍያ ለሌሎች በመራራት ወይም ለማሕበረሰብ በመቆርቆር የሚያደርጉት መልካም ተግባር ነው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት።

ይህ ተግባር “ድር ቢያብር አንበሳ ያስር…” እንዲሉ ችግረኞችን ለመደገፍ፣ አደጋዎችን ለመከላከል፣ አብሮነትን ለማጠናከር እና በአስቸጋሪ ወቅቶች ፈጣን ምላሽ መስጠት ያስችላል።

በዚህም ለተረጂው ወገን ብቻ ሳይሆን ለበጎ አድራጊውም ክህሎትን ለማዳበር፣ አዳዲስ ሰዎችን ለመተዋወቅ እና ከሁሉ በላይ የውስጥ ሰላምና እርካታን ለማግኘት ትልቅ እድል ይሰጣል። የመረዳዳት እና የመተሳሰብ ባህልን በማሳደግ የእርስ በርስ ትስስር ያጠናክራል።

በጎ ተግባር መልክ እና መገለጫው ብዙ ነው፤ የአዛውንቶችን መኖሪያ ቤት ማደስ፣ ሕጻናትን ወይም አቅም የሌላቸውን በነጻ ማስተማር፣ ደም መለገስ በየሆስፒታሎች ውስጥ ጠያቂና አስታማሚ የሌላቸውን ሕሙማን መርዳት፣ አካባቢን ማጽዳትና ማስዋብ ደጋግመን የምንሰማቸው ዘርፎች ናቸው።

የሕክምና፣ የሕግ፣ የቴክኖሎጂ ወይም ሌላ ዕውቀትን ለበጎ አድራጎት ድርጅቶች በነጻ ማጋራትና ማማከርም እንዲሁ በዋጋ የማይተመኑ አበርክቶዎች ናቸው ።

ሰዎች ያለ ምንም ክፍያ ጊዜያቸውን፣ እውቀታቸውን እና ጉልበታቸውን ለሌሎች ሲለግሱ፣ በማሕበረሰቡ መካከል ትስስርን እና አብሮነትን ለማጠናከር ትልቅ ድልድይ ይገነባሉ።

በጎ ፈቃድ አገልግሎት ሰዎችን ያለ ምንም የዘር፣ የሃይማኖት፣ የዕድሜ ወይም የኢኮኖሚ ደረጃ ልዩነት በአንድ ዓላማ ስር ያሰባስባል። እርስ በርሳቸው የመደማመጥ እና የመቀራረብ ዕድል ያገኛሉ። ይህ ደግሞ የተሳሳቱ ትርክቶችንና አመለካከቶችን እንዲሁም ጥርጣሬዎችን ያስወግዳል።

አንድ ሰው በሌላ ሰው ያለ ምንም ቁሳዊ ጥቅም ሲረዳ በማሕበረሰቡ ውስጥ ብቸኛ አይደለሁም የሚደርስልኝ ወገን አለ፤ የሚል የስነ-ልቦና ደህንነት ይፈጥራል። ይህ መረዳዳት በሰዎች መካከል ያለውን እርስ በርስ የመተማመን ስሜት ያሳድገዋል።

በጎ ፈቃደኝነት እኔ ምን አገባኝ ከሚል የግል ስሜት ወጥቶ ይህ የእኛ ጉዳይ ነው የሚል የባለቤትነት እና የጋራ ኃላፊነት ስሜትን ያጎለብታል።

በኢትዮጵያ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ የጋራ መገለጫ ነው። ከጥንት ጀምሮ ማሕበራዊ ትስስርን ለማጠናከር እና እርስ በርስ ለመረዳዳት የሚያገለግሉ በርካታ ባህላዊ እሴቶች አሉ።

ከአያት ቅድመ አያቶች ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ በክፉም በደግም ቀን፣ ሰዎች እርስ በርስ የሚደጋገፉበት የቆየ ማህበራዊ ዋስትና አላቸው፡፡

እንደ እድርና እቁብ ባሉ የቁጠባ እና የአደጋ ጊዜ ምርኩዞች መደጋገፍ እንዲሁም በተለይም በገጠሪቱ ኢትዮጵያ በግብርና ሥራ ወይም በቤት ግንባታ ወቅት እጅ ለእጅ መያያዝ የነበረ አሁንም ያለ ኢትዮጵያዊ እሴት ነው፡፡

አሁን አሁን ይህ እሴት ከዘመናዊ እና ከተደራጁ አሰራሮች ጋር እየተቀናጀ ይገኛል። የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በኢትዮጵያ ይበልጥ ተቋማዊ እየሆነ መጥቷል።

በርካታ አገር በቀል የበጎ አድራጎት ድርጅቶች እና የወጣት ማህበራት በተለያዩ ዘርፎች በጎ ፈቃደኞችን በማስተባበር እየሰሩ ይገኛሉ።

በየአመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወጣቶች ሀይማኖት ብሔር ወይም ቋንቋ ሳይገድባቸው በመላ ሀገሪቱ ተዘዋውረው ወደ ሚሳተፉበት ሀገር አቀፍ ንቅናቄም አድጓል፡:፡

በዚህም የበጎ ፈቃድ ተግባር ሀገሪቱ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ድጋፍ ከመሆኑም በላይ፣ ከተለያዩ ብሔረሰቦችና አካባቢዎች የመጡ ወጣቶች አብረው እንዲሰሩ በማድረግ ማህበራዊ አንድነትንና ሰላምን ለመገንባት ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል፡፡

በምህረት ደምሴ

09/07/2026

በመደመር መንግሥት የኢኮኖሚ ስትራቴጂ የታገዘው የግብርናው ዘርፍ፣ ፈጣን ዕድገትን በማረጋገጥ የሀገራችንን ራስን የመቻል ርዕይ እውን እያደረገ ይገኛል።

‎የውጭ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት እና የሥራ ዕድልን በመፍጠር፣ ዘርፉ ለሌሎች ኢንዱስትሪዎችም የማይናወጥ መሠረት ሆኗል። ይኸው ወሳኝ እመርታ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር አማካኝነት በሀገር በቀል መፍትሔዎች የዜጎችን የዕለት ተዕለት ሕይወት መለወጥና የሀገርን ኢኮኖሚ ማሳደግ እንደሚቻል በተግባር እያሳየን ነው።

‎በጋራ እናልማ፣ እናምርት፣ እንበልጽግ!


ቀይ ባሕር እና ኢትዮጵያ፡ ያልተቋረጠው የሉዓላዊነት ትስስር እና የትውልዱ አደራ*********************የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጥንካሬ እና ሉዓላዊነት ምንጊዜም ከቀይ ባሕር ጠረፍ ጋር በ...
09/07/2026

ቀይ ባሕር እና ኢትዮጵያ፡ ያልተቋረጠው የሉዓላዊነት ትስስር እና የትውልዱ አደራ
*********************

የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጥንካሬ እና ሉዓላዊነት ምንጊዜም ከቀይ ባሕር ጠረፍ ጋር በጥብቅ የተቆራኘ ነው።

ከጥንቱ የአክሱም ሥልጣኔ እስከ ዘመናዊው የታሪክ ምዕራፍ ድረስ ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር ላይ ጉልህ አሻራ ነበራት።

በታላቁ የአዱሊስ ወደብ አማካኝነት የሕንድ ውቅያኖስን እና የሜዲትራኒያንን የንግድ መስመሮች በመቆጣጠር፣ የራሷን ሳንቲም በማተም እና ጠንካራ የባሕር ኃይል በማሰማራት ከታላላቅ የዓለም ኃያላን ተርታ ተሰልፋ እንደነበር ታሪክ የማይክደው ሀቅ ነው።

ቀዳማዊ አፄ ዓምደጽዮን እና አፄ ዘርዓ ያዕቆብን የመሳሰሉ ነገሥታት የቀይ ባሕርን ጠረፍ እና የዘይላን የንግድ ኮሪደር ለመጠበቅ ከፍተኛ መዋቅሮችን ዘርግተው ነበር።

በዘመናዊቷ ኢትዮጵያም ቢሆን በቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ ዘመን የተመሠረተው የባሕር ኃይል በቀይ ባሕር አካባቢ ያለውን የጸጥታ ሚዛን ለመጠበቅ ሙሉ አቅም ነበረው።

ታሪካዊ አሻጥሮች እና ኢትዮጵያን ከባሕር የማራቅ ሤራ
ይህ የተፈጥሮ እና የታሪክ ባለቤትነት ግን በውጭ ኃይሎች ሤራ በተደጋጋሚ ሲደናቀፍ ቆይቷል።

እ.አ.አ ሰኔ 3 ቀን 1884 በእንግሊዝ መንግሥት እና በአፄ ዮሐንስ 4ኛ መካከል የተፈረመው የሂውት ውል (Hewett Treaty) ለዚህ ሤራ ዋነኛ ማሳያ ነው።

ኢትዮጵያ በሱዳን የተከበቡ የግብፅ ወታደሮችን በሰላም ለማስወጣት ቃሏን ብትጠብቅም፣ እንግሊዝ ግን ምፅዋን ለጣልያኖች አሳልፋ ሰጠች።

በሌላ በኩል ደግሞ የሱዳን መህዲስቶችን በማነሳሳት አፄ ዮሐንስ 4ኛ በመተማ በኩል በሁለት ግንባር እንዲወጠሩ የጂኦፖለቲካ ሤራ ተጠነሰሰ።

በ1928 ዓ.ም ፋሺስት ጣሊያን ሀገራችንን ስትወርር ጅቡቲን ትቆጣጠር የነበረችው ፈረንሳይ ኢትዮጵያ በሕጋዊ መንገድ የገዛቻቸው የጦር መሣሪያዎች ወደ መሃል አገር እንዳይገቡ ማገዷ አይዘነጋም።

ይህም ከረጅም ጊዜ ጀምሮ ሲቀነባበር የኖረው ሤራ የኢትዮጵያ ከቀይ ባሕር መራቅ ለደኅንነቷ ምን ያህል አደገኛ እንደሆነ በግልፅ ያሳየ ነበር።

የምፅዋ ሰቆቃ እና የትውልዱ የደም መስዋዕትነት
የኢትዮጵያ ልጆች የባሕር በራቸውን ለማስጠበቅ የከፈሉት የደም ዋጋ መቼም አይረሳም። የካቲት 1982 ዓ.ም በምፅዋ ወደብ የተካሄደው ውጊያ በታሪካችን እጅግ ከፍተኛ መስዋዕትነት ከተከፈለባቸው አውደ ውጊያዎች አንዱ ነው።

ለአሥር ቀናት ያለማቋረጥ በተካሄደው መራራ ፍልሚያ ከ9 ሺህ በላይ የኢትዮጵያ ወታደሮች ተሰውተዋል።

የ6ኛ ነበልባል ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል ተሾመ ተሰማ እና የ3ኛ ሜካናይዝድ ክፍለ ጦር ምክትል አዛዥ ኮሎኔል በላይ አስጨናቂ በጠላት እጅ ላለመማረክ የኢትዮጵያን ባንዲራ ለብሰው ሕይወታቸውን የሰጡበት ቆራጥ ውሳኔ የዚህ እውነት የዘለዓለም ምስክር ነው።

የዛሬው ትውልድ መብቱን ሲጠይቅ፣ ያን አጥንቱን የዘራበትን እና ደሙን ያፈሰሰበትን ታሪክ እያስታወሰ ነው።

የኢትዮጵያ ጥያቄ፡ ከቀጣናዊ ሰላም እስከ ዓለም አቀፍ ትስስር
ዛሬ የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ የታሪክ ብቻ ሳይሆን የነባራዊ እውነታ እና የህልውና ጥያቄ ነው።

ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት፣ በፍጥነት እያደገች ያለች እና የ 'BRICS' አባል የሆነች ሀገር ወደብ አልባ ሆና መቆየቷ ለራሷ ብቻ ሳይሆን ለዓለም አቀፉ የንግድ ሰንሰለትም ማነቆ ነው።

ባሕሩ መቶ ኪሎ ሜትር እንኳን በማይሞላ ቅርበት እያለ በየዓመቱ ከ1.5 አስከ 2 ቢሊዮን ዶላር የወደብ ኪራይ መክፈል ሀገራዊ የኢኮኖሚ ዕድገትን በእጅጉ የሚገታ ነው።

የኢትዮጵያ ጥያቄ ዓለም አቀፍ ሕግን የተከተለ እና በተባበሩት መንግሥ

Address

Behind To Plaza Hotel
Addis Ababa
251

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bole 04 communicatiion posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Bole 04 communicatiion:

Shortcuts

Share