17/06/2026
ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የአደጋዎች ቅድመ ማስጠንቀቂያ ግንዛቤ መፍጠሪያ ዘመቻ አካሄደ
በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር የሶማሌ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ከኔዘርላንድ ቀይ መስቀል ጋር በመተባበር በ‘የውሃ አቅርቦት ለአየር ንብረት ለውጥ እርምጃ ማዕከል ፕሮግራም (Water at the Heart of Climate Action Program, Ethiopia)- የድርቅ መከላከል እርምጃና የቅድመ ማስጠንቀቂያ ፕሮቶኮል (EAP) ትግበራ አማካይነት በክልሉ ለሀርሺን ወረዳና ለቀበሌ የቅድመ ማስጠንቀቂያ ኮሚቴ አባላትና ለሃርሺን ወረዳ የማኅበሩ በጎ ፈቃደኞች የግንዛቤ መፍጠሪያ መርሃ-ግብር አካሂዷል።
የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ-ግብሩ የማኅበረሰቡን ዝግጁነት ለማጠናከር እና በድርቅ ቅድመ ማስጠንቀቂያ ዘዴዎችንና የቅድመ እርምጃ ተግባራትን ላይ ያለውን ግንዛቤ ለማሳደግ ያለመ እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን ተሳታፊዎች የቅድመ ማስጠንቀቂያ መረጃን በወቅቱ ለማሰራጨት እና ከድርቅ ጋር ለተያያዙ አደጋዎች በቅድመ ጥንቃቄ የተሞሉ ምላሾች እንዲሰጡ የሚያስችላቸውን ዕውቀት እና ስነ- ዘዴዎችን ከስልጠናው ማግኘታቸው ነው የተገለጸው።
ከስልጠናው በኋላም የአደጋዎች ቅድመ ማስጠንቀቂያ መልዕክቶች በተሽከርካሪዎችና ቤት ለቤት በመሄድ ለማኅበረሰቡ እንዲደርሱ ተደርገዋል፡፡ይህም ተጋላጭ ቤተሰቦች ለድርቅ ተጽዕኖዎች ቀድመው መዘጋጀት እንዲችሉ ወሳኝ መረጃ እና መመሪያ እንዲያገኙ አድርጓቸዋል።
ተነሳሽነቱ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር የማኅበረሰብን የመቋቋም አቅም ለማጠናከር፣ ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር የተያያዙ አደጋዎችን ተጽእኖ ለመቀነስና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን በቅድመ ማስጠንቀቂያ እርምጃ( Anticipatory Action) እና በቅድመ ምላሽ ዘዴዎች ለመደገፍ የሚያደርገው ቀጣይ ጥረት አካል ነው።
ለሰብዓዊነት እንኖራለን!
------------------
The Branch Office Conducts an Early Warning Awareness Campaign
Under the Water at the Heart of Climate Action (WHCA) Program – Ethiopia Drought Activation and Early Action Protocol (EAP), the Ethiopian Red Cross Society (ERCS) Somali Regional Branch, in partnership with the Netherlands Red Cross, conducted an orientation session for Woreda and Kebele Early Warning Committee members, and Ethiopian Red Cross Society volunteers in Harshin Woreda.
The orientation aimed to strengthen community preparedness and enhance understanding of drought early warning mechanisms and early action measures. Participants were equipped with knowledge and tools to support the timely dissemination of early warning information and promote proactive responses to drought-related risks.
Following the training, early warning messages were shared with communities through mobile awareness campaigns using vehicles and house-to-house visits, ensuring that vulnerable households receive critical information and guidance to prepare for potential drought impacts.
The initiative forms part of ERCS’s ongoing efforts to strengthen community resilience, reduce the impact of climate-related hazards, and support vulnerable populations through anticipatory action and early response mechanisms.
We Live for Humanity!
EU Civil Protection & Humanitarian Aid Rode Kruis
---------------
📌Website: https://redcrosseth.org/
📌Instagram፡ https://www.instagram.com/ercs1935/
📌LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/ethiopian-red-cross-society/
📌YouTube: https://www.youtube.com/
📌X(Twitter): https://x.com/EthioRedCross
📌Telegram: https://t.me/ERCSHQ
📌 Tiktok: https://www.tiktok.com/
📌 Flickr፡- 137615657@N05/" rel="ugc" target="_blank">https://www.flickr.com/photos/137615657@N05/