Grace Leadership & Theological University GLTU

Grace Leadership & Theological University GLTU Grace Leadership & Theological University - GLTU is dedicated to equip future LEADERS through timely, cost effective training with BA MA and Ph. D.

18/04/2020

ዳዊትም በእግዚአብሄር በአምላኩ ልቡን አበረታ 1ሳሙ 30:6
በሰዎች ህይወት የተጠበቁና ያልተጠበቁ ብዙ ነገሮች ይደርሳሉ። ጥሩም መጥፎም ከባድና ቀላል አይነት።
በዳዊት ህይወት የደረሰው ግን ያልተጠበቀ ነው። ወደ ቤቱ እሱና አብረውት ያሉት ሲመለሱ የጠበቁትና የሆነባቸው ፈጽሞ የተለያዩ ነበሩ። ጉዳታቸው በማልቀስ ብቻ የሚያበቃ አልነበረምና ጨምረው ለማልቀስ ቢፈልጉ እንኳን አልቻሉም።
ዳዊት በዚህ መቀጠል እንደማያዋጣ ስላወቀ መፍትሄው ማልቀስ መቆጨት ሳይሆን ልብን ማበርታት እንደሆነ ገባው። ግን ልቡን የሚያበረታለት ሰው አልነበረም ይባስ ብለው የቅርብ የሚላቸው ከዱት።
ያለው አማራጭ በአምላኩ ልቡን ማበርታት ነበርና አበረታ። ወገኖች ሁኔታው ከባድ ሊሆን ይችላል መፍትሄው ስጋት ልቅሶና ፍርሃት ሳይሆን ልባችንን አበርትተን እንደ ዳዊት በሞት ጥላ መካከል እንኳን አንተ ከኔ ጋር ነህና ክፉን አልፈራም ብለን መዘመር ነው።

08/04/2020

የተወደዳችሁ የጸ ጋ ስነመለኮትና መሪነት ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በሙሉ;

በመላ ዓለም የገባው ወረርሽኝ የሰውን ልጅ አቅም የተፈታተነበትና ሰውም አቅሙን አውቆ ወደ አምላኩ ፊቱን ዞር አያደረገ ነው። እውነተኛና አዋጭ መሸሸጊያ ጌታ ብቻ መሆኑን እያወቀና ስለ እሱም ማሰብ የጀመረ ይመስላል። በየማለዳውም የዓለም ሃያል ሃገር የሆነችውና እኔ የምኖርባት ሀገር አሜሪካ የሞቱ ሰዎችን ቁጥር ልክ በሽቅድድም ሜዳ ላይ እንዳለ ቀደመና ተቀደመ በሚባል የዕልቂት ስሌት ውስጥ ገብታለች።
የዚህ ወረርሽኝ መግባት የሰውን ሕይወት ከመቅጠፉ ባሻገር ብዙ የኢኮኖሚ ቀውስ አምጥቶአል መድሃኒት አለመገኘቱ ደግሞ ሰዎች በቤታቸው አንዲቀመጡና እንዳይቀራረቡ ወደሚል መመሪያ ውስጥ አስገብቶናል።
ስለዚህም አግዚአብሔር በስልጣኑ በቃ ብሎት ይህ የመከራ ጊዜ እስኪያልፍ ድረስ ራሳችሁን ጠብቁ። ከጤና ባለሙያዎች የሚሰጠውንም መመሪያና ሕግ በመቀበል ከቫይረሱ ሽሹ።
ከሁሉም በላይ በጸጋው አንደዳነ ሰው አጥብቃችሁ የጌታን ፊት ፈልጉ። የመጣው ሞት በየሁላችን ቤት ላይ ጥላውን አጥልቷል እኛ ግን እንደ ዳዊት “በሞት ጥላ ውስጥ ባልፍ እንክዋን ክፉን አልፈራም” አንላለን።
እንደምታውቁት ትምህርት ቤታችን ይህ ችግር እስኪያልፍ ድረስ አገልግሎት መስጠቱን አቁሞአል። በዚህም ምክንያት ሊመጣ ካለው የኢኮኖሚ ጫና የምንወጣበትን መንገድም አንዲያመቻችልን በዘወትር ጸሎታችሁ አስቡን።
ለጊዜው ሰራተኞች ሁሉም በየቤታቸው ስለሚሆኑ በቀጥታ እኔን ለማነጋገር የምትፈልጉ በስልክ ቁጥር (510) 600 9812 ላይ በቴሌግራም ላይ ብትደውሉ ታገኙኛላችሁ። [email protected] በሚል አድራሻዬም ጻፉልኝ።
መቼ ይጀመራል ለሚለው ጥያቄ መልሱን ማንም አያውቅም። ዘንድሮ ምርቃት ይኖራል ወይ? የሚለውም አሁን ሰዓት ላይ መልስ የለውም። ግን አይተከታጠልን ኢንፎርሜሽን እናስተላልፋለን። ሁኖም ግን ችግሩ ከተነሳ የማይኖርበት ምክንያት የለም። ምናልባት ትምህርቱን በኦን ላይን ለመማር ለሚፈልጉ ሁኔታን አያመቻቼን ነው አንደጨረስን በፌስ ቡክና በተለያየ መንገድ አናስታውቃለን። ግን በዚህ ጉዳይ ተግዳሮትን ስላለብን አጥብቃችሁ ጸልዩልን። እኔም ስለእናንተና የእናንተ ስለሆኑት አጸልያለሁ፣ ተባርኩ ጌታ ከክፉ ይጠብቃችሁ።

ዶ/ር ደረጀ ፋንታዬ (ፕሬዚደንት)

እባካችሁ ይህንን የምታነቡ ሰዎች የፌስ ቡክ ተከታዮች ላልሆኑ ተማሪዎቻችን አስተላልፉልን

24/02/2020
24/02/2020
15/11/2019

we are enrolling New Students for 2012 academic year

23/02/2019

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Grace Leadership & Theological University GLTU posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share