Ifada Islamic Organization

Ifada Islamic Organization በተያያዙ ክንዶች
በኢስላማዊ ቤተሰብነት

የተረሳውን ማስታወስ፣
የጎደለውን መሙላት፣
በልብ ለልብ ትስስር
ስለ እስልምና መተዋወስ፣

ሁሉንም በህብረት!

ባሳለፍነው ሳምንት ዳሽን ባንክ 30ኛ አመቱን ምክንያት በማድረግ በተዘጋጀው ዳሽን ኤክስፖ ላይ የዳሽን ባንክ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ስምንተኛ አመት የምስረታ በዓሉን አክብሯል።በእለቱ...
15/05/2026

ባሳለፍነው ሳምንት ዳሽን ባንክ 30ኛ አመቱን ምክንያት በማድረግ በተዘጋጀው ዳሽን ኤክስፖ ላይ የዳሽን ባንክ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ስምንተኛ አመት የምስረታ በዓሉን አክብሯል።

በእለቱ የዳሽን ባንክ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ሸሪክ ከደንበኞቹ የሰበሰበውን 16.5 ሚሊየን ብር ለተለያዩ በጎ አድራጎት ተቋማት ድጋፍ አድርጓል።

ድጋፍ ከተደረገላቸው ግብረሰናይ ተቋማት መካከል የኢፋዳ ኢስላማዊ ድርጅት አንዱ ሲሆን፤ በተዘጋጀው የምስረታ ክብረ በዓል ላይ የ500ሺህ ብር የገንዘብ ድጋፍ ለኢፋዳ ኢስላማዊ ድርጅት አበርክቷል።

የኢፋዳ ኢስላማዊ ድርጅት የዳሽን ባንክ ከወለድ ነፃ የባንክ ስርአት እንዲሁም ከሚሰጣቸው የባንክ አገልግሎቶች ባሻገር እየተወጣ ያለውን ማህበራዊ ኃላፊነት ስራ አድንቋል።

28/04/2026

በወር 1000 ብር ብቻ እየከፈሉ በአካል ኪታብ የመጀመር ህልምዎን ያሳኩ!

0908819999
0908829999

በመደወል አሊያም በቴሌግራም አድራሻችን በማናገር መመዝገብ ትችላላችሁ።

በአካል 1000 ብር ብቻ
በኦንላየን 500 ብር ብቻ

በደረጃ 1 የሚሰጡ ቂርዓቶች
ሰፊና፣ ኹላሰቱ ኑረል የቂን፣ አርበዒን ሀዲስ

የቂርዓት ቀን እና ሰአት:-
ቅዳሜ እና እሁድ ከጠዋቱ 3:00 - 6:00

ደረጃ 2 የሚሰጡ ቂርዓቶች
ኡምደቱል አህካም፣ ረውደቱል አንዋር እና ሪያዱሷሊሂን

የቂርዓት ቀን እና ሰአት:-
ቅዳሜ እና እሁድ ከቀኑ 8:00 - 10:00
ወይም
ማክሰኞ እና ሀሙስ ከጠዋቱ 3:00 - 6:00

አድራሻ
ቤተል ሚና የገበያ ማዕከል 2ኛ ፎቅ

ኢፋዳ የቂርዓት ማዕከል

30/11/2025
የእኛ ቀን
30/11/2025

የእኛ ቀን

ያማረ የቁርአን ቲላዋ 😍😍😍
30/11/2025

ያማረ የቁርአን ቲላዋ 😍😍😍

የኢፋዳ ኢስላማዊ ድርጅት 2ተኛ አመት የመክፈቻ ጉባኤ እንዲሁም የ44 የውሀ ፕሮጀክቶች የምርቃት ስነ-ስርዓት ፕሮግራም።
30/11/2025

የኢፋዳ ኢስላማዊ ድርጅት 2ተኛ አመት የመክፈቻ ጉባኤ እንዲሁም የ44 የውሀ ፕሮጀክቶች የምርቃት ስነ-ስርዓት ፕሮግራም።

ኢፋዳ ዜና ኢፋዳ ጤና በዛሬው እለት የደም ልገሳ መረሀ ግብር አከናወነ። ከሀድረል ተቋም ውስጥ ካሉ ዲፓርትመንቶች አንዱ የሆነው የጤና ዘርፍ  ከፍተኛ የደም ለጋሾች ቁጥር የተስተናገደበትን ዘ...
17/08/2025

ኢፋዳ ዜና

ኢፋዳ ጤና በዛሬው እለት የደም ልገሳ መረሀ ግብር አከናወነ። ከሀድረል ተቋም ውስጥ ካሉ ዲፓርትመንቶች አንዱ የሆነው የጤና ዘርፍ ከፍተኛ የደም ለጋሾች ቁጥር የተስተናገደበትን ዘመቻ ከኢፋዳ ማህበረሰብ የሀድራ ትስስር ጋር በመተባበር የኢፋዳ የማህበራዊ ሀላፊነት ቀን በሚል ስያሜ ዘመቻውን በዛሬው ዕለት አከናውኗል።

በዛሬው የኢፋዳ ማህበረሰብ የሀድራ ትስስር የማህበራዊ ሀላፊነት ቀን ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የሴቶች የንፅህና መጠበቂያዎች ገቢ የተደረገ ሲሆን የቲሸርት ሽያጭም ተካሒዷል።

የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ9 ህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ-ፈቃድ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ዋና ሃላፊ የሆኑት ሲስተር ኤልሳቤት ይስማ አረዳ ወጣቱ እንደዚህ አይነት የበጎነት ስራዎች ላይ መሳተፋ በእጅጉ የሚበረታታና ይበል የሚያሰኝ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል ።

አክለውም የኢፋዳ ማህበረሰብ የሀድራ ትስስር አባላትን እና አመራሮችን አመስግነው ዛሬ የተመዘገበው የደም ለጋሾች ቁጥር እስካሁን ከነበረው ተሳትፎ ከፍተኛ ቁጥር የተስተናገደበትና በአንድ ቀን ውሎ ውስጥ ይመዘገቡ ከነበሩ የደም ለጋሾች ቁጥር እጥፍ እንደነበር ገልጸዋል።

በቀጣይ የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 የህብረተሰብ ተሳትፎ እና በጎ አድራጎት ከኢፋዳ ማህበረሰብ የሀድራ ትስስር ጋር የተለያዩ ስራዎችን መስራት እንደሚፈልግ አስታውቀዋል።

የኢፋዳ ማህበረሰብ የሀድራ ትስስር የማህበራዊ ሀላፊነት ቀን ላይ ባደረገው የደም ልገሳ ዘመቻ የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ የደም ለጋሾችን ቁጥር ሪከርድ ሰብሯል።

በእለቱ የኢፋዳ ኮምዩኒኬሽን ያነጋገራቸው ተሳታፊዎች እንደዚህ አይነት ስራዎች ላይ መሳተፍ ከሚሰጠው የህሊና እርካታ በተጨማሪ ሁሉም ሊያደርገው የሚገባው የስብአዊነት ተግባር መሆኑን ተናግረዋል።

ለዚህ የማህበራዊ ሀላፊነት ተግባር መሳካት ከፍተኛ የሆነ ርብርብ እና ትጋት ያደረጉ ባለድርሻ አካላት አስተባባሪዎች እንዲሁም ተሳታፊዎች ለዚህ ወደር የማይገኝለት መልካም ስራ ልትመሰገኑ እና ልትደነቁ ይገባል ሲል የኢፋዳ ኮምዩኒኬሽን ይገልፃል።

ኢፋዳ ኮምዩኒኬሽን

ልክ እንደ ዩሱፍ አለይሂ ሰላም ፍቅርን ወዳጅነትን ጓደኝነትን ወንድምነትን ቤተሰብን ለመጠበቅ ስህተትን በውስጣቹ ሸሽጋቹ ለምትይዙ እና በይቅርታ የምታልፉ ባለ ንፁህ ልብ የአላህ ባሮች እንደ ...
08/08/2025

ልክ እንደ ዩሱፍ አለይሂ ሰላም ፍቅርን ወዳጅነትን ጓደኝነትን ወንድምነትን ቤተሰብን ለመጠበቅ ስህተትን በውስጣቹ ሸሽጋቹ ለምትይዙ እና በይቅርታ የምታልፉ ባለ ንፁህ ልብ የአላህ ባሮች እንደ አዩብ ላለፋት ብዙ አመታት መከራን ችግርን ማጣትን ከሰው መገለል ደርሶባቹ የአላህን ነስር በሰብር በትእግስት የምትጠብቁ ይህ ባሮች ባላቹበት ይጠብቃቹ። የሚያምር ጁምአን ተመኘንላቹ!

ኢፋዳ ኮምዩኒኬሽን

29/06/2025

Address

Addis Ababa

Opening Hours

Monday 08:30 - 05:00
Tuesday 08:30 - 05:00
Wednesday 08:30 - 05:00
Thursday 08:30 - 05:00
Saturday 08:30 - 05:00
Sunday 08:30 - 05:00

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ifada Islamic Organization posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share