15/05/2026
ባሳለፍነው ሳምንት ዳሽን ባንክ 30ኛ አመቱን ምክንያት በማድረግ በተዘጋጀው ዳሽን ኤክስፖ ላይ የዳሽን ባንክ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ስምንተኛ አመት የምስረታ በዓሉን አክብሯል።
በእለቱ የዳሽን ባንክ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ሸሪክ ከደንበኞቹ የሰበሰበውን 16.5 ሚሊየን ብር ለተለያዩ በጎ አድራጎት ተቋማት ድጋፍ አድርጓል።
ድጋፍ ከተደረገላቸው ግብረሰናይ ተቋማት መካከል የኢፋዳ ኢስላማዊ ድርጅት አንዱ ሲሆን፤ በተዘጋጀው የምስረታ ክብረ በዓል ላይ የ500ሺህ ብር የገንዘብ ድጋፍ ለኢፋዳ ኢስላማዊ ድርጅት አበርክቷል።
የኢፋዳ ኢስላማዊ ድርጅት የዳሽን ባንክ ከወለድ ነፃ የባንክ ስርአት እንዲሁም ከሚሰጣቸው የባንክ አገልግሎቶች ባሻገር እየተወጣ ያለውን ማህበራዊ ኃላፊነት ስራ አድንቋል።