መቄዶንያ-mekedonia

መቄዶንያ-mekedonia ሁሌም ምሽት 12 ሰዓት ጀምሮ በመቄዶንያ youtube live fundraising ላይ ይሳተፉ! ZELL OR CASHAPP 240,938,2992

የሁሉም ባንክ አካውት ቁጥራችን - 7979
call 8131/0979797979/0989898989
(10)

የ40 ቀን መታሰቢያኮሚሽነር  ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል  የኢ/ያ ፌደራል  ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ የእህታቸዉን ወ/ሮ እህተ ማርያም የ40 ቀን  ምክንያት በማድረግ በመቄዶንያ ዋናዉ ግቢ...
13/06/2026

የ40 ቀን መታሰቢያ

ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል የኢ/ያ ፌደራል ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ የእህታቸዉን ወ/ሮ እህተ ማርያም የ40 ቀን ምክንያት በማድረግ በመቄዶንያ ዋናዉ ግቢ ከአረጋዉያን አባቶች እና እናቶች ጋር የፀሎት እና የነፍስ ይማር እንዲሁም የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም አድርገዋል!!!

እህታችን እህተ ማርያም በማለፋቸዉ የተሰማንን ጥልቅ የሆነ ሀዘን እየገለፅን ለቤተሰቦቻቸዉ ፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸዉ እንዲሁም ለስራ ባልደረቦቻቸዉ መፅናናትን እንመኛለን!!

የእህታችን እህተ ማርያምን ነፍስ በአፀደ ገነት ያኑርልን!!

መቄዶንያ

ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው!
11/06/2026

ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው!

04/06/2026
ብፁዕነታቸዉ  ድጋፍ  ሲያደርጉ  የመጀመሪያቸዉ አይደለም ፣ እድሜ ዘመናቸዉን ሲደግፉ ፣ ሲያበረታቱ ፣ ሲያግዙየቆዩ ደግ ፣ ሩህሩህ ፣ አርዓያ እና ምሳሌ የሆኑ አባት ናቸዉ!! (ዘማሪት ፋንቱ...
04/06/2026

ብፁዕነታቸዉ ድጋፍ ሲያደርጉ የመጀመሪያቸዉ አይደለም ፣ እድሜ ዘመናቸዉን ሲደግፉ ፣ ሲያበረታቱ ፣ ሲያግዙ
የቆዩ ደግ ፣ ሩህሩህ ፣ አርዓያ እና ምሳሌ የሆኑ አባት ናቸዉ!! (ዘማሪት ፋንቱ ወልዴ)

በምድር ላይ ስንኖር እራሳችን በእራሳችን ላይ የምንፈርደዉ ፍርድ ፈፅሞ የተሳሳተ ነዉ ፣ እጃችንን ለፍርድ አናንሳ የአባታችን ደግነት ፣ ለሰዉ ያላቸዉ ፍቅር እና ክብር ከልጅነታቸዉ ጀምሮ የመጣ ነዉ!!(ኡስታዝ ጀማል)
ይህ ቤት የተሰራበት ዋናዉ አላማ የተቸገሩትን ለመርዳት እና ተስፋ ለመስጠት ሲሆን እኔም በሙያየ እንዲሁም በምችለዉ አቅም ድጋፍ ለማድረግ እና ከመቄዶንያ ጎን ለመሆን ቃል እገባለሁ!! (ኢንጅነር አማኑኤል ጌታሁን)

ይህ የፋይናንስ እና የሞራል ድጋፍ በችግር ዉስጥ ላሉት ወገኖቻችን የሚሰጥ የስነ -ልቦና እገዛ ነዉ!! (ዶ/ ጌትነት ፈለቀ)

ብፁዕ አባታችን ለመቄዶንያ ድጋፍ ያደረጉት ቤት የሚከራይ ወይም የሚሸጥ ሳይሆን ለመቄዶንያ 57ኛ ቅርንጫፍ (አቡነ ፋኑኤል መቄዶንያ ቅርንጫፍ) ሆኖ የሚያገለግል በመሆኑ ይህንን ዉድ ስጦታ አስመልክቶ የምስጋና እና የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም በመቄዶንያ ዋናዉ ግቢ ያደረግን ሲሆን በዚሁ ዕለት ሌላ ብስራት ይዘን መተናል፡፡

በአለፈዉ ዓመት በተሰበሰበዉ ገንዘብ የፊኒሽንግ እቃዎችን እና ማሽነሪዎችን እያስገባን ሲሆን ግንቦት 22 ቀን 2 ኮንቴነር እቃዎች እና ማሽነሪዎች አስገብተናል፡፡

በአጠቃላይ እስካሁን የገቡት የፊኒሽንግ እቃዎች እና ዘመናዊ ማሽነሪዎች 111 ኮንቴነር የደረሱ ሲሆን ወደ ፊትም ብዙ የሚገቡ እቃዎች እና ማሽነሪዎች አሉን፡፡

የእኔን የታናሻችሁን ጥሪ አክብራችሁ የተገኛችሁ ብፁዓን አባቶቼ ፣ ቀሳዉስት እና ዲያቆናት እንዲሁም የሚዲያ አካላት እና ጥሪ የተደረገላችሁ እንግዶች በመቄዶንያ አረጋዉያን ስም ከልብ እናመሰግናለን!!

ለፍርድ እጃችንን አናንሳ  (ኡስታዝ ጀማል)!!ኡስታዝ ጀማል የዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢዋ  የሀይመኖት ተቋማት ጉባኤ ም/ ሰብሳቢ እና በኪንግ ኦፍ አባይ በአባይ ግድብ ዙሪያ መልስ በመስጠት...
03/06/2026

ለፍርድ እጃችንን አናንሳ (ኡስታዝ ጀማል)!!

ኡስታዝ ጀማል የዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢዋ የሀይመኖት ተቋማት ጉባኤ ም/ ሰብሳቢ እና በኪንግ ኦፍ አባይ በአባይ ግድብ ዙሪያ መልስ በመስጠት የምናውቃቸው በምስጋና እና የማዕድ ማጋራት ፕሮግራማችን ላይ ከብፁዓን አባቶቻችን ጋር በመገኘታቸዉ የተሰማቸዉን ደስታ ገልፀዋል፡፡

በዚህ ፕሮግራም ላይ እንደተናገሩት መቄዶንያን ለመጎብኘት ረቂቅ ምክንያት አንሻም ምክንያቱም መቄዶንያ ቋንቋ ፣ ዘር እና ሀይማኖት ሳይለይ ሰዉን ሰዉ በመሆኑ ብቻ መርዳት መቻሉ እና በ56 ከተሞች ላይ ቅርንጫፎችን ዘርግቶ በሰፊዉ እያስተዳደረ መገኘቱ ከበቂ በላይ ነዉ፡፡

ይህ የብፁዕ አባታችን ስጦታ ሁላችንም የእርዳታ እጆቻችንን እንድንዘረጋ ፣ ያለንን እንድናካፍል ተምሳሌት የሆነ ተግባር ነዉ ብለዉናል፡፡

በመጨረሻም በምድር ላይ ስንኖር እራሳችን በእራሳችን ላይ የምንፈርደዉ ፍርድ ረፅሞ የተሳሳተ ነዉ ፣ እጃችንን ለፍርድ አናንሳ የአባታችን ደግነት ፣ ለሰዉ ያላቸዉ ፍቅር እና ክብር ከልጅነታቸዉ ጀምሮ የመጣ ነዉ በማለት የአባታችንን መልካም ተግባር እንድንከተል መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

ጥሪያችንን አክብራችሁ ስለተገኛችሁ በተገልጋዮቻችን ስም ከልብ እናመሰግናለን!!!

👉መጋቢት 6 የተጀመረዉ የመቄዶንያ አመታዊ የገቢ ማሰባሰቢያ  68ኛ ቀኑን  የያዘ ሲሆን በዛሬዉ ዕለት በመቄዶንያ ስቱዲዮ በመገኘት የቀጥታ ስርጭታችንን  በድምቀት ሲመሩልን የነበሩት የብዙ ሙ...
31/05/2026

👉መጋቢት 6 የተጀመረዉ የመቄዶንያ አመታዊ የገቢ ማሰባሰቢያ 68ኛ ቀኑን የያዘ ሲሆን በዛሬዉ ዕለት በመቄዶንያ ስቱዲዮ በመገኘት የቀጥታ ስርጭታችንን በድምቀት ሲመሩልን የነበሩት የብዙ ሙያ ባለቤት የሆነችዉ ጋዜጠኛ መቅደስ ደበሳይ እና ጋዜጠኛ ጥላሁን በየነ ናቸዉ፡፡

👉በቀጥታ ስርጭታችን ላይ የክብር እንግዳ ሆነዉ የተገኙልን የፍኖተ ሎዛ ት/ቤት መስራች ወ/ሮ ሳራ ፣ማህተቤ ታደሰ (ርዕሰ መምህር) ፣ መምህራን እንዲሁም ታዳጊ ተማሪዎች ናቸዉ፡፡

👉ተወዳጇ እና አንጋፋዋ ጋዜጠኛ መቅደስ ደበሳይ እንዲህ ስትል ልብ የሚነካ መልዕክቷን አስተላልፋለች!!

👉ስሙን በተደጋጋሚ ሰማነዉ ማለት እናዉቀዋለን ማለት አይደለም ሁላችንም መጠን ስንጎበኝ በደንብ እናዉቀዋለን ስለዚህ መጥታችሁ ጎብኙ ፣ ዛሬ ላይ የቆምን ቢመስለንም ላለመዉደቃችን ምንም ዋስትና የለንም ብንወድቅ ቤታችን ነዉ እና ሁሌም ከመቄዶንያ ጎን እንሁን በማለት መልዕክቷን አስተላልፋለች::

👉የዛሬዉን ቀን ለየት የሚያደርገዉ የፍኖተ ሎዛ ተማሪ የሆነችዉ ራኬብ የማነህ በልደቷ ቀን በመቄዶንያ ስቱዲዮ በመገኘት ቀጥታ ስርጭቱ ላይ መሳተፏ ሲሆን በዚህ የልጅነት ጊዜዋ መቦረቅ ሳትሻ ፣ መናፈሻ ሳትመርጥ ልደቴን ከመቄዶንያ አረጋዉያን ጋር ማለቷ ነዉ፡፡
👉ይቺ ታዳጊ ህፃን 18ኛ ዓመት ልደቷን በመቄዶንያ ስቱዲዮ በእናቶች እና አባቶች ምርቃት ተባርካ ፣ በፍኖተ ሎዛ ት/ቤት ተማሪዎች ፣ መምህራን ታጅባ በድምቀት አክብራለች፡፡

👉እንኳን ተወለድሽ ቀሪ ዘመንሽ የተባረከ ይሁን!!!
🎂🎂🎂🎂🎂🎂🎂

👉ይህም ብቻ አይደለም በዛሬዉ የገቢ ማሰባሰቢያ ላይ ከፍተኛ ገንዘብ በማስገባት ቀዳሚዋ ሆናለች፡፡

👉ጥሪያችንን አክብራችሁ የተገኛችሁ እንግዶቻችን እንዲሁም ድጋፍ ስታደርጉ የነበራችሁ በሀገር ዉስጥም በሀገር ዉጪም የምትገኙ ኢትዮጵያዉያን ከልብ እናመሰግናለን!!
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏

ሰዉን ለመርዳት ሰዉ መሆን በቂ ነዉ!!

መቄዶንያ

ስንሰጥ በደስታ ይሁን (ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ)!!!🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የሲዳማ እና ጌዲዮ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ  በምስጋና   እና  በማዕድ ማጋራት  ፕሮግራሙ ላይ ተገኝተዉ ...
31/05/2026

ስንሰጥ በደስታ ይሁን (ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ)!!!
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏

ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የሲዳማ እና ጌዲዮ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምስጋና እና በማዕድ ማጋራት ፕሮግራሙ ላይ ተገኝተዉ እንደተናገሩት መስጠት የሚጀምረዉ ራስን ከመስጠት ሲሆን ራሱን ለእግዚአብሔር የሰጠ ቁሳቁስ ወይም ገንዘብ ለመስጠት አይቸገርም፡፡

👉ስጦታ ከዉስጥ የመነጨ ፣ በሀይማኖት የፀና ፣ ርህራሄ የተሞላበት ፣ በመንፈሳዊነት የተቃኘ ፣ እንዲሁም የሌሎችን ችግር ፣ ህመም ፣ ረሀብ እና ጥም መጋራት ሲሆን ከዉስጥ የመነጨ ደስታን ይሰጠናል በማለት የመስጠትን ጥልቅ ሚስጥር ገልፀዉልናል፡፡

👉ብፁዕነታቸዉ ለመቄዶንያ ያደረጉት ድጋፍ ሊበረታታ የሚገባዉ አርዓያ እና አስተማሪ የሆነ ተግባር መሆኑን ገልፀዉ ሁላችንም ከዚህ መልካም ተግባር አርዓያነትን ወስደን የቻልነዉን ሁሉ ለመቄዶንያ ድጋፍ እናድርግ ፣ መቄዶንያን እናግዝ ብለዉናል!!

👉በመጨረሻም በዚህ የምስጋና እና የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም ላይ በመገኘታቸዉ የተሰማቸዉን ጥልቅ የሆነ ደስታ ገልፀዋል!!

31/05/2026
31/05/2026

Address

Hayat
Addis Ababa
4315

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when መቄዶንያ-mekedonia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to መቄዶንያ-mekedonia:

Share