17/10/2025
https://www.facebook.com/100064499087509/posts/1202601121899846/
በኢትዮጵያ ብሎም በክልላችን የክረምት ወቅት ማለፋን ተከትሎ የወባ ወረርሽኝ በስፋት ሊከሰት ይችላል
የወባ በሽታ በትንኝ አማካኝነት ከታመመ ሰው ወደ ጤነኛው የሚተላለፍ በዋነኛነት በትኩሳት የሚገለጥ ተወሳስቦ ለከፍተኛ አደጋ ሊዳርግ የሚችል በሽታ ነው፡፡
በሽታው በዓለም ላይ የበርካቶችን ህይወት የቀጠፈና በትንኝ አማካኝትት የሚከሰት ተላላፊ በሽታ እንደሆነም ይነገራል፡፡
በተለይ በኢትዮጵያ ፕላዝሞዴም ፋሲፋረም በተለምዶ ቢጫ ወባ የሚባለውን እና አንድ ሶስተኛው ደግሞ ቫይቫክስ በተባለ ተህዋስ ዝርያ የሚከሰት ነው።
ወንድ እና ሴቴ ተህዋስ በወባ ውስጥ አንድ ሳምንት ያድግና ትንኟ ለመራባት የሰው ደም የሚያስፈልጋት በመሆኑ በዚህ ሁኔታ ሰውን በምትነክስበት ጊዜ በሽታውን ታስተላልፋለች፡፡
ትንኟ ለመራባት ቆላማ አካባቢ በመምረጥ ከባህር ጠለል በላይ ከ1ሺህ 400 ሜትር በታች በሆኑ አካባቢዎች ላይ እንደምትገኝና ከዛ በላይ ባለ ከፍታ የመራባት ምጣኔዋ እንደሚቀንስ ይገለፃል፡፡
በሽታው ከዚህ በፊት ለተያዘ ሰው እንዲሁም በተለይ በነፍሰ ጡር እናቶች እና ህፃናት ላይ የመከላከል አቅማቸው አናሳ በመሆኑ የከፋ ጉዳት ያደርሳል፡፡
በአብዛኛው የክረምት ወቅት አልፎ የበጋ ወቅት ሲጀምር ውሀዎች ሙሉ ለሙሉ ስለማይደርቁ እና የታቆሩ ውሀዎች ስለሚኖሩ እንዲሁም በትንንሽም ውሀዎች የመራባት እድል ስለሚኖር ለትንኞች መራባት አመቺ ይሆናል፡፡
የወባን በሽታን ለመከላከል ትንኟ የምትራባባቸውን ቦታዎች ማጽዳት ያስፈልጋል ያቆሩ ውሀዎችና የቆሸሹ ነገሮችን ማስወገድም ይገባል፡፡
ጸረ-ትንኝ ኬሚካሎች በሚረጩበት ጊዜ ቀለም መቀባት፣ ማጠብ እንደማይገባ እንዲሁም በጸረ ትንኝ የተነከረ አጎበር መጠቀም እንደሚገባ የህክምና ባለሙያዎች ይመክራሉ፡፡
#አብክመጤናቢሮ