Health, Development and Anti-Malaria Association - HDAMA

Health, Development and Anti-Malaria Association - HDAMA This page is intended to help promote HDAMA as an NGO, thereby endorse its activities and accomplishments.

የጤና፣ ልማት እና ፀረ-ወባ ማህበር በትምባሆ ቁጥጥር ዙሪያ መረጃዎችን በአንድ ማዕከል የሚያቀርብ አዲስ ዳሽቦርድ ይፋ አደረገ አዲስ አበባ — የጤና፣ ልማት እና ፀረ-ወባ ማህበር (HDAMA)...
07/08/2026

የጤና፣ ልማት እና ፀረ-ወባ ማህበር በትምባሆ ቁጥጥር ዙሪያ መረጃዎችን በአንድ ማዕከል የሚያቀርብ አዲስ ዳሽቦርድ ይፋ አደረገ

አዲስ አበባ — የጤና፣ ልማት እና ፀረ-ወባ ማህበር (HDAMA) ከኢትዮጵያ ምግብ እና መድኃኒት ባለሥልጣን (EFDA)፣ ከዴቨሎፕመንት ጌትዌይ (DG) እና ከአፍሪካ ኢኮኖሚ ጥናት ማዕከል (CSEA) ጋር በመተባበር በትምባሆ ቁጥጥር ዙሪያ የሚገኙ መረጃዎችን በአንድ ማዕከል የሚያቀርበውን "TCDI Ethiopia" ዲጂታል ዳሽቦርድ በአማርኛ ቋንቋ አዘጋጅቶ በኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል ይፋ አድርጓል።

ይህ ዲጂታል ዳሽቦርድ የተበታተኑ የትምባሆ ቁጥጥር መረጃዎችን በአንድ ቋት በማሰባሰብ ለፖሊሲ አውጪዎች፣ ለሚዲያ አካላት፣ ለተመራማሪዎች እና ለመላው ህብረተሰብ መረጃን በቀላሉ ተደራሽ ለማድረግ የተወሰደ ትልቅ እርምጃ መሆኑ ተገልጿል።

በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት የማህበሩ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ አክሊሉ ጌትነት ዳሽቦርዱ በትምባሆ ቁጥጥር ዙሪያ የሚከናወኑ ተግባራት በሙሉ በትክክለኛና በተረጋገጠ መረጃ ላይ እንዲመሰረቱ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ገልጸዋል። የፕሮጀክቱ ማናጀር አቶ መላኩ ጌታቸው በበኩላቸው የዲጂታል ዳሽቦርዱን አጠቃቀምና አሰራር በተመለከተ ለታደሙት ተሳታፊዎች ዝርዝር ገለጻ አቅርበዋል።

በመጨረሻም ፖሊሲ አውጪዎችና የሕግ አስፈፃሚዎች ዳሽቦርዱን በመጠቀም የሕግ ማስከበር ሥራቸውን እንዲያጠናክሩ፣ ሚዲያዎችና የሲቪል ማህበራት ህዝቡን የማንቃት ስራቸውን በመረጃ ላይ መስረተው እንዲከውኑ፣ እንዲሁም ተመራማሪዎች ተጨማሪ ጥናቶችን ለማካሄድ ዳሽቦርዱን እንዲጠቀሙ ጥሪ ቀርቧል።https://ethiopia.tobaccocontroldata.org/am

30/07/2026
• Investing in Stronger and More Resilient Health Systems Access to quality healthcare depends not only on skilled healt...
24/07/2026

• Investing in Stronger and More Resilient Health Systems
Access to quality healthcare depends not only on skilled health professionals but also on the availability of essential medical equipment. Recognizing this, the MOMENTUM Integrated Health Resilience (MIHR) Project, funded by the United States Government and implemented by JSI Ethiopia in partnership with the Health Development and Anti-Malaria Association (HDAMA), has donated medical equipment worth more than ETB 3.5 million to health facilities under the South Wollo Zone Health center.
The donation includes 52 different types of medical equipment identified through joint supportive supervision with the Zone Health Department to address critical service delivery gaps and improve the quality of maternal, newborn, and child health services.
• Addressing Critical Healthcare Needs
The donated equipment is designed to strengthen lifesaving services across health facilities. It includes newborn warmers to help prevent hypothermia among newborns, ORT Corner equipment for the management of childhood diarrheal diseases, cooking demonstration kits to promote improved nutrition practices, and milk preparation equipment for Stabilization Centers treating severely malnourished children.

These essential supplies will enable healthcare providers to deliver safer, higher-quality, and more effective services while improving health outcomes for mothers and children.
• Expanding Access to Quality Care
The MIHR Project has already been supporting 38 health centers and two hospitals across five districts in South Wollo. With the recent inclusion of Wereilu District, the project has expanded its reach to six districts, allowing more communities to benefit from improved healthcare services.
Beyond supplying equipment, the project also strengthens the capacity of health workers through training and mentorship, ensuring that the equipment is effectively utilized to provide quality care.
• Building Resilient Health Facilities
Resilient health systems are essential for responding to routine healthcare needs as well as emergencies and disease outbreaks. By filling critical equipment gaps, the MIHR Project is helping health facilities become better prepared to provide uninterrupted, high-quality services under all circumstances.
This support reflects the project's commitment to strengthening Ethiopia's health system and ensuring that health facilities have the resources needed to save lives and deliver quality care.

በካናዳ ካልገሪ ከተማ የመጽሐፍ ፊርማና የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ-ግብር ሊካሄድ ነውካልገሪ፣ ካናዳ —የጤና ልማትና የፀረ-ወባ ማኅበር መሥራችና ዋና ዳይሬክተር የሆኑት የክብር ዶ/ር አበረ ምሕረ...
15/07/2026

በካናዳ ካልገሪ ከተማ የመጽሐፍ ፊርማና የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ-ግብር ሊካሄድ ነው
ካልገሪ፣ ካናዳ —
የጤና ልማትና የፀረ-ወባ ማኅበር መሥራችና ዋና ዳይሬክተር የሆኑት የክብር ዶ/ር አበረ ምሕረቴ፣ በመጪው ነሐሴ ወር 2026 በካናዳ ካልገሪ ከተማ ታላቅ የመጽሐፍ ፊርማ፣ የውይይትና የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ-ግብር እንደሚያካሂዱ ተነገረ።
እንደ ዝግጅቱ አስተባባሪዎች ገለጻ፣ መርሃ-ግብሩ እ.ኤ.አ. ነሀሴ 8 ቀን 2026 ከቀኑ 7:00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 12:00 ሰዓት (1:00 PM – 6:00 PM) በካልገሪ በሚገኘው (Varsity Community Association) አዳራሽ ይካሄዳል።
ይህ መድረክ በካናዳና አካባቢዋ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የማኅበሩን መስራችና ዋና ዳይሬክተር በአካል አግኝተው ለመወያየት፣ለመመካከርና የበጎ አድራጎት ሥራዎችን ለመደገፍ ትልቅ ዕድል የሚፈጥር መሆኑ ተገልጿል።
የጤና ልማትና የፀረ-ወባ ማኅበር ከተመሠረተበት ከ1990 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ በርካታ አገራዊ የበጎ አድራጎት ሥራዎችን ሲያከናውን የቆየ አንጋፋ ማኅበር ነው። በዚህ ልዩ መርሃ-ግብር ላይ ከሚሸጡት መጻሕፍት የሚገኘው አብዛኛው ገቢ በቀጥታ የማኅበሩን የሰብዓዊ ርዳታ ሥራዎች ለመደገፍ የሚውል መሆኑ ታውቋል።
ማኅበሩ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ውስጥ ትኩረት ሰጥቶ ከሚንቀሳቀስባቸው ዋና ዋና ዘርፎች መካከል፦
• ወባንና ሌሎች ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን መከላከልና መቆጣጠር፣
• የፀጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች አስፈላጊ የሆኑ ሕይወት አድን የመደኃኒት ግብዓቶችን ማጓጓዝ
• የውሃ ጉድጓዶች ቁፋሮ፣ የምንጮች ማጎልበትና የውኃ እጥረት ባለባቸው አካባቢዎች ንጹሕ ውኃ ተደራሽ ማድረግ፣
• የሴት ተማሪዎች በትምህርታቸው እንዲገፉና ከትምህርት ገበታቸው እንዳይቀሩ የቁሳቁስና የገንዘብ ድጋፍ ማድረግ፣ እንዲሁም
• ትምባሆ በዜጎች ጤና ላይ እያደረሰ ስላለው ጉዳት የማኅበረሰቡን ግንዛቤ ማሳደግና ዜጎችን ከሲጋራ ሱስ መጠበቅ የሚሉ ይገኙበታል።
የዝግጅቱ አስተባባሪዎች ባስተላለፉት መልዕክት፤ "በዚህ መርሃ-ግብር ላይ የሚደረገው ተሳትፎና የመጽሐፍ ግዢ፣ በኢትዮጵያ ለሚገኙ ወገኖቻችን ለመደገፍ በሚደረገው ጉዞ በቀጥታ የሚደግፍ በመሆኑ በካልገሪና አካባቢዋ የምትገኙ ወገኖቻችን በዕለቱ በክብር ተገኝታችሁ የበኩላችሁን አሻራ እንድታሳርፉ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን" ብለዋል።
የዝግጅቱ አድራሻ፦ Varsity Community Association, 4303 Varsity Drive, NW, Calgary.

የጤና ልማትና ፀረ-ወባ ማኅበር በተንቀሳቃሽ ሠራተኞች ላይ ያተኮረ የወባ መከላከል፣ ምርመራና ሕክምና ሥራዎችን እያከናወነ ነው::የጤና ልማትና ፀረ-ወባ ማኅበር "ሰናይ" በተሰኘው ፕሮጀክቱ አ...
06/07/2026

የጤና ልማትና ፀረ-ወባ ማኅበር በተንቀሳቃሽ ሠራተኞች ላይ ያተኮረ የወባ መከላከል፣ ምርመራና ሕክምና ሥራዎችን እያከናወነ ነው::

የጤና ልማትና ፀረ-ወባ ማኅበር "ሰናይ" በተሰኘው ፕሮጀክቱ አማካኝነት በአማራ ክልል በ5 ወረዳዎች በሚገኙ ሰፋፊ እርሻዎች እና የልማት ቀጠናዎች ላይ ትኩረት አድርጎ እየሠራ ይገኛል። ማኅበሩ በእነዚህ አካባቢዎች ለሚገኙና ለበሽታው ይበልጥ ተጋላጭ ለሆኑ ጊዜያዊና ተንቀሳቃሽ ሠራተኞች አጠቃላይ የወባ መከላከል ተግባራትን፣ የምርመራና የሕክምና አገልግሎቶችን ተደራሽ በማድረግ ላይ ነው።
በአሁኑ ወቅትም በምዕራብ ጎጃም ዞን ጃቢጠህናን ወረዳ በሚገኘው ላይበር እርሻ ልማት ውስጥ፦
📌 የወባ ትንኝ መራቢያ ቦታ የቁጥጥር ሥራዎች በስፋት እየተሰሩ ነው፤
🩸 ፈጣን የወባ ምርመራና የሕክምና አገልግሎት እየተሰጠ ይገኛል።
#ጃቢጠህናን

ጤና ልማትና ፀረ-ወባ ማኅበር ከ627 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የሕይወት አድን መድኃኒቶችን ማጓጓዙን ገለጸ፤ባሕር ዳር – የጤና ልማትና ፀረ-ወባ ማኅበር በአሜሪካ መንግሥት ድጋፍ በሚትገበ...
29/06/2026

ጤና ልማትና ፀረ-ወባ ማኅበር ከ627 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የሕይወት አድን መድኃኒቶችን ማጓጓዙን ገለጸ፤

ባሕር ዳር – የጤና ልማትና ፀረ-ወባ ማኅበር በአሜሪካ መንግሥት ድጋፍ በሚትገበረው Supply Chain Strengthening (SCS) ፕሮጀክት አማካኝነት ለባህርዳር እና ጎንደር የመድኃኒት ማከማቻ ማዕከላት ከ627 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ የሕይወት አድን መድኃኒቶችን ማጓጓዙን አስታወቀ።

በዚህ ሳምንት አስፈላጊ እና የሕይወት አድን መድኃኒቶችን የጫኑ 8 ተሽከርካሪዎች በባሕር ዳር እና ጎንደር የክልል ማዕከላት በተሳካ ሁኔታ ደርሰዋል። ለተጠቃሚዎች የተከፋፈለው የሕክምና ግብዓት ጠቅላላ ዋጋም 627,149,169.38 ብር መሆኑ ተገልጿል።

ይህ የማጓጓዝ ስራ ግጭት በተከሰተባቸው አካባቢዎች የሚገኙ ወገኖችን የጤና አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ ያለመ ሲሆን፤ የሕክምና አቅርቦት በማጠናከር፣ በተለይም በችግር ጊዜ የሚከሰተውን የመድኃኒት እጥረት ለመቅረፍ እና የጤና ተቋማት አገልግሎት እንዳይቋረጥ ለማድረግ እያከናወነ ያለው ይህ ስራ ወሳኝ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ ተጠቁሟል።

Address

Yeka Sub-city, Woreda-6, Located On The Right Bend Of Megenagna Road, Situated Between Women's Square And Adwa Bridge
Addis Ababa

Opening Hours

Monday 08:00 - 17:00
Tuesday 08:00 - 17:00
Wednesday 08:00 - 17:00
Thursday 08:00 - 17:00
Friday 08:00 - 17:00

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Health, Development and Anti-Malaria Association - HDAMA posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Health, Development and Anti-Malaria Association - HDAMA:

Shortcuts

Share