Christ Embassy Ethiopia ZONE

Christ Embassy Ethiopia  ZONE Christ Embassy Ethiopia Zone Zonal HQ @ Kenenisa Road, AJ Car Inspection by Shola Market, Addis Ababa

የተወደዳችሁ ወንድሞችና እህቶችበጌታ በኢየሱስ ስም ሰላም ለእናንተ ይሁንለፈውስ ዥረት የቀጥታ ስርጭት የፈውስ ፕሮግራም ከፓስተር ክሪስ ጋር ደርሷልለመመዝገብ ይህንን ሊንክ ይጠቀሙhttps://...
20/02/2026

የተወደዳችሁ ወንድሞችና እህቶች

በጌታ በኢየሱስ ስም ሰላም ለእናንተ ይሁን

ለፈውስ ዥረት የቀጥታ ስርጭት የፈውስ ፕሮግራም ከፓስተር ክሪስ ጋር ደርሷል

ለመመዝገብ ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ

https://healingstreams.tv/zone/EWCAZ1

በኦንላይን የፈውስ ማዕከል ለመፍጠር ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ
https://healingstreams.tv/virtualz/EWCAZ1

አካላዊ የፈውስ ዥረት ማዕከል ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ
https://healingstreams.tv/vc/EWCAZ1

ለፈውስ ዥረት ፕሮግራም ለመጸለይ ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ
https://prayerclouds.org/app/ceethiopia

ቤተሰቦቻችሁን፣ ጓደኞቻችሁን፣ የስራ ባልደረቦቻችሁን መመዝገባችሁን እርግጠኛ ሁኑ!

ከፕሮግራሙ ጋር አብሮ ሰራተኛ ለመሆን ይህንን አካውንት ይጠቀሙ ደረሰኙንም ይላኩልን

1000466668207
ብሊቨርስ ላቭወርልድ ፓርትነርሺፕ
ንግድ ባንክ

እግዚአብሔር አብዝቶ ይባርካችሁ!

07/12/2025

RHAPSODY OF REALITIES
(Amharic )

Sunday _ December 7th_2025
(እሁድ _ ህዳር 28— 2018)

የነፍስ ዋጋ
📖 ════════
“ሰው ዓለምን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱንም ቢያጐድል ምን ይጠቅመዋል?” (ማርቆስ 8፥36)።
ፓስተር ክሪስ
📖 ═══════
ለእግዚአብሔር፣ አንዲት ነፍስ በዓለም ካሉት ባለጠግነት፣ ሀብቶች እና ኃይላት ሁሉ ትበልጣለች። ይህ እጅግ የሚያስደንቅ እውነት ነው፣ ሆኖም ግን በመንግሥቱ ውስጥ ዋጋ ያለው እውነታ ነው። ከሰው ነፍስ ዋጋ ጋር የሚወዳደር ምንም ነገር የለም። መጽሐፍ ቅዱስ በ (ዮሐንስ 3፥16) ላይ እንዲህ ሲናገር፡- “በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።” ይላል።

ጌታ ኢየሱስ ለዓለም ሥርዓቶች፣ ሕንፃዎች እና ተክሎች አልሞተም፤ እርሱ የሞተው ለሰዎች ነበር። የምታገኙት እያንዳንዱ ነፍስ የዘላለም ዋጋ አለው። ያለፈው ታሪኩ ወይም ባሕርይው ምንም ይሁን ምን፣ እያንዳንዱ ሰው፣ ለእግዚአብሔር እጅግ በጣም አስፈላጊ ዋጋ አለው። ዋጋቸው የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ነው፦ “ከአባቶቻችሁ ከወረሳችሁት ከከንቱ ኑሮአችሁ በሚያልፍ ነገር በብር ወይም በወርቅ ሳይሆን፥ ነውርና እድፍ እንደ ሌለው እንደ በግ ደም በክቡር የክርስቶስ ደም እንደ ተዋጃችሁ ታውቃላችሁ።” (1ኛ ጴጥሮስ 1፥18-19)።

የነፍስን ዋጋ በእውነት ስትረዱ፣ ወንጌላዊነት ከሕጋዊነት በላይ ይሆናል፤ የፍቅር ተልዕኮ ይሆናል። በጠፉት ላይ ታለቅሳላችሁ። ለእነርሱ ትጸልያላችሁ። እነርሱን ለመድረስ ከምቾት ቀጠናችሁ ትወጣላችሁ። ሰይጣን ሰዎች ዘላለማዊነትን ይረሱ ዘንድ ትኩረታቸውን በዝና፣ በሀብትና በደስታ እንዲያጡ ይፈልጋል። ነገር ግን የእግዚአብሔር ልጅ እንደመሆናችሁ መጠን፣ ከወጫዊው ገጽታ ባሻገር ማየት አለባችሁ። እያንዳንዱን ነፍስ መልሶ ለማግኘት እንዲሚጠበቅ ውድ ሀብት አድርጋችሁ ተመልከቱ።

የነፍስን ዋጋ ይበልጥ እንድናውቅ፣ መጽሐፍ ቅዱስ በ (ሉቃስ 15፥7) ላይ፦ “…ንስሐ ከማያስፈልጋቸው ከዘጠና ዘጠኝ ጻድቃን ይልቅ ንስሐ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በሰማይ ደስታ ይሆናል።” ይላል። አስቡት፦ ሰማይ ሁሉ ንስሐ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ ደስ የሚል ከሆነ፣ ደጋግመን ሲከሰት ለማየት እኛ ምን ያህል መትጋት አለብን። ስለዚህ፣ ነፍስ ማዳን ልማዳችሁ እና የአኗኗር ዘይቤያችሁ ይሁን። ዕጣ ፈንታዎችን እና ፍጻሜዎችን ታደጉ። የሰዎችን ነፍስ ከጨለማ ወደ ብርሃን፣ ከሰይጣን ኃይል ወደ እግዚአብሔር አድኑ። ከዚህ የበለጠ የሚያረካ ምንም ነገር የለም።

ጸሎት
📖 ═══════
የሰማይ አባት ሆይ፣ አንተ ሰዎችን በምታይበት መንገድ እኔም እንዳይ ዓይኖቼን ስለከፈትክ አመሰግንሃለሁ። የነፍስን እውነተኛ ዋጋ እንዳደንቅ እና እንድንገነዘብ ስለረዳኸኝ አመሰግንሃለሁ፤ ይህ ደግሞ በጠፉት ላይ ልቤን በርህራሄ እንዲቃጠል ያደርጋል፣ ወንጌልን በጋለ ስሜት በምሰብክበት ጊዜ፣ ከጨለማ ግዛት ወደሚደነቅ ብርሃንህ አድናቸዋለሁ፣ በኢየሱስ ስም አሜን።

ለተጨማሪ ጥናት
ሉቃስ 15፡7
ዮሐንስ 3፡16-17
ያዕቆብ 5:20

02/11/2025

Address

Christ Embassy
Addis Ababa
1000

Telephone

+251911067343

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Christ Embassy Ethiopia ZONE posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Christ Embassy Ethiopia ZONE:

Share