የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር /ኢመማ/ Ethiopian Teachers Association /EI/

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር /ኢመማ/ Ethiopian Teachers Association /EI/

የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር /ኢመማ/ Ethiopian Teachers Association /EI/ BETTER EDUCATION FOR BETTER WORLD!

03/11/2025

የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በወቅታዊ ፕሮግራሙ የብሄራዊ ጥቅሞቻችንን እንዴት እናስጠብቅ? በሚል ርዕስ ስር ወቅታዊ በሆነው የባህር በር አጀንዳ የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ሊቀ_መንበር ዶ/ር ዮሀንስ በንቲ ጋር ውይይት አካሂዷል።

ጥቅምት 20/2018 የትምህርት ጥራትን ለማሻሻልና ትውልድን ለማነጽ ተግባራዊ የተደረጉ ፕሮጀክቶች በዘርፉ ስኬት እንዲመዘገብ እያደረጉ መሆኑን የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ገለፀ።በጠቅላይ ሚኒ...
30/10/2025

ጥቅምት 20/2018
የትምህርት ጥራትን ለማሻሻልና ትውልድን ለማነጽ ተግባራዊ የተደረጉ ፕሮጀክቶች በዘርፉ ስኬት እንዲመዘገብ እያደረጉ መሆኑን የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ገለፀ።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተግባራዊ የተደረገው የትምህርት ለትውልድ ፕሮጀክት የትምህርት ጥራትን ለማምጣት የሚደረገውን ጥረት በስፋት እያገዘ መሆኑንም ተጠቁሟል፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከትናንት በስቲያ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ መንግስትና ሕዝብ በመተባበር ተግባራዊ ያደረጉት የትምህርት ለትውልድ ፕሮጀክት ስኬታማ ስራዎችን ለማከናወነ አስችሏል ብለዋል።

የፕሮጀክቱ አንዱ ዓላማ የትምህርት ጥራትን ማስጠበቅ መሆኑን አመልክተው፤ ከታችኛው የትምህርት እርከን ጀምሮ ትውልድን የሚገነቡና የሚያንጹ ስራዎች መሰራታቸውን ጠቅሰዋል።

በተጨማሪም ለመምህራን የተለያዩ ስልጠናዎችን በመስጠት የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች በትምህርትና በፈተና አሰጣጥ ስርዓት ላይም ለውጥ ማስመዝገብ አስችሏል ነው ያሉት።

የተማሪዎች ምገባን በተመለከተም አስደናቂና ማሕበረሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ስራዎች መስራታቸውንም ነው ለምክር ቤቱ የገለጹት።

የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ፕሬዚዳንት ዮሐንስ በንቲ(ዶ/ር ) ለኢዜአ እንዳሉት፤ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የትምህርት ጥራትን ለማምጣት የተከናወኑ ተግባራት ውጤት የተገኘባቸው ናቸው።

በዋናነት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ኢንሼቲቭ ተግባራዊ የተደረገው የትምህርት ለትውልድ ፕሮጀክት በዘርፉ የሚታይ ለውጥ እያመጣ መሆኑን ገልፀዋል።

የአንደኛ ደረጃ ትምህርትን በማዳረስና በትምህርት ቤቶች ተግባራዊ የተደረገው የምገባ መርሃ ግብር ስኬት ከተመዘገበባቸው ዘርፎች መካከል ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል።

እስካሁን ባለው ሒደት ፕሮጀክቱ ውጤታማ ነው ያሉት ፕሬዚዳንቱ፤ ካሉት የትምህርት ተቋማት ብዛት አኳያ ፕሮጀክቱ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ነው ያሉት።

ይህም ትውልዱን ለመገንባትና የትምህርት ዘርፉን በሚፈለገው ደረጃ መቀየር የሚያስችል መሆኑንም አመላክተዋል።

የኢመማ 23ኛ ጠቅላላ ጉባኤ በአዲስ አበባ እና በአዳማ ከተሞች ተካሔደ የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር  23ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የመክፈቻው ሥነ_ሥርዓት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአድ...
18/10/2025

የኢመማ 23ኛ ጠቅላላ ጉባኤ በአዲስ አበባ እና በአዳማ ከተሞች ተካሔደ

የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር 23ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የመክፈቻው ሥነ_ሥርዓት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአድዋ መታሰቢያ ሙዚያም ተካሂዷል፡፡ በዚህ ዕለት የተለያዩ እህት ማህበራት ተገኝተው የአጋርነት መልዕከት ያስተላለፉ ሲሆን ዶ/ር ዴኒስ ሲኞሎ የትምህርት ዓለም አቀፍ አፍሪካ አህጉር ዳይሬክተር ተገኝተው መልዕክት ከማስተላለፋቸውም በላይ ከጉባኤ አባላት ጋር በመሆን "Go public Fund Education" ዘመቻን መርተዋል፡፡

ጉባኤውን የትምህር ሚንስትር ተወካይ ዶ/ር ሰለሞን አብርሃም በንግግር ከፍተውታል፡፡ እውቅናዎችም ለማህበሩና ለመምህራን የጎላ ድጋፍና አስተዋጽኦ ላደረጉ ድርጅቶችና ግለሰቦች ተሰጥቷል፡፡

የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት፣ ፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን፣ ኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ፣ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ፣ አሀዱ ሬድዮ ፣ ቬሎሲቲ ትራንስፖርት(ፕ.አል.ሲ)፣ ፐብሊክ ትራንስፖርት እንዲሁም በአፈጻጸማቸው የኦሮሚያ ክልል መምህራን ማህበር፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መምህራን ማህበር እና የማዕከላዊ ኢት/ክልል መምህራን ማህበር ዕውቅና ያገኙ ሲሆን በችግር ወቅት አባሎቻቸውን ላገለገሉ ለአማራ፣ ለትግራይና ለቤኒሻንጉል-ጉሙዝ ክልሎች እውቅና ተሰጥቷል፡፡

በግለሰብ ደረጃ አምባሳደር ዶ/ር ገነት ዘውዴ፣ አምባሳደር ዶ/ር ሽፈራው ሽጉጤ ፣ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና ማህበሩን ሲያገለግሉ ቆይተው በሌላ ለተተኩ የቀድሞ ክልል ማህበራት ፕሬዝደንቶች እንዲሁም ማህበሩን ለረጅም ዓመታት በትጋት ሲያገለግሉ ለነበሩት መ/ርት ደስታዬ ታደሰ የእውቅናው አካል ነበሩ፡፡ ከመክፈቻ ሥነስርዓት በኋላ የአፊሪካ ኮንቬንሽን ሴንተርን ጨምሮ በአዲስ አበባ በአራዳ፣ ለሚ ኩራና አቃቂ ቃልቲ ክፍለ ከተሞች የተለያዩ የልማት ሥራዎች ጉብኝት ተደርጓል፡፡

ጉባኤው ከጥቅምት 5-6/2018 ዓ/ም በአዳማ ከተማ በአባ ገዳ እኮኖሚ ዞን በሚገኘው የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ አዳራሽ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ የመከረ ሲሆን በተለይ በትምህርት ጥራት ፣ መብትና ጥቅም፣ የመምህርነት ሙያ ተመራጭ አለመሆን ፣ ሰላም እና ሀገራዊ ጉዳዮች ፧ የተማሪዎች ወደ ት/ቤት መምጣት አለመቻል በተለይ በአማራ ክልል ያለው ሁኔታ ላይ ሲመክር ቆይቶ በሀገር ደረጃ ለቀጣይ ዓመታት ማህበሩን የሚመሩ ሥራ አስፈጻሚ እና የኦዲት ኮሚቴ አባላትን መርጧል፡፡

ተመራጮቹም
ዶ/ር ዮሐንስ በንቲ ፕሬዚዳንት ከኦሮሚያ፤
አቶ ሽመልስ አበበ ም/ፕሬዚዳንት ከአማራ፤
አቶ ጥላሁን ታረቀኝ ዋና ፀሐፊ ከትግራይ፤
ወ/ሮ መስታወት በላቸው ም/ዋና ፀሐፊና ስርዓተ ፆታ ኃላፊ ከኦሮሚያ ፤ ኢንስትራክተር ታረቀኝ ኃይሌ ትምህርት ስልጠናና ምርምር ኃላፊ ከደቡብ ኢትዮጵያ፤ ዶ/ር በፈቃዱ ዘለቀ የከፍተኛ ትምህርት ተወካይ ከኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች (አዲስ አበባ ዩኒ.) ፤ ወ/ሮ ደብሪቱ ጌታቸው የኦዲት ኮሚቴ ሰብሳቢ ከድሬዳዋ፤ ወ/ሮ ገነት ከበደ የኦዲት ኮሚቴ አባል ከደቡብ ምዕ/ኢትዮጵያ፤ አቶ ታከለ ኸመቻ ከሲዳማ ክልል የኦዲት ኮሚቴ አባል ሆነው ከተመረጡ በኋላ ባለ 12 ነጥብ የአቋም መግለጫ ወጥቶ ጉባኤው በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል፡፡

18/10/2025
የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር የሴት አመራሮች ኮከስ 5ኛ ምክክር መድረክ ተካሄደ። በኢትዮጵያ መምህራን ማህበር የሴት አመራሮች ኮከስ 5ኛ የምክክር መድረክ ጥቅምት 3/2018 ዓ.ም በአዳማ ከተ...
18/10/2025

የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር የሴት አመራሮች ኮከስ 5ኛ ምክክር መድረክ ተካሄደ።

በኢትዮጵያ መምህራን ማህበር የሴት አመራሮች ኮከስ 5ኛ የምክክር መድረክ ጥቅምት 3/2018 ዓ.ም በአዳማ ከተማ ሳፋሪ ሎጅ የሁሉም ክልልና ሁለቱ ከተማ አስተዳደር እንዲሁም የኢትዮጵያ ዩንቨርስቲ መምህራን ማህበር ፕሬዚዳንቶች፣ በየደረጃው ከሚገኘው የማህበራችን ሴት አመራሮች፣ የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ ተካሂዷል።

በዕለቱ የሀገር አቀፉ ኮከስ አመቻቾች የአራት ዓመት የስራ እንቅስቃሴ ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
መድረኩ ልምድ የሚቀሰምበት በመሆኑ ሁለት አንጋፋ ሴት አመራሮች የተከበሩ አምባሳደር ጊፍቲ አባስያና የተከበሩ ወ/ሮ አበበች ነጋሽ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አማካሪ ሁለቱም ከተማሪነት ህይወት አስከ ከፍተኛ አመራርነት እንዴት እንደ ደረሱ የሥራና የህይወት ተሞክሯቸውን አካፍለዋል።

በመጨረሻም ለኢመማ ኮከስ መስራች፣ የኢመማ ምክትል ዋና ፀሀፊና ስርዓተ ጾታ ተጠሪ መምህርት ደስታዬ ታደሰ ማህበሩን ለረጅም ዓመታት በማገልገላቸው እውቅና በመስጠት ለቀጣይ ዓመታት የማህበረን ሴት መምህራንን በአመቻችነት የሚያገለግሉ አመራሮችን በመምረጥ መድረኩ ተጠናቋል።

የኢትዮጵያ  መምህራን ማህበር 38ኛ መደበኛ ምክር ቤት ተካሔደ  የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር 38ኛ ዓመታዊ ምክር ቤት ስብሰባውን ከመስከረም 29/2018 ዓ/ም  እስከ ጥቅምት 1/2018 ዓ/...
17/10/2025

የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር 38ኛ መደበኛ ምክር ቤት ተካሔደ

የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር 38ኛ ዓመታዊ ምክር ቤት ስብሰባውን ከመስከረም 29/2018 ዓ/ም እስከ ጥቅምት 1/2018 ዓ/ም በአዳማ ከተማ በከተማ አስተዳደሩ መሰብሰቢያ አዳራሽ ከሁሉም ክልሎች፣ ከተማ መስተዳድሮች ፣ የኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲዎች መምህራን ማህበር፣ ከትምህርት ኮሌጅና ቴክኒክና ሙያ የተወከሉ የምክር ቤት አባላት በተገኙበት ተካሂዷል፡፡

ከምክር ቤት አባላት የሚነሱ ጉዳዮችን ለመከታተል እና ለመንግስት ለማድረስ ያመች ዘንድ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባል የተከበሩ አቶ ታደሰ ጌጡ የተገኙ ሲሆን የተከበሩ ዶ/ር ቶላ በሪሶ የኦሮሚያ ብ/ክ/መንግስት ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ምክር ቤቱን በንግግር ከፍተዋል፡፡

በም/ቤቱ መክፈቻ እለት በተደራራቢ ተልእኮዎች መገኘት ያልቻሉት በኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ እና በአጠቃላይ ትምህርት የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ሙሉቀን ንጋቱ እንዲሁም በዚሁ ዘርፍ ዳሬክተሯ ወ/ሮ አሰገደች ምሬሳ የተገኙ ሲሆን ሚኒስቴር ዲኤታዋ ለም/ቤት አባላት መልዕክት አስተላልፈዋል።

ስለመምህራን መብትና ጥቅማ ጥቅሞች፣ የመልካም አስተዳደር ችግሮች፣ የትምህርት ጥራት፣ ሀገራዊ ጉዳዮችና በመምህርነት ሙያ ዙሪያ ከም/ቤት አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች እንደ ሀገር አቅጣጫ ተይዞ እየተሰራ ስላለው ሥራ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

ዶ/ር ሙሉቀን ንጋቱና ወ/ሮ አሰገደች ምሬሳም በቴክኒካል ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተጋበዙ የቋሚ ኮሚቴ አባልም አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡

በመጨረሻም ምክር ቤቱ ለ3 ቀን በተለያዩ ሙያዊ መብትና ጥቅም እንዲሁም ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ መክሮ በሰላም ተጠናቋል፡፡

የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ከአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር ከመስከረም 26-27/2018 ዓ.ም ድረስ "Together for Teachers, Together for Tomor...
07/10/2025

የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ከአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር ከመስከረም 26-27/2018 ዓ.ም ድረስ "Together for Teachers, Together for Tomorrow" በሚል አለማቀፍ መሪ ቃል ያካሄደውን የአለም መምህራን ቀን የአመቱን ምርጥ መምህርት እውቀናና ሽልማት በመስጠት አጠናቀቀ ።

በመርሀ_ግበሩ መጀመሪያ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ፕሬዝዳንትና የትምህርት አለማቀፍ የስራ አስፈፃሚ ቦርድ አባል ዶ/ር ዮሐንስ በንቲ ለመላው መምህራን በተለይም ባልተመቻቸ ሁኔታ ውስጥ ሆነው ከራሳቸው ይልቅ ለትውልድ ቅድሚያ በመስጠት በዚህ ድንቅ ሙያ ላይ ለተሰማሩ መምህራን እንኳን አደረሳችሁ ካሉ በኋላ ማህበሩ የመምህራንን መብትና ጥቅም ለማስጠበቅ ብሎም የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ አበክሮ እየሰራ እንደሆነ አፅንኦት ሰጥተው መልዕክት አስተላልፈዋል።

በበአሉ ላይ ትምህርት ሚኒስቴርን ወክለው የተገኙትና የሚኒስቴሩ የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ልማት መሪ ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ሙሉቀን ንጋቱ መርሀ_ግብሩን ሲከፍቱ ባስተላለፉት መልዕክት መንግስት የመምህራንን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል እና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት ጥረት እያደረገ መሆኑን ጠቅሰው መንግስት ለመንግሥት ሰራተኞች ያደረገው የደሞዝ ማሻሻያ አንዱ ማሳያ ነው ካሉ በኋላ ባጠቃላይ መምህራንና የትምህርት ማህበረሰቡን ችግሮች መቅረፍ የሚያስችል ማዕቀፍ ከኢመማና ሌልች ባለድርሻ አካላት ጋር አዘጋጅቶና ለፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ተልኮ ዉሳኔውን እየተጠባበቁ መሆኑን ገልፀዋል ።

የአዳማ ሳይንስና ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ለሚ ጉታ ዩኒቨርስቲው ይሄንን የአለም መምህራን ቀንን በማስተናገዱ የተሰማቸውን ደስታ ገልፀው ተቋሙ እያካሄደ ያለውን የመማር ማስተማርና የምርምር ስራዎች ለታዳሚያን ገለፃ አድርገዋል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ዩኔስኮ ፅ/ቤት ዋና ፀሀፊ አቶ አለሙ ጌታሁንም የአለም መምህራን ቀን መልዕክት አስተላልፈው የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር እየሰራ ያለውን ዘርፈ ብዙ ችግር አድንቀው ዩኔስኮ ከማህበሩ ጋር ያለውን መልካም ግንኙነት አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል ።

በመርሀ ግብሩ ላይ ለዕለቱ የሚመጥኑ አምስት የምርምር ስራዎች በዩኒቨርስቲ ምሁራን ቀርበው ዉይይትና ክርክር የተካሄደ ሲሆን በመጨረሻም ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን አርባምንጭ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተገኙትን የፊዚክስ መምህርት ቀለሟ ተፈራን ባሳዩት ከፍተኛ አፈፃፀምና ለሰሯቸው ማህበረሰብ ተኮር ችግር ፈቺ ስራዎች በ2017 ዓ.ም አፈፃፀም የ2018 ዓ.ም የአመቱ ምርጥ መምህርት ብሎ በመሰየም የዕውቅና ሰርተፍኬትና ሽልማት አበርክቶላቸዋል ።

በመርሀ_ግብሩ ላይ የኢመማ ስራአስፈፃሚ ኮሚቴ፣ የሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች መምህራን ማህበራት ፕሬዝዳንቶች፣ የተለያዩ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የመምህራን ማህበር አመራሮች ፣ የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ መምህራን ማህበር አመራሮችና መምህራን እንዲሁም ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

በመጨረሻም የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ለመርሀ_ግብሩ መሳካት አስተዋጽኦ ላደረጉ ሁሉ በተለይም በአሉን የመስተንግዶ ወጪዎችን በመሸፈንና በማስተናገድ ሚናውን ለተወጣው ለአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ማኔጅመንት፣ መርሀ_ግብሩን ላስተባበረው የዩኒቨርስቲው መምህራን ማህበር እና ለኢመማ ስራ አስፈፃሚዎች ምስጋናውን ያቀርባል ።

Together for Teachers
Together for Tomorrow !!

ለመላው መምህራን እና የትምህርት ማህበረሰብ በሙሉ በየአመቱ October 5 ለሚከበረው የአለማቀፍ መምህራን ቀን እንኳን አደረሳችሁ እያለ የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ከአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎ...
05/10/2025

ለመላው መምህራን እና የትምህርት ማህበረሰብ በሙሉ
በየአመቱ October 5 ለሚከበረው የአለማቀፍ መምህራን ቀን እንኳን አደረሳችሁ እያለ የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ከአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ እና ከዩኒቨርስቲው መምህራን ማህበር ጋር በመተባበር በአሉን መስከረም 26-27/2018 ዓ.ም በጥናትና ምርምር ኮንፈረንስ የሚያከብር ሲሆን ለአመቱ ምርጥ መምህር /ርት ወይም አሰልጣኝ ዕውቅና ይሰጣል ።

26/09/2025
በሰላሌ ዩኒቨርሲቲ የመምህራን ማህበር ጠቅላላ ጉባኤ ተካሄደ ***የሰላሌ ዩኒቨርሲቲ መምህራን ማህበር ፕሬዝዳንት መምህር ሲሳይ በቀለ  በጠቅላላ ጉባኤ  ፕሮግራሙ ላይ የማህበሩን የስራ አፈጻጸ...
26/09/2025

በሰላሌ ዩኒቨርሲቲ የመምህራን ማህበር ጠቅላላ ጉባኤ ተካሄደ
***
የሰላሌ ዩኒቨርሲቲ መምህራን ማህበር ፕሬዝዳንት መምህር ሲሳይ በቀለ በጠቅላላ ጉባኤ ፕሮግራሙ ላይ የማህበሩን የስራ አፈጻጸም ሪፖርት በማቅረብ በጉባኤው ተሳታፊዎች ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል።

በጠቅላላ ጉባኤው መርሃ ግብር ላይ የሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ፈዬራ ዲንሳ፣ የአካዳሚክና ምርምር ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ፀጋዬ ደዩ፣ የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ቶሎሳ ዳዲ በመድረኩ ላይ በመገኘት ተሳታፊዎቹን አወያይቷል::

የሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ፈዬራ ዲንሳ በፕሮግራሙ መዝጊያ መርሃ ግብር ላይ በመገኘት ባደረጉት ንግግር መምህራን በምርምርና ጥናት እንዲሁም በማህበረሰብ አገልግሎት ዘርፍ የመማር ማስተማር ስራ ከመስራት በላይ የዩኒቨርሲቲያችንን ተልዕኮና ራዕይ ለማሳካት የላቀ ሚና እንዳላቸው ተናግረዋል።

በተጨማሪም የመምህራን ማህበር የራሱ ህግና ደንብ ያለው ሲሆን የመምህራንን ጥቅምና መብት በማስከበር ዘርፍ ትልቅ ሚና እንደሚጫወት፣ እንዲሁም የመምህራን ማህበሩ በመማር ማስተማሩ ዘርፍ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ እያከናወነ ያለው ተግባር ሊበረታታና ሊቀጥል ይገባል በማለት ዶ/ር ፈዬራ ተናግረዋል።

በመጨረሻም በጠቅላላ ጉባኤ ፕሮግራም መርሃ ግብር ላይ የዩኒቨርሲቲው መምህራን ማህበር የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴዎች ተመርጠው የቀጣይ የስራ አቅጣጫም ተቀምጧል።

26/09/2025

Dambi Dollo University Launches Teachers’ Association

In a significant move to enhance academic quality and safeguard the professional interests and rights of its academic staff, Dambi Dollo University has officially launched its Teachers’ Association on the 25th of September 2025.

The inauguration ceremony was held on campus and attended by university officials, deans, and faculty representatives. The event marks a major milestone in organizing the university’s educators into a unified body dedicated to advancing their collective interests and supporting institutional development.

Dr. Reda Nemo, Vice President for Academic Research, Technology Transfer, and Community Service, delivered the opening remarks. In his speech, he emphasized that the establishment of the Dambi Dollo University Teachers’ Association represents a shared commitment to improving the quality of education, increasing research productivity, and achieving the university’s broader academic mission.

The event also featured remarks from Dr. Dembelash Mengistu, Vice President of the Teachers’ Association of Ethiopian Universities. He provided insightful guidance on the purpose, structure, and importance of Teachers’ Associations within the Ethiopian higher education system.

After discussion and having debated on various issues,
the election process was conducted in a transparent and democratic manner, reflecting the association’s commitment to fairness, accountability, and inclusive representation.

The successful establishment of Dambi Dollo University Teachers’ Associatio sets a strong foundation for collaboration, academic excellence, and faculty empowerment at Dambi Dollo University.

እንኳን ለአዲሱ አመት አደረሳችሁ !!               ለመላው የኢትዮጵያ የመምህራን ማህበር አመራሮች እና አባሎቻችን ሁሉ  እንኳን ለ 2018 ዓ.ም አደረሳችሁ እያልን አዲሱን አመት አ...
10/09/2025

እንኳን ለአዲሱ አመት አደረሳችሁ !!

ለመላው የኢትዮጵያ የመምህራን ማህበር አመራሮች እና አባሎቻችን ሁሉ እንኳን ለ 2018 ዓ.ም አደረሳችሁ እያልን አዲሱን አመት አስመልክቶ የመልካም ምኞት መግለጫችንን አሼ ታለንት(ጋዜጠኛና የፀረ ሱስ አክቲቪስት አሸናፊ ግዛው) ከተባለው የሚድያ አጋራችን ጋር በመተባበር ዛሬ ጷጉሜን 5/2017 ዓ.ም ከቀኑ 10-12 ሰአት ድረስ ከፍተኛ አድማጭ ባለው በ FM ADDIS 97.1 ሬድዮ ልዩ የአውዳመት መርሀግብር ላይ ስለምናስተላልፍ እንድትከታተሉ እንጋብዛለን ።

Address

Addis Ababa
13205

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር /ኢመማ/ Ethiopian Teachers Association /EI/ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር /ኢመማ/ Ethiopian Teachers Association /EI/:

Share