Bole Youth Association

Bole Youth Association ይህ ገጽ የቦሌ ክ/ከተማ አዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር የመረጃ አማራጭ ነው።
የላቀ ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ለከተማችን ወጣት!!

“ወጣቶች ለሰላም መረጋገጥ የማይተካ ሚና አላቸው!” የቦሌ ክፍለ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት “ሀገር በቀል የሰላምና የመቻቻል እሴቶች ለትውልድ ግንባታ” በሚል መሪ ቃል ክፍለ ከተ...
08/11/2025

“ወጣቶች ለሰላም መረጋገጥ የማይተካ ሚና አላቸው!”

የቦሌ ክፍለ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት “ሀገር በቀል የሰላምና የመቻቻል እሴቶች ለትውልድ ግንባታ” በሚል መሪ ቃል ክፍለ ከተማ አቀፍ የወጣቶች ኮንፈረንስ አካሄደ፡፡

ጽ/ቤቱ ከአዲስ አበባ ወጣቶች ማኅበር ቦሌ ክ/ ከተማ ቅርንጫፍ ጋር በመተባበር ባዘጋጀው ኮንፈረንስ ላይ ከአሥራ አንዱም ወረዳዎች የተውጣጡ ወጣቶች የተሳተፉ ሲሆን የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ መርዕድ አስፋው የበርካታ ብሔር ብሔረሰቦች፣ ባሕሎች፣ እምነቶች እና ታሪኮች ባለቤት የሆነችው ኢትዮጵያ ወደላቀ ከፍታ እንድትጓዝ ሰላም ከፍ ያለ ሚና እንዳለው ተናግረዋል፡፡ ወጣቶች ለሀገር ግንባታ ግንባር ቀደም ተዋንያን ናቸው” ያሉት ኃላፊው፣ ወጣቱ ትውልድ ሀገር በቀል የሰላምና የመቻቻል እሴቶችን በአግባቡ ተረድቶ ሰላሟ የተረጋገጠች ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ በከፍተኛ የኃላፊነት መንፈስ መረባረብ እንዳለት አክለው አስገንዝበዋል፡፡

የአዲስ አበባ ወጣቶች ማኅበር ቦሌ ክ/ ከተማ ቅርንጫፍ ሰብሳቢ ወጣት ታምራት ሚሊዮን በበኩሉ ወጣቶች ሰላም፣ ልማት እ ዴሞክራሲ እንዲረጋገጥ በግንባር ቀደምነት በመሰለፍ ሚናቸውን ሲወጡ መቆየታቸውን አውስቶ፣ በሀገር በቀል የሰላምና የመቻቻል እሴቶች ዙሪያ ወጣቶች የጋራ መግባባት በመያዝ ጸረ ሰላም እንቅስቃሴዎችን ለማክሸፍ የዜግነት ግዴታቸውን እንዲወጡ ኮንፈረንሱ ከፍተኛ ሚና እንዳለው አመልክቷል፡፡

በኮንፈረንሱ “ሀገር በቀል የሰላምና የመቻቻል እሴቶች ለትውልድ ግንባታ በአዲስ አበባ” በሚል ርዕስ የውይይት መነሻ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡

ጥቅምት 29/2018

የ2018 የሩብ አመት አፈፃጸም ግብረ መልስ ላይ ውይይት ተደረገ!!.የቦሌ ክ/ከተማ አዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር የሩብ አመት አፈፃጸም የከተማ ግብረ መልስ ውይይት ተደረገ!! በውይይቱ ላይ የ...
07/11/2025

የ2018 የሩብ አመት አፈፃጸም ግብረ መልስ ላይ ውይይት ተደረገ!!.
የቦሌ ክ/ከተማ አዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር የሩብ አመት አፈፃጸም የከተማ ግብረ መልስ ውይይት ተደረገ!! በውይይቱ ላይ የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ም/ፕሬዝደንት እና የክ/ከተማው ደጋፊ ፎሊ ንጉሴ የግብረ መልሱን ሰነድ በማቅረብ የወረዳውን አመራሮች ማወያየት የቻለች ሲሆን፤ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ መሰረት ያደረጉ ሃሳቦች መነሳታቸውን እና የስራ እድል ፈጠራ ቀሪ ተግባራቶች መገመገማቸውን የክ/ከተማው ሰብሳቢ ታምራት ሚሊዮን ገልጿል።

"""ዉጤታማ የተሞክሮ ልምድ ልዉዉጥ ለጠንካራ አደረጃጀት"""የቦሌ ክ/ከተማ ወጣት ማህበር አመራሮች ማህበራዊ  ዘርፍ ና ቅስቀሳና ማደራጀት ዘርፍ   በየካ ክ/ከተማ አዲስ አበባ ወጣት ማህበር...
06/11/2025

"""ዉጤታማ የተሞክሮ ልምድ ልዉዉጥ ለጠንካራ አደረጃጀት"""

የቦሌ ክ/ከተማ ወጣት ማህበር አመራሮች ማህበራዊ ዘርፍ ና ቅስቀሳና ማደራጀት ዘርፍ በየካ ክ/ከተማ አዲስ አበባ ወጣት ማህበር በክ/ከተማው ወ/ስ/ጽ/ቤት ከረፋዱ 4:00 በመገኘት ና እንዲሁም

የየካ ክፍለ ከተማ ማህበራዊ ዘርፍ አመራር በቦሌ ከተማ ክ/ከተማ አዲስ አበባ ወጣት ማህበር በክ/ከተማው ወ/ስ/ ጽ/ቤት ከቀኑ 8:00 በመገኘት ልምድ ልዉዉጥ አካሄዱ።

ልምድ ልውውጥ ምርጥ ተሞክሮዎችን ለማስፋትና ተመሳሳይ ወደሆነ መልካም የተግባራት አፈጻጸም ላይ ለመድረስ ወሳኝ ሚና ያለው ሲሆን ይሄን መነሻ በማድረግ በዛሬው ዕለት ልምድ ልዉዉጥ አድርጓል። በልምድ ልዉዉጡ ከመረጃ አያያዝ አኳያ ፤ ከአመራርና አባላቶች የአቅም ግንባታ ስራዎች ፤ የግንኙነት ግዜን በተመለከተ መረጃን በቴክኖሎጂ ከማዘመን አንፃር፣ የመረጃ አማራጮችን ከማብዛት እና የሚድያ ተሳትፎ አንጻር በርካታ ጉዳዮች ላይ ውይይት ተደርጉዋል ::

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶች ማህበር ከጌጅ ኮሌጅ ጋር የስምምነት ሰነድ ተፈራረመጥቅምት 26/2018ዓ.ም የሰነዱ ዋና አላማ በባጀት አመቱ ለማህበሩን አባለት መደበኛ ትምህርት እና ...
05/11/2025

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶች ማህበር ከጌጅ ኮሌጅ ጋር የስምምነት ሰነድ ተፈራረመ

ጥቅምት 26/2018ዓ.ም

የሰነዱ ዋና አላማ በባጀት አመቱ ለማህበሩን አባለት መደበኛ ትምህርት እና አጫጭር ኮርሶችን ተደራሽ በማድረግ ከፍለው መመር ለማይችሉ ወጣቶች በቅናሽ እና አነስተኛ ክፍያ የዕድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያለመ መሆኑን የማህበሩ ፕሬዝዳንት ወጣት በረከት ብርቢርሳ ገልፀዋል።

ማህበሩ ወጣቶችን በትምህርት ለማብቃት ከተለያዩ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር ውል በመፈራረም በርካታ ወጣቶችን በመጀመርያ እና ሁለተኛ ድግሪ ተጠቃሚ ማድረጉን ወጣት በረከት ገልፆአል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ በቦሌ ክፍለ ከተማ የመደመር መንግስት የወጣቶች የፖናል ውይይት በክፍለ ከተማው ጎሮ አከባቢ በኮሪደር ልማቱ በተሰራ የመዝናኛ ቦታ ላይ አ...
04/11/2025

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ በቦሌ ክፍለ ከተማ የመደመር መንግስት የወጣቶች የፖናል ውይይት በክፍለ ከተማው ጎሮ አከባቢ በኮሪደር ልማቱ በተሰራ የመዝናኛ ቦታ ላይ አካሄደ።

በውይይቱ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና የስፖርት ቢሮ ም/ቢሮ ሀላፊ አቶ ዳዊት ትርፉ በኮሪደር ልማቱ የተሰሩ የመዝናኛ ቦታዎች ወጣቶች የእርስ በእርስ ግንኙነታቸውን እንዲያጠናክሩና በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ውይይት እንዲያደርጉ እድል የሰጠ ነው ብለዋል።

ወጣቶች በሀገራቸው ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ የነቃ ተሳትፎ ማድረግ አንዳለባቸው የተናገሩት አቶ ዳዊት በዚህ ጊዜ በውይይት የሚያምን እና ምክንያታዊ የሆነ ወጣት መሆን እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል።

ወጣቶች ያሎቸውን ፀጋዎች፣ ክህሎቶች፣ እውቀቶች እና ልምዶች በመደመርና አብሮ ሰርቶ የማደግ ባህላቸውን በማጎልበት በሀገራቸው የብልፅግና ጉዞ አሻራቸውን ማስቀመጥ እንዳለባቸው ም/ቢሮ ሀላፊው ተናግረዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ም/ቢሮ ሀላፊ አቶ ክብረአለም ደምሴ በጠቅላይ ሚኒስቴር ዳ/ር አብይ አህመድ በተፃፈው የመደመር ትውልድ መፅሐፍ ዙሪያ ለፖናል ውይይት መነሻ ፁሁፍ አቅርበዋል።

ወጣቶች አዳዲስ ፍልስፍናን፣ ፈጠራን እና የሀሳብ ሀይላቸውን በመደመር አገርን ለመለወጥ በሚያስችል መልኩ እንዲጠቀሙበት አቶ ክብረአለም ገልፀዋል።

የመደመር ፅንሰ ሀሳብ በመንፈሳዊ፣ በኢኮኖሚያዊ፣ በፖለቲካዊ እና በማህበራዊ ደረጃ ያለውን የአንድነት ሀሳብ አቶ ክብረአለም ባቀረቡት የመነሻ ፁሁፍ በዝርዝር ቀርቦል።

የቦሌ ክፍለ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ አንዳለም ወጣቶች መንግስት የፈጠረላቸውን መልካም እድል የራሳቸውን ሂይወት በመቀየር መልኩ በአግባቡ መጠቀም እንዳለባቸው ተናግረዋል።

በፖናል ውይይቱ ላይ የተሳተፉ ወጣቶች በበኩላቸው በኮሪደር ልማቱ የመዝናኛ ቦታዎችን ጨምሮ የተሰሩ የልማት ስራዎች ትርፍ ጊዚያቸውን አልባሌ ቦታ እንዳያሳልፉ እንዳረጋቸውና በማህበራዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ውይይት ለማድረግ እንደረዳቸው ገልፀዋል።

በመደመር ፅንሰ ለችግሮቻቸው መፍትሔ ለስኬታቸው መዳረሻ መንገድ መግኝት እንደሚቻል በፖናል ውይይቱ መረዳት እንደቻሉ ወጣቶች ተናግረዋል

👉ፕሬስ ሪሊዝ                                        የአዲሰ አበባ ወጣቶች ማህበር በየደረጃዉ ለሚገኙ የማህበር አመራሮች ስልጠና ሊሰጥ መሆኑን ገለፀ            ...
04/11/2025

👉ፕሬስ ሪሊዝ
የአዲሰ አበባ ወጣቶች ማህበር በየደረጃዉ ለሚገኙ የማህበር አመራሮች ስልጠና ሊሰጥ መሆኑን ገለፀ የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ከነገ ጀምሮ ለወረዳና ለክ/ከተማ የማህበሩ አመራሮች ለ3ትቀን የሚቆይ የአቅም ግንባታ ስልጠና እንደሚሰጥ የማህበሩ ተቀዳሚ ም/ል ፖሬዘዳት ወጣት ተከስተ አያሌዉ ገልጿል
አዲስ አበባ ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ Addis Ababa Youth and Sport Bureau .የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር / Addis Ababa Youth AssociationTekeste Ayalew

የቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 04 አስተዳደር ስፖርት ጽ/ቤት እንዲሁም የወረዳው ወጣቶች ማህበር በጋራ የ2018 ሩብ አመት አፈፃጸም እና  የእቅድ ውይይት አደረጉ!!በውይይቱ ላይ የጽ/ቤቱ ሃላፊ አቶ...
01/11/2025

የቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 04 አስተዳደር ስፖርት ጽ/ቤት እንዲሁም የወረዳው ወጣቶች ማህበር በጋራ የ2018 ሩብ አመት አፈፃጸም እና የእቅድ ውይይት አደረጉ!!
በውይይቱ ላይ የጽ/ቤቱ ሃላፊ አቶ ሰኢድ እንዲሁም የማህበሩ ሰብሳቢ ወጣት አብርሃም ሽመልስ ለማህበሩ ምክር ቤት አባላት እና ነዋሪዎች የተያዙትን እቅዶች አወያይተዋል።

01/11/2025
በአዲስ አበባ ወጣቶች ማኅበር የቦሌ ቅርንጫፍ በ2017 በጀት ዓመት የተሻለ አፈጻጸም ለነበራቸው አካላት የዕውቅና መርሐ ግብር አካሄደ፡፡ በመርሐ ግብሩ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የቦሌ...
30/10/2025

በአዲስ አበባ ወጣቶች ማኅበር የቦሌ ቅርንጫፍ በ2017 በጀት ዓመት የተሻለ አፈጻጸም ለነበራቸው አካላት የዕውቅና መርሐ ግብር አካሄደ፡፡

በመርሐ ግብሩ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከበደ ፈይሳ ባደረጉት ንግግር ወጣቶች በሀገር ግንባታ ወሳኝ ሚና እንዳላቸው አውስተው፣ ይህንን የወጣቶች ሚና በማጠናከር በፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማኀበራዊ መስኮች ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆኑ በስፋት እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡ የወጣቶች የተደራጀ ተሳትፎና እንቅስቃሴ ለሁለንተናዊ ተጠቃሚነት መረጋገጥ አስፈላጊ እንደሆነ የተናገሩት ኃላፊው፣ የቦሌ ክፍለ ከተማ አዲስ አበባ ወጣቶች ማኅበር ይህንን ግብ ለማሳካት እያደረገ ያለው አመርቂ እንቅስቃሴ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባው አስገንዝበዋል፡፡

የቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አንዱዓለም አሰፋ በበኩላቸው የአዲስ አበባ ወጣቶች ማኅበር ቦሌ ቅርንጫፍ ከምሥረታው አንስቶ በወጣቶች ተጠቃሚነት ዙሪያ በስፋት ሲሠራ መቆየቱን አውስተው፣ በተከናወኑ ተግባራት የተገኙ ስኬቶችን በማስቀጠል በ2017 በጀት ዓመት ያከናወናቸው ሥራዎች አበረታች ውጤት ማስመዝገባቸውን ተናግረዋል፡፡ በ2018 በጀት ዓመት ጉልህ ተግባራትን በመፈጸም የወጣቶች ተሳትፎን ለማረጋገጥ የተጀመረው እንቅስቃሴ በተሻለ ጥንካሬ እንዲቀጥል አባላት ንቁ ተሳትፎ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ኃላፊው በተጨማሪ አመልክተዋል፡፡ በአዲስ አበባ ወጣቶች ማኅበር የቦሌ ቅርንጫፍ ሰብሳቢ ወጣት ታምራት ሚሊዮን ባለፉት ዓመታት የወጣቶች ተሳትፎ እንዲያድግ ሰፊ ሥራዎች በማከናወን ማኅበሩ ከፍተኛ ሥራ ማከናወኑን አውስቶ፣ የ2017 በጀት ዓመት ስኬቶችን በግብዓትነት በመውሰድ በ2018 በጀት ዓመት ይህንን እንቅስቃሴ በላቀ ደረጃ ለማሳደግ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት በሰላም፣ በማኅበራዊ ተሳትፎና በክህሎት ግንባታ ወጣቶችን ተጠቃሚ ያደረጉ ሥራዎች በስፋት መከናወናቸውን አመልክቷል፡፡

በመድረኩ በ2018 በጀት ዓመት ማኅበሩ ለማከናወን ባቀዳቸው ተግባራት ዙሪያ ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን፣ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ለማኅበሩ ስኬት አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት የዋንጫና የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል፡፡

ጥቅምት 20/2018

30/10/2025
''አዲስ አቅም፤ አዲስ እድል ለወጣቶች!'' በቦሌ ክፍለ ከተማ ከአስራ አንዱም ወረዳዎች ለተውጣጡ ወጣቶች በሥራ እድልና በመንግሥት የድጋፍ ማዕቀፍ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫና የማይንድ ሴት ሥ...
28/10/2025

''አዲስ አቅም፤ አዲስ እድል ለወጣቶች!''

በቦሌ ክፍለ ከተማ ከአስራ አንዱም ወረዳዎች ለተውጣጡ ወጣቶች በሥራ እድልና በመንግሥት የድጋፍ ማዕቀፍ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫና የማይንድ ሴት ሥልጠና ተሰጥቷል።

''አዲስ አቅም፤ አዲስ እድል ለወጣቶች!'' በሚል መሪ ሐሳብ በተሰጠው በዚህ ሥልጠና ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ዳዊት ትርፉ የሰው ሀይል፣ ሀብትና ፀጋዎች በመጠቀም የሚቻል በመሆኑ ወጣቶች ሀገራችን ባላት ሀብትና በተመቻቸላቸው የሥራ ዕድል ተጠቅመው እራሳቸውን፣ ቤተሰባቸውንና ሀገራቸውን ከድህነት ለማውጣት በቅድሚያ አመለካከታቸውን መቀየርና በተግባር ማሳየት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።

የቦሌ ክፍለ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አንዷለም አሰፋ በበኩላቸው እንደተናገሩት አስተሳሰብ ከተቀየረ ብቁ፣ የተማረና የፈጠራ ክህሎት ያለው ዜጋ ካለ ሀገር ትለወጣለች፣ ልማትም ይፋጠናል ለዚህ ደግሞ የቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ በመሆን ወጣቶች ላይ የሚታይ ለውጥ እንዲመጣ በመስራት ላይ መሆናቸውን ገለጸው የማይንድሴት ስልጠናው ለወጣቶች የሚታይ ለውጥ የሚያመጣ፣ እይታን የሚያስተካክል ትርጉም ያለው ህይወት እንዲመሩ የሚያስችል ፋይዳ ያለው በመሆኑ ስልጠናው የወጣቱን አስተሳሰብ፣ አመለካከትና የእውቀት አድማስ ይበልጥ እንዲያሰፋ በየጊዜው ስልጠና እንደሚሰጥም ገልፀዋል።

ወጣቶች ሁልጊዜ ብልህና አስተዋይ የሆነ አስተሳሰብን በመላበስ የይቻላል መንፈስን በማጎልበት ስራ ፈጣሪና የስራ ባለቤት በመሆን ውጤታማ መሆን እንዳለባቸው በስልጠናው ላይ ግንዛቤ ተፈጥሮላቸዋል።

በስልጠናው የተሳተፉ ወጣቶች በሰጡት አስተያየት ከስልጠናው በቂ እና ጠቃሚ ግንዛቤን ስለመያዛቸውና ወደ ተግባር ለመቀየር ስለመዘጋጀታቸው ገልጸው በቀጣይ መሰል የስልጠና መድረኮች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ ጠይቀዋል።
ጥቅምት 18/2018
ቦሌ ማህበር ኮሙኒኬሽን

የጋራ ስምምነት ለውጤታማነት!!የአዲስ አበባ ምግብ መድሃኒት  ባለስልጣን ቦሌ ቅርንጫፍ ከአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ቦሌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ጋር የ2018 የጋራ የስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ!!በ...
28/10/2025

የጋራ ስምምነት ለውጤታማነት!!
የአዲስ አበባ ምግብ መድሃኒት ባለስልጣን ቦሌ ቅርንጫፍ ከአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ቦሌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ጋር የ2018 የጋራ የስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ!!
በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ የቅ/ጽ ሃላፊዋ ወ/ሮ አለሜ ባጫ እንደገለፁት የ2018 ተግባራት ቀደም ብለው በጋራ የተጀመሩ ቢሆንም በእቅድ መስፈር ያለባቸው ሃሳቦች በማስተካከል ከማህበሩ ጋር የሚያሰራ ሰነድ መሆኑን ገልጸዋል።
የማህበሩ ሰብሳቢ ወጣት ታምራት ሚሊዮን በበኩሉ ይህ ሰነድ ቀደም ሲል የተዘጋጀ አዳዲስ ኢኒሼቲቮች የተጨመሩበት የሚያሰራ ስምምነት መሆኑን ገልጾ ወጣቱ ጤናማ አምራች ዜጋ እንዲሆን ከጽ/ቤቱ ጋር በመሆን ሰፊ ስራዎችን እንሰራለን ብሏል። የማህበሩ የወረዳ አመራሮች ተገኝተው ውይይት በማድረግ ፕሮግራሙ ተጠናቋል።

Address

Bole Subcity
Addis Ababa
1234567890

Telephone

0934538279

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bole Youth Association posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share