18/08/2026
ተልእኳችን ማለዳ
ነሀሴ 12 - 2018 ዓ.ም
የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ — የማርቆስ ወንጌል 4:26
እርሱም አለ። በምድር ዘርን እንደሚዘራ ሰው የእግዚአብሔር መንግሥት እንደዚህ ናት ሌሊትና ቀን ይተኛልም ይነሣልም።
እኔ ዘርን የምዘራ ነኝ
ኢየሱስ በመካከላችን ለመኖርና ለማስተማር በነበረበት ዘመን፣ አንድ ገበሬ የዘር ከረጢቱን በትከሻው አርጎ በተዘጋጀው እርሻ ላይ ዘሩን በእጁ እየበተነ ሲያርስ ማየት የተለመደ ክስተት ነበር። ኢየሱስ በዚህ ምሳሌ ውስጥ ዘሩ እንዴት በቀስ በቀስ እንደሚበቅልና እንደሚያድግ ሲያስረዳ እንደምንመለከተው፣ ዘሩ አዲስ ሕይወትን የማስገኘት አቅም ያለውን የማዳን የምሥራች ይወክላል።
ሐዋርያው ጳውሎስ በሮሜ 1:16 ላይ፣ "ወንጌል ለሚያምኑ ሁሉ የእግዚአብሔር ኃይል ለማዳን ነው" በማለት ተመሳሳይ ሐሳብ ያብራራል። ወንጌል የግለሰቦችን ሕይወትም ሆነ የሙሉ የማህበረሰብን ገጽታ የመለወጥ ትልቅ አቅም ያለው ሕያው ኃይል ነው። ከምድር በታች ተሰውሮ እንደሚበቅል ዘር ሁሉ፣ የወንጌልም መልእክት በሰው ልብ ጥልቅ ውስጥ ተሸሽጎ ሥር ይደዳል። እዚያው እያደገ እና እየጎለበተ ሄዶም በመጨረሻ የጽድቅን ፍሬ ያፈራል።
እኛም የወንጌልን ዘር በውስጣችን አምቀን ከማስቀረት ይልቅ፣ በሕይወት ዘመናችን ሁሉ በልግስና እንድንበትነው ተጠርተናል። ዘሩን የምንበትነው ሚሲዮናውያንን ወይም የሚሲዮን ድርጅቶችን በመደገፍ፣ በማህበረሰብ የበጎ አደራጎት አገልግሎቶች ላይ በመሳተፍ፣ ጎረቤታችንን ለቡና በመጋበዝ እና በመሳሰሉት መልካም ነገሮች ነው፦ ከቤተሰቦቻችንና ከጓደኞቻችን ጋር መንፈሳዊ ውይይቶችን ስናደርግ የወንጌልን ዘር እንዘራለን፤ ከሥራ ባልደረቦቻችን ጋርም እንዲሁ። የኢየሱስን የምሥራች በምናሰራጭበት ጊዜ ሁሉ፣ መንፈሳዊ ፍሬን በማፍራቱ ሂደት ውስጥ የበኩላችንን ድርሻ እየተወጣን እንገኛለን።
ጸሎት
ጌታ ሆይ፣ መልካሙን የምሥራች አካፍለኸናል፤ አዲስ ሕይወትንም ሰጥተኸናል። ዘሩ አድጎ ለክብርህ የሚሆን የበዛ ፍሬ እንዲያፈራ የምታደርገው አንተ እንደሆንክ በመተማመን፣ ይህን የምሥራች ለሌሎች እንድናካፍል እርዳን። አሜን።
ከ https://todaydevotional.com/authors/kevin-deraaf ድህረ ገጽ ተወስዶ የተተረጎመ