የቅማንት ልማት ማህበር አ/አ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት

የቅማንት ልማት ማህበር አ/አ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from የቅማንት ልማት ማህበር አ/አ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት, Charitable organisation, megenaga, Addis Ababa.

📖=1000036184926 ንግድ ባንክ
Phone 🤳=0938781800=0918423643
- ከለገሱ በኃላ ኮሜንት ላይ ደረሰኙን ያስቀምጡልን
እናመሰግናለን
ይህ የቅማንት ልማት ማህበር የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ይፋዊ የፌስቡክ ፔጅ ሲሆን ተጠሪነቱም ለዋና መስሪያ ቤት ነው።
#አድራሻ፦ አዲስ አበባ መብራት ሀይል ጃክሮስ

17/06/2026

👇👇👇👇👇👇👇👇👇

 👌_______________________________________እንኳን ለ1447ኛው ለተከበረው የኢድ አል–አድሐ በዓል በሰላም፣ በጤናና በፍቅር አደረሳችሁ!ይህ ታላቅ በዓል የሰላም፣ የአንድ...
26/05/2026

👌
_______________________________________
እንኳን ለ1447ኛው ለተከበረው የኢድ አል–አድሐ በዓል በሰላም፣ በጤናና በፍቅር አደረሳችሁ!
ይህ ታላቅ በዓል የሰላም፣ የአንድነት፣ የመተሳሰብና የመቻቻል እሴቶችን የሚያጠናክር የእምነት እና የፍቅር እዲሆንላችሁ እየተመኘን ።
ቅማንት ልማት ማህበርን በመደገፍ ለህዝባችን እድገትና ለቀጣይ ትውልድ ብሩህ ተስፋ ተሳታፊ እንሁን።

ዒድ ሙባረክ
18/09/2018 ዓ/ም
ጎንደር
ኢትዮጵያ

በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የሚንቀሳቀሱ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የሚከናወኑ የልማት ስራዎችን በመከታተል እና በመደገፍ ውጤታማ ማድረግ እንደሚገባ ተገለጸየማዕከላዊ ጎንደር ዞን ገንዘብ መምሪያ...
23/05/2026

በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የሚንቀሳቀሱ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የሚከናወኑ የልማት ስራዎችን በመከታተል እና በመደገፍ ውጤታማ ማድረግ እንደሚገባ ተገለጸ

የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ገንዘብ መምሪያ የመንግስትንና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የምክክር መድረክ አዘጋጅቷል።

በዕለቱ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አወቀ አስፈሬ፥ የልማት ድርጅቶች በዞኑ ዘርፈብዙ ስራዎችን እያከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።

ለዚህም የህብረተቡን ችግሮች ለመፍታት የሚያከናውኗቸውን የልማት ተግባራት በሚገባ መከታተል እና መደገፍ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

በዞኑ የተያዙ የልማት እቅዶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የጋራ ርብርብ ይጠይቃል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው ባለድርሻ አካላት በእነዚሁ ድርጅቶች የሚከናወኑ የልማት ስራዎችን በመከታተል እና በመደገፍ ውጤታማ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸውም ተናግረዋል፡፡

የመንግስት እና የሲቪል ማህበራት ጥምረት የህዝብን የልማት እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ መመለስና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ማስፈን እንደሚያስችል ጠቁመው፤ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ድጋፍ ሊጠናከር እንደሚገባም አክለዋል፡፡

የዞኑ ገንዘብ መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ሰላማዊት ነጋ በበኩላቸው በተቋቋመው አዋጅ መሠረት ተግባራዊ ተደርጎ በየጊዜው የጋራ ግምገማ መደረጉን አንስተዋል።

በዞኑ በዘንድሮው በጀት ዓመት 26 የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሁለት ነጥብ አንድ ቢሊዮን በሚጠጋ ብር 28 የልማት ፕሮጀክቶች እያከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል፡፡

ጤና፣ ትምህርት፣ ንጹህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ማስፋፋት እና የሴቶች እና ህጻናት ተጠቃሚነት ማጎልበት ድርጅቶቹ የዞኑን መንግስት ጥረት እየደገፉ ከሚገኙባቸው ዘርፎች መካከል እንደሆኑ አስረድተዋል፡፡

በዞኑ ስምምነት ወስደው እየተቀሳቀሱ ከሚገኙ 26 የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ውስጥ 15ቱ አገር አቀፍ እና 11ዱ ደግሞ አለምአቀፍ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እንደሆኑም ታውቋል።

በዚሁ የምክክር መድረክ የተለያዩ የዞኑ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አመራር አባሎች እንዲሁም ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

#ምንጭ-Central Gondar Zone Communications

 #የቅልማ የዛሬ ውሎው ይህንን ይመስላል። #ስራዎቻችን የሽልማቶቻችን ምክንያት ናቸው። የተሻለ እንድንሰራ ደግሞ የአባላቶቻችን ድጋፍ እና መዋጮ የሽልማቶቻችን መሰረት ናቸው። #ሽልማቶቻችን ሁ...
23/05/2026

#የቅልማ የዛሬ ውሎው ይህንን ይመስላል።
#ስራዎቻችን የሽልማቶቻችን ምክንያት ናቸው።
የተሻለ እንድንሰራ ደግሞ የአባላቶቻችን ድጋፍ እና መዋጮ የሽልማቶቻችን መሰረት ናቸው።
#ሽልማቶቻችን ሁሉ የጋራ ውጤቶቻችን ናቸው

 #እናመሰግናለን  #እናመሰግናለን  #የዓመት ሰው ይበልልን #ወንድማችን አባይ እሸቴ በ2018ዓ/ም ድጋፍ ከአደረጉ ሰዎች መካከል 15,000 (አስራ አምስት) ሺ ብር ድጋፍ በማድረግ የአመቱ ...
07/04/2026

#እናመሰግናለን
#እናመሰግናለን
#የዓመት ሰው ይበልልን
#ወንድማችን አባይ እሸቴ በ2018ዓ/ም ድጋፍ ከአደረጉ ሰዎች መካከል 15,000 (አስራ አምስት) ሺ ብር ድጋፍ በማድረግ የአመቱ #ደረጃ አንድ ሰፖንሰራችን ነበር እናመሰግናለን

 #ቅንነታችን ከልብ የመነጨ እና ልማታዊ ከሆነ የአንድ ቀን ሻይ ቡናችን የቅልማ ዓመታዊ ክፍያ ነው። እና እርስዎ ከፍለዋል  #ጓደኛዎስ?
24/02/2026

#ቅንነታችን ከልብ የመነጨ እና ልማታዊ ከሆነ የአንድ ቀን ሻይ ቡናችን የቅልማ ዓመታዊ ክፍያ ነው። እና እርስዎ ከፍለዋል #ጓደኛዎስ?

   #ቅልማ የካቲት 17/2018ዓ/ም
24/02/2026


#ቅልማ

የካቲት 17/2018ዓ/ም

 #እናመሰግናለንየሰራነውን ት/ቤት ትውልድ ይቀረፅበታል። ልማት ማህበሩ ዛሬ ከሰራው የተሻለ መስራት እንዲችል በሀሳብ፣በእውቀት እና በገንዘብ መደገፍ ግድ ይላል። ለዚህ ደግሞ የሚዲያ አካላት ...
14/02/2026

#እናመሰግናለን
የሰራነውን ት/ቤት ትውልድ ይቀረፅበታል። ልማት ማህበሩ ዛሬ ከሰራው የተሻለ መስራት እንዲችል በሀሳብ፣በእውቀት እና በገንዘብ መደገፍ ግድ ይላል። ለዚህ ደግሞ የሚዲያ አካላት የሰጡት ትኩረት እና ማስታወቂያ ያልስሙት እንዲሰሙ ሰምተው ያልተረዱ ደግሞ ስለ ቅማንት ልማት ማህበር የተሻለ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ትልቅ ሚና ያለው ሲሆን አባል ያልሆኑ እንዲሆኑ አባል የሆኑ ደግሞ ኩራት እንዲሰማቸው ያደርጋል ለማለት እንወዳለን።
🙏

12/02/2026

Check out የቅማንቷ ንግስት (አንዛኮና)💙🤍❤️3ቱወፎች❤’s video.

Address

Megenaga
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የቅማንት ልማት ማህበር አ/አ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share