Eyerusalem Negash

Eyerusalem Negash “ብዙ ሰዎች የመሰከሩለትን ከእኔም የሰማኸውን ሌሎችን ደግሞ ሊያስተምሩ ለሚችሉ ለታመኑ ሰዎች አደራ ስጥ።”
— 2ኛ ጢሞቴዎስ 2፥2

በክርስቶስ ኢየሱስ ላረፍን ሰዎች የትኛውም እርምጃ ከእረፍት በስቲያ እንጂ ከእረፍት ወዲህ አይደለም። በዚህች ቀውጢ ዓለም በእረፍቱ ያሳረፈን ጌታ ስሙ የተባረከ ይሁን።ኢየሱስ እረፍታችን ነው!...
12/06/2026

በክርስቶስ ኢየሱስ ላረፍን ሰዎች የትኛውም እርምጃ ከእረፍት በስቲያ እንጂ ከእረፍት ወዲህ አይደለም። በዚህች ቀውጢ ዓለም በእረፍቱ ያሳረፈን ጌታ ስሙ የተባረከ ይሁን።

ኢየሱስ እረፍታችን ነው!

እነሆ ለተቅበዘበዘች፥ እረፍቷን በነገሮች ልትሞላ ለምትባክን ነፍስ መልዕክቴ እነሆ:- ኢየሱስ ክርስቶስ የዘላለም እረፍት ነው!

በቅርቡ….
11/06/2026

በቅርቡ….

ለብዙዎች ምናልባት ተምሮ ጨርሶ መመረቅ፤ በተለይ በመጀመሪያ ዲግሪ አሁን አሁን ብዙም ብርቅ አይደለ ይሆናል። እውነት ነው ከፍ ብሎም ባለ ደረጃ በተማሩበት መስክ መጨረስና መሸለም ምንም ሊሆን...
09/06/2026

ለብዙዎች ምናልባት ተምሮ ጨርሶ መመረቅ፤ በተለይ በመጀመሪያ ዲግሪ አሁን አሁን ብዙም ብርቅ አይደለ ይሆናል። እውነት ነው ከፍ ብሎም ባለ ደረጃ በተማሩበት መስክ መጨረስና መሸለም ምንም ሊሆን ይችላል።

ግን የመንገዱ ነገር ከዚህ ይለያል። በተለይ ደግሞ እግዚአብሔር ሲመራ እሺ ብሎ ለሚጓዝ ሂደቱ ልብ አንጠልጣይ ነው።

ብዙዎች እንደሚሉ የእግዜር መንገድ መሃሉ አይነገርም! አቀበት፣ ቁልቁለት፣ ሜዳ፣ ጎርባጣ፣ ስርጓጎጥ፣ ዓይነቱ እልፍ ነው። ግን ደግሞ እርሱም አለ። ጌታ ካለ ደግሞ የትም ይመቻል። የአእኔም የETC ጉዞዬ ይሄንኑ ነው የሚመስለው።

እውነቱ የአራት ዓመት ትምህርትን ሰባት ዓመታት አድርጌ ስጨርስ በመሃል እንዳልጨርስ ሊያደርጉ የሚችሉ ተግዳሮቶች ነበሩ ግን በእግዚአብሔር ሃይል አሸነፍኳቸው።

በእነዚህ ዓመታት ካሳለፈኳቸው ከባባድ ሁኔታዎች ውስጥ ትልቁ ሶስተኛዋን ልጄን ሩትዬን ለስምንት ወራት በማህፀኔ ተሸክሜ ቀኑ ደርሶ ላቅፋት ጓጉቼ ያጣሁበት ጊዜ ነበር። በዚህ ምክንያት አቋርጬም ነበር።

ደግሞ የካሳው ጌታ የተወደደውን ልጄን ክርስቲያንን የሰጠኝና የተቀበልኩትም በእነዚሁ ዓመታት መሃከል ነበር።

ሌሌችም እዚህ ልገልጣቸው የማልችላቸውን አስቸጋሪ ጎዳናዎችን ተጉዣለሁ። በርግጥ ይሄም ብርቅ አይደለም። ግና አብሮኝ የተጓዘው ኢየሱስና ከመንገዴ የተማርኳቸው መርኾዎች ብርቅ ናቸው። ከዚህ መንገድ ውጪ አይገኙምና!

እናማ ምን ለማለት ነው? እያለቀሱ የሚስቁበት፣ እየታመሙ ለሌሎች የሚያበሩበት መንገድ። ይህ በጌታ መንገድ ላይ ብቻ የሚገኝ እውነት ነው። ይህ ደግሞ ከብርቅ በላይ ነው!

ኢየሱስ የሰጠኝ አቅሞቼ ናችሁ። ያለ እናንተ ድጋፍ ይህ እውን አልሆነም።              በአደባባይ አመሰግናችኋለሁ!❤️
08/06/2026

ኢየሱስ የሰጠኝ አቅሞቼ ናችሁ። ያለ እናንተ ድጋፍ ይህ እውን አልሆነም።

በአደባባይ አመሰግናችኋለሁ!❤️

«እግዚአብሔር ብቻውን መራው፤ከእርሱም ጋር ሌላ አምላክ አልነበረም።»      ዘዳግም 32፥12
07/06/2026

«እግዚአብሔር ብቻውን መራው፤
ከእርሱም ጋር ሌላ አምላክ አልነበረም።»

ዘዳግም 32፥12

31/05/2026

የሰው ልጅ የማይደበዝዝ ተስፋ ኢየሱስ ብቻ!!

27/05/2026

ህይወት ያለ ኢየሱስ አድካሚ፣ አሰልቺ፣ ፋይዳ ቢስና አስከፊ ቆይታ ናት። ገንዘብ፣ ትዳር፣ ክብር ሁሉ ከተስፋ ቢስነቷ አያድኗትም። ኢየሱስ አንተን አውቆ በአንተ ለኖረ ሰው በምንም ውስጥ አንተ የነፍስ ፍስሃ ነህ።

“42-ዓመታት”ን በእግዚአብሔር ቸርነት በማይቀያየር ፍቅሩ፤ በማይዝል ትዕግስቱ፤ በማያልቅ ይቅርታው፤ በአስደናቂ ጥበቃውና በተትረፈረፈ ፀጋው ኖርኩ። በዚህ ሁሉ ውስጥ የተረዳሁት ነገር በምድር...
22/05/2026

“42-ዓመታት”ን

በእግዚአብሔር ቸርነት በማይቀያየር ፍቅሩ፤ በማይዝል ትዕግስቱ፤ በማያልቅ ይቅርታው፤ በአስደናቂ ጥበቃውና በተትረፈረፈ ፀጋው ኖርኩ።

በዚህ ሁሉ ውስጥ የተረዳሁት ነገር በምድር እርሱን ለማክበርና ለፈጠረኝ ነገር ኖሬ ለማለፍ እንደሰነበትሁ ነው።

ዛሬን የመኖር ዕድል ዘላለምን በክብርና በላቀ ብድራት ለመኖር ካልሆነ እነሆ በህይወት መኖር ምን ይጠቅማል? ትርፉስ ምንድን ነው?

የልደት ቀን መልዕክቴ:- እነሆ በህይወት ያለሁት ለስራ ነው…… በህይወት ያለነው በእኛ ሊሰራ ላለው የከበረ ዓላማው ነው የሚል ነው። በፍፃሜም እረፍትና ክብር በጌታ እጅ ይጠብቀናል። 🏃‍♀️🏃‍♀️🏃‍♀️ ወደ ስራ….

መልካም ልደት ለእኔ!!

መልዕክቴ፡-ክርስቶስን ለምንከተል ሁላችን፣ ዘመኑ ከእርሱ ጋር መቆየትን እንደሚጠይቅ ተረድተን ከመጮህ ዝምታን፣ ከሩጫ መስከንን፣ ብዙ ከማውራት አብዝተን ቃሉን መመገብን፣ በእርጋታ ሆነን መምጣ...
21/05/2026

መልዕክቴ፡-

ክርስቶስን ለምንከተል ሁላችን፣ ዘመኑ ከእርሱ ጋር መቆየትን እንደሚጠይቅ ተረድተን ከመጮህ ዝምታን፣ ከሩጫ መስከንን፣ ብዙ ከማውራት አብዝተን ቃሉን መመገብን፣ በእርጋታ ሆነን መምጣቱን እንጠባበቅ የሚል ነው።

በእውነት ከእግሩ ስር ከመሆን የተሻለስ ቦታ ይኖራልን? ሰላም፣ ደስታ፣ ፍስሃ፣ እረፍት መገኛቸውስ እርሱ ጋር አይደለምን?

የሰላሙን ጌታ እያመለክን እስከመቼ ተረብሸን እንኖራለን? የደስታ ምንጭ የሆነውን ኢየሱስን እየተከተልን ከደስታ ርቀን እስከ መቼ እንቆያለን? እስከመቼስ ዼንጤ ዼንጤ እንጫወታለን? ከእውነተኛው ህይወት ርቀን ምድራዊ ለሆነ ከንቱ ስኬት እንጋደላለን? የሚበልጠው ቀሎብን ለተራው ነገር እናጎበድዳለን?

የህይወት ምልልሳችን ሌጣችንን መቅረታችን አላሰበቀብንም? እስከመቼ ነው “ማረን ከአንተ ርቀናል፤ በሃይማኖታዊ ካባ ተጀቡነን የነፍሳችን ጌታ ትተን ስኬትን፣ ገንዘብን አምልከናልና ማረን የማንለው?

ወገኖች የክርስቶስ ተከታይ ክርስቶስን መምሰሉ ሀቅ ነው። ስለዚህ ከኢየሱስ ጋር የቆየ ንግግሩም፣ ህይወቱም ሁለንተናው ኢየሱስን ያብረቀርቃል። ታዲያ ዛሬ ሰዎች ቀርበው በውኑ ሲያዩን ማንን ያዩብን ይሆን? በምንስ ይታነፁብን ይሆን?

እናማ ምን ለማለት ነው:- ሰከን እንበልና ህይወታችንን፣ የቆምንበትን እንመርምር። ወደ ህይወት ጌታ ኢየሱስ እንመለስ። መንፈሳዊ ጥማት የሚረካው በየኮንፍረን በመዞር፣ በመዝሙር ድለቃ በማበድና በመዝለል ላብ በላብ በመሆን ሳይሆን ከክርስቶስ እግር ስር በመሆንና ቃሉን በመታዘዝ ነው።

ኢየሱስ ዳግም በመለከት ታጅቦ ይመጣል የተዘጋጀን እንሁን!!

ኢየሩሳሌም ነጋሽ
(ምስል በAl)

20/05/2026

ጌታን ለማመስገን ጥሩ ስሜት እንዲሰማን አያስፈልግም። ይልቁንም
በምንም ውስጥ ሆነን እንዲህ እንላለን፡-
ስለሁሉ እግዚአብሔር ይመስገን!

Address

Addis Ababa

Telephone

+251970070404

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Eyerusalem Negash posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Eyerusalem Negash:

Share