Berhan Lehetsanat

Berhan Lehetsanat An Ethiopian NGO based in Addis Ababa that works primarily with disabled children.

የህይወትን የተለያዩ ተግዳሮትን አልፈው ለሌሎች ትልቅ ተምሳሌት  ከሆኑ  ታላላቅ ሰዎች መካከል አንዷ የሆኑት የድርጅታችን የብርሃን ለሕፃናት መስራችና ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ እቴነሽ ወንድም...
24/12/2025

የህይወትን የተለያዩ ተግዳሮትን አልፈው ለሌሎች ትልቅ ተምሳሌት ከሆኑ ታላላቅ ሰዎች መካከል አንዷ የሆኑት የድርጅታችን የብርሃን ለሕፃናት መስራችና ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ እቴነሽ ወንድምአገኘሁ በየነ ታህሳስ 11 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዶር አዲስ ሆቴል በነበረው ፕሮግራም ላይ የህይወት ተሞክሮዎቻቸውን እና ልምዳቸውን አካፍለዋል ስለነበረው ፕሮግራም እጅግ በጣም እናመሰግናለን። 🙏🙏🙏👍👍👍

ሰላም የተናፈቃችሁ የፌስኩክ ቤተሰቦቻችን ጥሩና አስተማሪ የህይወት ተሞክሮዎች ለመስማትና ለመማር ተዘጋጅታችሁል;  እኔ ዝግጁ ነኘ እንግዲያውስ ታህሳስ 11 ቀን 2018 ዓ.ም. 10:30 ሰዓት...
18/12/2025

ሰላም የተናፈቃችሁ የፌስኩክ ቤተሰቦቻችን ጥሩና አስተማሪ የህይወት ተሞክሮዎች ለመስማትና ለመማር ተዘጋጅታችሁል; እኔ ዝግጁ ነኘ እንግዲያውስ ታህሳስ 11 ቀን 2018 ዓ.ም. 10:30 ሰዓት በአዶር አዲስ ሆቴል እንገናኝ፡፡🙏🙏🙏👍👍👍

ጆሮ ከወሊድ በኋላ የሐፊዝ መሐመድ  አጭር ታሪክ በአርእስቱ ትንሽ ሳትደነግጡ አልቀራችሁም ግን እውንተኛ ታሪክ ነው ጆሮ የተገኘው ከወሊድ በኋላ እንደውም ትምህርት ቤት ከገባ በኋላ ነው፡፡...
08/12/2025

ጆሮ ከወሊድ በኋላ የሐፊዝ መሐመድ  አጭር ታሪክ
በአርእስቱ ትንሽ ሳትደነግጡ አልቀራችሁም ግን እውንተኛ ታሪክ ነው ጆሮ የተገኘው ከወሊድ በኋላ እንደውም ትምህርት ቤት ከገባ በኋላ ነው፡፡ ታሪኩ እንዲህ ነው የታሪኩ ባለቤት ሐፊዝ መሐመድ ይባላል የተወለደው ነሐሴ 26, 2004 በደሴ ከተማ ነው፡፡ የሚኖረው ገራዶ ቀበሌ 06 ከእናቱ ጋር ነው፡፡ ታላቅ እህትና ታናሽ ወንድም አለው አሱ ለቤቱ ሁለተኛ ልጅ ነው፡፡

የሐፊዝ እናት በእርግዝናዋ ወቅት በጣም ስለምትታመም በጣም ብዙ መድሐኒት ትወስድ ነበር፡፡ በዚህ ላይ ገቢ የሚያስገኝ ሥራ የሌላትና ልጆቿን የምታሳድገው ብቻዋን ነው፡፡ የልጆቹን ጉሮሮ ለመሸፈንና መሰረታዊ ፍላጎቶቿቸውን ለሟሟላት የተለያዩ ሰዎች ቤት ትሰራለች፡፡

ሐፊዝ በ2017 ዓ.ም. የ5ተኛ ክፍል ተማሪ ሲሆን ብዙ ጊዜ ከትምህርት ቤት ይቀራል፡፡ በዚህም ምክንያት ውጤቱ አመርቂ አልሆነም በመሆኑም 5ተኛ ክፍልን ደገመ፡፡ ሐፊዝ አካል ጉዳተኛ ነው ጆሮው አይሰማ ከዚህም ባሻገር እንደማንኛውም ሰው ጆሮው በቦታው የለም፡፡

የጆሮ ቀዳዳም የለውም እናቱ ስለሐፊዝ ስትናገር ስለልጇ አካል ጉዳተኝነት በጣም አዝናሁ ጉዳቱ ሲወለድ ጀምሮ ነው ትላለች፡፡ ምንም ገንዘብ ስለሌለኝ የትኛውም ሆስፒታል አልወሰድኩትም ግን አንዴ ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ወስጄው ነበር፡፡ ከሰው ባገኘሁት የገንዘበ እርዳታ ጥቁር አንበሳ ሲቲ እስካን ከተነሳ በኋላ የህክምና ባለሞያው የልጁ ጉዳት ትንሽ የተወሳሰበ ስለሆነ ከዚህ በላይ ሌላ የሕክምና አገልግሎት መሰጠት እንደማይችሉ አስረዱኝ፡፡ የካቲት ሆስፒታልም ተመሳሳይ ምላሽ ሰጠኝ ሌላው የተሰጠኝ ምላሽ ወደ መጣበት ይመለስና በምልክት ቋንቋ ትምህርቱን እንዲቀጥል የሚል ነው፡፡ ከዚህ ባሻገር ባለበት አካል ጉዳት ምክንያት ትንሽ አስቸጋሪ ባህሪ አለው፡፡ አይናገርም ሰው የሚለውን ስለማይሰማ ይናደዳል ይህ ለኔ አስቸጋሪ ጊዜ ነው፡፡

ከዛ ትምህርት ቤት ወሰድኩትና በምልክት ቋንቋ ከአንደኛ ክፍል መማር ጀመረ፡፡ አሁን የሚባለውን ስለሚሰማ ባህርይውም እየተስተካከለ መጣ የ4ተኛ ክፍል ተማሪ ሳለ የብርሃን ለሕፃናት ድርጅት ሠራተኞች አገኙትና የተሃድሶ ስራው ተጀመረ፡፡ በመሰረቱ የልጁ አካል ጉዳት አይነት የተለመደና ቀላል ባለመሆኑ ለተሃድሶ ሥራው አስቸጋሪ ነው የሚሆነው፡፡ ሆኖም ከጥቂት ሳምንታት በኋላ ወደ ደሴ ሆስፒታል በድርጅቱ ተላክን ደሴ ከአቅሙ በላይ ስለሆነበት ወደ ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል እንዲሄድና የተሃድሶው ሥራ እንዲጀመር ተወሰነ በዚህን ወቅት እናቱ በጣም ሰጋሁ ግራምገባኝ ትላለች፡፡ ግን የብርሃን ለሕፃናት ሠራተኞች አዲስ አበባ የድርጅቱ ሠራተኞች ይቀበሉሻል ማሪፊያም ያዘጋጁልሻል በማለት አጽናኑኝ እኔም ወደ አዲስ አበባ ሄድኩ እንደተባለውም የብርሃን ለሕፃናት የአዲስ አበባ ቢሮ ተቀበሎኝ ማረፊያም አዘጋጅቶልኝ የልጄም ሕክምና ተጀመረ ትራንስፖርት፣ ሕክምና፣ አልጋና የምግብ ወጪያችን ተሸፍኖ ህክምናው ቀጠለ የህክምና ዶክተሮች የመስማት ችሎታ ከፈተሹ በኋላ ልጁ የፕላስቲክ ቀደ ጥገናው እንደሚደረግለት ገለፁልኝ የቀረውን ፡፡ ሆኖም ጳውሎስ ሆስፒታል ፕላስቲክ ሰርጀሪ ክፍል ስለሌለው ወደ አቤም ሆስፒታል ሪፈር ተደረግን በዚሁ ሆስፒታል የፕላስቲክ የቀዶ ጥገና ተጀመረ ስጋው ከአንድ አካሉ ክፍል ተወስዶ በአንድ ጆሮው ተከናወነ በዚህን ወቅት እናትየዋ በጣም በጭንቅ ውስጥ ገባች ምክንያቱም ቀዶ ጥገናው ረዥም ጊዜ ወስዶ ስለነበር፡፡ ከጠዋት እስከ ማታም ምግብ አልቀመሰችም፡፡ ሆኖም የፕላስቲክ ሰርጀሪው በተሳካ ሁኔታ ተጠናቀቀ፡፡

ማታ ሲነቃ እናቱ በጣም ደስ አላት ከዛ ለ21 ቀናት ተከታታይ የሕክምና አገልግሎት በጳውሎስ ሆስፒታል ተሰጠው እናቱ በጣም ደስተኛ ሆነች የልጁ ጆሮ ሲገለጥ ቁስሉም ደርቆ መስማትም ጀመረ ከኦፕሬሽኑ በፊት ስለማይስማ ይበሳጫል ለረዥም ጊዜም ያለቅሳል እሱ ሲጠራት ካልሰማችው ይናደዳል፡፡ ያማርራል በራሱ ምንም ማድረግ አይፈልግም አሁን ግን በራሱ ብዙ ነገር ይሰራል ደስተኛ ነው፡፡ አሁን የትምህርቱም ደረጃ ጥሩ ነው፡፡ ትምህርቱን ጨርሶ ሥራ ሲይዝ መኪና ይኖረኛል መንጃ ፈቃድ በማውጣት መኪና እነዳለሁ ይላል፡፡ አሁን በጣም ደስተኛ ነው፡፡

እሱን ጨምሮ ሶስት ልጆች አሏት እናቱ እሱ እንደማንኛውም ሰው መናገርና ማውራት ይመኛል፡፡ ብርሃን ለሕፃናት የሕክምናውን ወጪ ሙሉ ለሙሉ ሸፈኖለታል ብርሃን ለሕፃናትን እናትየዋ ከልብ ማመስገን ትፈልጋለች፡፡

የህይወትን የተለያዩ ተግዳሮትን አልፈው ለሌሎች ትልቅ ተምሳሌት  ከሆኑ  ታላላቅ ሰዎች መካከል አንዷ የሆኑት የድርጅታችን የብርሃን ለሕፃናት መስራችና ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ እቴነሽ ወንድም...
05/12/2025

የህይወትን የተለያዩ ተግዳሮትን አልፈው ለሌሎች ትልቅ ተምሳሌት ከሆኑ ታላላቅ ሰዎች መካከል አንዷ የሆኑት የድርጅታችን የብርሃን ለሕፃናት መስራችና ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ እቴነሽ ወንድምአገኘሁ በየነ ናቸው። ስለዚህ ሁላችንም ታህሳስ 11 ቀን 2018 ዓ.ም. 10:30 ሰዓት በአዶር አዲስ ሆቴል እንገናኝ 🙏🙏🙏👍👍👍

24/11/2025

የድርጅታችን የክብር አምባሳደር ሰአሊ ብሩክ የሺጥላ ዘንድሮ ለ25ተኛ ጊዜ በተካሄደው በታላቁ ታላቁ ሩጫ ላይ ተካፍሏል።

አስደሳች ዜና ከብርሃን ለሕፃናት!ብርሃን ለሕፃናት ድርጅት ሕዳር 11/2018 ዓ.ም ባካሄደው ደማቅ ሥነ-ሥርዓት፣ ሰዓሊ ብሩክ የሺጥላን "የክብር አምባሳደር" አድርጎ ሾሟል!በዚህ ልዩ የፊርማ...
22/11/2025

አስደሳች ዜና ከብርሃን ለሕፃናት!

ብርሃን ለሕፃናት ድርጅት ሕዳር 11/2018 ዓ.ም ባካሄደው ደማቅ ሥነ-ሥርዓት፣ ሰዓሊ ብሩክ የሺጥላን "የክብር አምባሳደር" አድርጎ ሾሟል!

በዚህ ልዩ የፊርማ ፕሮግራም ላይ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣
የድርጅቱ የቦርድ አባላት፣
አጋር ድርጅቶች፣
ታዋቂና ተፅእኖ ፈጣሪዎች እንዲሁም የሚዲያ አካላት ተገኝተዋል።

ሰዓሊ ብሩክ የሺጥላ በተሰጠው አደራ መሠረት በሚሄድበት ቦታ ሁሉ ስለ ብርሃን ለሕፃናት በጎ ተግባራት ለማስተዋወቅ እና ድርጅቱን በቅንነት ለማገልገል ቃል ገብቷል።

እንኳን ደስ አለን!

19/10/2025

በ2017 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን በጭልጋ ወረዳ የ6ኛ፣ 8ኛ እና 12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገባቸው፣ የወረዳው አስተዳደር ምክር ቤትና ትምህርት ጽ/ቤት ለ"ብርሃን ለሕፃ....

ኢትዮቴሌኮም የደብተር ልገሳ አደረገ**ብርሃን ለሕጻናት ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር ጳጉሜ 1 ቀን 2017 ዓ.ም. በአዲስ አበባ እና በቢሾፍቱ ከተማ ለሚገኙ 330 አካል ጉዳተኛ ሕጻናት የ...
16/09/2025

ኢትዮቴሌኮም የደብተር ልገሳ አደረገ
**
ብርሃን ለሕጻናት ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር ጳጉሜ 1 ቀን 2017 ዓ.ም. በአዲስ አበባ እና በቢሾፍቱ ከተማ ለሚገኙ 330 አካል ጉዳተኛ ሕጻናት የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።

ኢትዮቴሌኮም ብርሃን ለሕጻናት ለሚረዳቸው ሕጻናት በየግላቸው አንድ ደርዘን ደብተር መለገሱ ተማሪዎች ያለስጋት ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉ ትልቅ እገዛ ያደርጋል።

ይህ የኢትዮ ቴሌኮም ድጋፍ ከሶስት ዓመታት በፊት ተጀምሮ እስካሁን የቀጠለ ነው። ኢትዮ ቴሌኮም ለብርሃን ለሕጻናት ድርጅት በ2015 ዓ.ም. ክረምት ላይ የ625 ሺህ ብር ድጋፍ ያደረገ ሲሆን ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በየዓመቱ በጳጉሜ ወር ለድርጅቱ ተጠቃሚዎች የደብተር ድጋፍ ያለማቋረጥ እያደረገ ይገኛል።

ብርሃን ለሕጻናት ድርጅት አካል ጉዳተኛ ሕጻናትን በመርዳት ብሩሕ ሕይወት እንዲኖራቸው ለማስቻል የሚተጋ ሀገር በቀል ግብረ ሰናይ ድርጅት ነው።

የድርጅቱ መስራች እና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ እቴነሽ ወ/አገኘሁም ኢትዮ ቴሌኮም ላደረገው ድጋፍ በሕጻናቱ ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ይህ አይነቱ ትብብር ሌሎች ድርጅቶችም የማኅበራዊ ኃላፊነት ስሜታቸውን እንዲወጡና አካል ጉዳተኛ ሕጻናት የተሻለ ትምህርት እንዲያገኙ ድጋፋቸውን እንዲያደርጉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

15/09/2025
Board of Directors of Berhan Lehetsanat has conducted  its regular meeting Berhan Lehetsanat has conducted its board of ...
04/08/2025

Board of Directors of Berhan Lehetsanat has conducted its regular meeting

Berhan Lehetsanat has conducted its board of Directors meeting on 29 of July 2025. In the meeting the Quarter Program and Finance utilization was presented and discussions performed with the Objective of Improving the performance of the organization. More over organizational updates also presented to provide the necessary information for the participants.

The second Bi-annual program & Financial Plan also presented and approved by the board of Directors. In the meeting the need to strengthen the organization development efforts through visibility and resource mobilization took the necessary attention and set future direction.

Berhan Lehetsanat held its annual board meeting on March 15, 2025 at Ras Hotel. At this meeting, the 2024 audit report o...
20/03/2025

Berhan Lehetsanat held its annual board meeting on March 15, 2025 at Ras Hotel. At this meeting, the 2024 audit report on the work and budget performance during the year, the 2025 work and budget plan, and the organization's current updates were discussed and approved.
At the same meeting, the Board of Directors presented letters of recognition and certificates of appreciation to three outgoing Board members. The Board also approved the nominations of new Board members with diverse work experience and educational background to help to strengthen the organization.

Address

Ldeta S/city, Woreda 09 823/50
Addis Ababa
1000

Opening Hours

Monday 02:30 - 17:00
Tuesday 02:30 - 17:15
Wednesday 08:30 - 17:15

Telephone

+251115544814

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Berhan Lehetsanat posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Berhan Lehetsanat:

Share