Berhan Lehetsanat

Berhan Lehetsanat An Ethiopian NGO based in Addis Ababa that works primarily with disabled children.

We are delighted to announce that Ms. Etenesh Wondmagegnehu, the Founder and Chief Executive Officer of our organization...
17/07/2026

We are delighted to announce that Ms. Etenesh Wondmagegnehu, the Founder and Chief Executive Officer of our organization, Berhan Lehetsanat, has been selected as the Ethiopia representative for the CBR Africa Network (CAN).
Congratulations!

እንኳን ደስ አላችሁ የድርጅታችን የብርሃን ለሕፃናት መስራችና ዋና ስራ አስፈፃሚ የሆኑት ወ/ሮ እቴነሽ ወንድምአገኘሁ የCBR Africa Network (CAN) የኢትዮጵያ ተወካይ ሆነው ስለተመረጡ እጅግ በጣም ደስ ብሎናል እንኳን ደስ አላችሁ፡፡

ብርሃን ለሕፃናት ከሚሰጧቸው አገልግሎቶች ውስጥ አንዱ የሆነው የአእምሮ እድገት ውስንነት ጉዳተኞች ሕፃናት የሞያና የእለት ተእለት ክህሎት ተማሪዎች የ2018 ዓ.ም. የትምህርት መዝጊያን በማስ...
07/07/2026

ብርሃን ለሕፃናት ከሚሰጧቸው አገልግሎቶች ውስጥ አንዱ የሆነው የአእምሮ እድገት ውስንነት ጉዳተኞች ሕፃናት የሞያና የእለት ተእለት ክህሎት ተማሪዎች የ2018 ዓ.ም. የትምህርት መዝጊያን በማስመልከት በቀበና የመዝናኛ ፓርክ የተከናወነ የመዝጊያ ፕሮግራም

የህይወትን የተለያዩ ተግዳሮትን አልፈው ለሌሎች ትልቅ ተምሳሌት  ከሆኑ  ታላላቅ ሰዎች መካከል አንዷ የሆኑት የድርጅታችን የብርሃን ለሕፃናት መስራችና ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ እቴነሽ ወንድም...
24/12/2025

የህይወትን የተለያዩ ተግዳሮትን አልፈው ለሌሎች ትልቅ ተምሳሌት ከሆኑ ታላላቅ ሰዎች መካከል አንዷ የሆኑት የድርጅታችን የብርሃን ለሕፃናት መስራችና ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ እቴነሽ ወንድምአገኘሁ በየነ ታህሳስ 11 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዶር አዲስ ሆቴል በነበረው ፕሮግራም ላይ የህይወት ተሞክሮዎቻቸውን እና ልምዳቸውን አካፍለዋል ስለነበረው ፕሮግራም እጅግ በጣም እናመሰግናለን። 🙏🙏🙏👍👍👍

ሰላም የተናፈቃችሁ የፌስኩክ ቤተሰቦቻችን ጥሩና አስተማሪ የህይወት ተሞክሮዎች ለመስማትና ለመማር ተዘጋጅታችሁል;  እኔ ዝግጁ ነኘ እንግዲያውስ ታህሳስ 11 ቀን 2018 ዓ.ም. 10:30 ሰዓት...
18/12/2025

ሰላም የተናፈቃችሁ የፌስኩክ ቤተሰቦቻችን ጥሩና አስተማሪ የህይወት ተሞክሮዎች ለመስማትና ለመማር ተዘጋጅታችሁል; እኔ ዝግጁ ነኘ እንግዲያውስ ታህሳስ 11 ቀን 2018 ዓ.ም. 10:30 ሰዓት በአዶር አዲስ ሆቴል እንገናኝ፡፡🙏🙏🙏👍👍👍

ጆሮ ከወሊድ በኋላ የሐፊዝ መሐመድ  አጭር ታሪክ በአርእስቱ ትንሽ ሳትደነግጡ አልቀራችሁም ግን እውንተኛ ታሪክ ነው ጆሮ የተገኘው ከወሊድ በኋላ እንደውም ትምህርት ቤት ከገባ በኋላ ነው፡፡...
08/12/2025

ጆሮ ከወሊድ በኋላ የሐፊዝ መሐመድ  አጭር ታሪክ
በአርእስቱ ትንሽ ሳትደነግጡ አልቀራችሁም ግን እውንተኛ ታሪክ ነው ጆሮ የተገኘው ከወሊድ በኋላ እንደውም ትምህርት ቤት ከገባ በኋላ ነው፡፡ ታሪኩ እንዲህ ነው የታሪኩ ባለቤት ሐፊዝ መሐመድ ይባላል የተወለደው ነሐሴ 26, 2004 በደሴ ከተማ ነው፡፡ የሚኖረው ገራዶ ቀበሌ 06 ከእናቱ ጋር ነው፡፡ ታላቅ እህትና ታናሽ ወንድም አለው አሱ ለቤቱ ሁለተኛ ልጅ ነው፡፡

የሐፊዝ እናት በእርግዝናዋ ወቅት በጣም ስለምትታመም በጣም ብዙ መድሐኒት ትወስድ ነበር፡፡ በዚህ ላይ ገቢ የሚያስገኝ ሥራ የሌላትና ልጆቿን የምታሳድገው ብቻዋን ነው፡፡ የልጆቹን ጉሮሮ ለመሸፈንና መሰረታዊ ፍላጎቶቿቸውን ለሟሟላት የተለያዩ ሰዎች ቤት ትሰራለች፡፡

ሐፊዝ በ2017 ዓ.ም. የ5ተኛ ክፍል ተማሪ ሲሆን ብዙ ጊዜ ከትምህርት ቤት ይቀራል፡፡ በዚህም ምክንያት ውጤቱ አመርቂ አልሆነም በመሆኑም 5ተኛ ክፍልን ደገመ፡፡ ሐፊዝ አካል ጉዳተኛ ነው ጆሮው አይሰማ ከዚህም ባሻገር እንደማንኛውም ሰው ጆሮው በቦታው የለም፡፡

የጆሮ ቀዳዳም የለውም እናቱ ስለሐፊዝ ስትናገር ስለልጇ አካል ጉዳተኝነት በጣም አዝናሁ ጉዳቱ ሲወለድ ጀምሮ ነው ትላለች፡፡ ምንም ገንዘብ ስለሌለኝ የትኛውም ሆስፒታል አልወሰድኩትም ግን አንዴ ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ወስጄው ነበር፡፡ ከሰው ባገኘሁት የገንዘበ እርዳታ ጥቁር አንበሳ ሲቲ እስካን ከተነሳ በኋላ የህክምና ባለሞያው የልጁ ጉዳት ትንሽ የተወሳሰበ ስለሆነ ከዚህ በላይ ሌላ የሕክምና አገልግሎት መሰጠት እንደማይችሉ አስረዱኝ፡፡ የካቲት ሆስፒታልም ተመሳሳይ ምላሽ ሰጠኝ ሌላው የተሰጠኝ ምላሽ ወደ መጣበት ይመለስና በምልክት ቋንቋ ትምህርቱን እንዲቀጥል የሚል ነው፡፡ ከዚህ ባሻገር ባለበት አካል ጉዳት ምክንያት ትንሽ አስቸጋሪ ባህሪ አለው፡፡ አይናገርም ሰው የሚለውን ስለማይሰማ ይናደዳል ይህ ለኔ አስቸጋሪ ጊዜ ነው፡፡

ከዛ ትምህርት ቤት ወሰድኩትና በምልክት ቋንቋ ከአንደኛ ክፍል መማር ጀመረ፡፡ አሁን የሚባለውን ስለሚሰማ ባህርይውም እየተስተካከለ መጣ የ4ተኛ ክፍል ተማሪ ሳለ የብርሃን ለሕፃናት ድርጅት ሠራተኞች አገኙትና የተሃድሶ ስራው ተጀመረ፡፡ በመሰረቱ የልጁ አካል ጉዳት አይነት የተለመደና ቀላል ባለመሆኑ ለተሃድሶ ሥራው አስቸጋሪ ነው የሚሆነው፡፡ ሆኖም ከጥቂት ሳምንታት በኋላ ወደ ደሴ ሆስፒታል በድርጅቱ ተላክን ደሴ ከአቅሙ በላይ ስለሆነበት ወደ ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል እንዲሄድና የተሃድሶው ሥራ እንዲጀመር ተወሰነ በዚህን ወቅት እናቱ በጣም ሰጋሁ ግራምገባኝ ትላለች፡፡ ግን የብርሃን ለሕፃናት ሠራተኞች አዲስ አበባ የድርጅቱ ሠራተኞች ይቀበሉሻል ማሪፊያም ያዘጋጁልሻል በማለት አጽናኑኝ እኔም ወደ አዲስ አበባ ሄድኩ እንደተባለውም የብርሃን ለሕፃናት የአዲስ አበባ ቢሮ ተቀበሎኝ ማረፊያም አዘጋጅቶልኝ የልጄም ሕክምና ተጀመረ ትራንስፖርት፣ ሕክምና፣ አልጋና የምግብ ወጪያችን ተሸፍኖ ህክምናው ቀጠለ የህክምና ዶክተሮች የመስማት ችሎታ ከፈተሹ በኋላ ልጁ የፕላስቲክ ቀደ ጥገናው እንደሚደረግለት ገለፁልኝ የቀረውን ፡፡ ሆኖም ጳውሎስ ሆስፒታል ፕላስቲክ ሰርጀሪ ክፍል ስለሌለው ወደ አቤም ሆስፒታል ሪፈር ተደረግን በዚሁ ሆስፒታል የፕላስቲክ የቀዶ ጥገና ተጀመረ ስጋው ከአንድ አካሉ ክፍል ተወስዶ በአንድ ጆሮው ተከናወነ በዚህን ወቅት እናትየዋ በጣም በጭንቅ ውስጥ ገባች ምክንያቱም ቀዶ ጥገናው ረዥም ጊዜ ወስዶ ስለነበር፡፡ ከጠዋት እስከ ማታም ምግብ አልቀመሰችም፡፡ ሆኖም የፕላስቲክ ሰርጀሪው በተሳካ ሁኔታ ተጠናቀቀ፡፡

ማታ ሲነቃ እናቱ በጣም ደስ አላት ከዛ ለ21 ቀናት ተከታታይ የሕክምና አገልግሎት በጳውሎስ ሆስፒታል ተሰጠው እናቱ በጣም ደስተኛ ሆነች የልጁ ጆሮ ሲገለጥ ቁስሉም ደርቆ መስማትም ጀመረ ከኦፕሬሽኑ በፊት ስለማይስማ ይበሳጫል ለረዥም ጊዜም ያለቅሳል እሱ ሲጠራት ካልሰማችው ይናደዳል፡፡ ያማርራል በራሱ ምንም ማድረግ አይፈልግም አሁን ግን በራሱ ብዙ ነገር ይሰራል ደስተኛ ነው፡፡ አሁን የትምህርቱም ደረጃ ጥሩ ነው፡፡ ትምህርቱን ጨርሶ ሥራ ሲይዝ መኪና ይኖረኛል መንጃ ፈቃድ በማውጣት መኪና እነዳለሁ ይላል፡፡ አሁን በጣም ደስተኛ ነው፡፡

እሱን ጨምሮ ሶስት ልጆች አሏት እናቱ እሱ እንደማንኛውም ሰው መናገርና ማውራት ይመኛል፡፡ ብርሃን ለሕፃናት የሕክምናውን ወጪ ሙሉ ለሙሉ ሸፈኖለታል ብርሃን ለሕፃናትን እናትየዋ ከልብ ማመስገን ትፈልጋለች፡፡

Address

Ldeta S/city, Woreda 09 823/50
Addis Ababa
1000

Opening Hours

Monday 02:30 - 17:00
Tuesday 02:30 - 17:15
Wednesday 08:30 - 17:15

Telephone

+251115544814

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Berhan Lehetsanat posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Berhan Lehetsanat:

Shortcuts

Share