15/04/2022
ከዚህ በፊት እንደገለፅኩት ፦
ገፁ የወደፊት እቅድ እንጅ የተመሰረተ እንዳልሆነ መግለፄ ይታወቃል።
ከፅሁፉ ያልተረዱኝ አንዳንድ ወንድሞችና እህቶች በውስጥ ምን ልትመሰርት አስበህ ነው ?የሚል ጥያቄ በተደጋጋሚ እያቀረቡልኝ ይገኛል።
መልሴ ምንም ነው።ምክንያቱም የሚመሰረተው ማህበር ገና ለውይይት የቀረበ ነው።ሲመሰረትም በግለሰብ ደረጃ የሚቋቋም ሳይሆን መሪ ተመርጦለት ሰብሳቢ ...ተመርጦለት በብዙ ሰዎች ስብስብ የሚቋቋም መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል።
ለውይይት ይረዳ ዘንድ ይህን የቴሌግራም ቻናል ከፍቻለሁ።
https://t.me/wogededevelopmentalassociation
♥ ሌላው በኮመንት ብዙ አስተያየቶች መጥተዋል ።በጥቂቱ ፦አመራሩ ሌባ ነው እንደት ልንመሰርት እንችላለን?
ብር ሰብስባችሁ ልትበሉ አስባችሁ ነው።
መቼም ወግዲ አትለወጥም እና ሌሎች አስተያየቶች ተሰጥተዋል።
ይህ ማህበር መግባባት ላይ ተደርሶ ቢመሰረት ከማንኛውም ፖለቲካዊ ጣልቃ ገብነት ነፃ እንደሚሆን ልናምን ይገባል።ስለዚህ ማንኛውም የፖለቲካ አመራር ማህበሩ ውስጥ ሊካተት አይችልም ያ ማለት በነፃነት ይንቀሳቀሳል ማለት ነው።
♥ በተጨማሪም ማህበሩ ሲመሰረት የራሱ የሆነ ህግ ይኖረዋል ።ህጉ ማህበሩን የሚመሩትም ሆኑ አባላቶች ህጉን ከተላለፉ በህግ ተጠያቂ ይሆናሉ ማለት ነው። ህግ ሲወጣለት የገንዘብ ብክነትን የስነ ምግባር ጉድለትንም ጭምር ማዕቀፍ አድርጎ የሚወጣ ይሆናል።ህግ ሲረቀቅም የህግ ባለሙያዎችን በማማከር እንጅ በዘፈቀደ አይሆንም ።ማህበሩም ሲቋቊም እንድሁ።
ትኩረት ልንሰጥበት የምንችለው ጉዳይ ደግሞ በወረዳው የመልማት ጉዳይ ላይ ተስፋ ማሟጠጥ ነው።
ይህ ፈፅሞ ስህተት ነው።እኔ እስከማውቀው ድረስ ልማታዊም ሆነ መረዳጃ ማህነራት ተመስርተው አልሰምር ብሏቸው የተበተኑ የሉም።ይህ ባልሆነበት ሁኔታ ተስፋ መቁረጡ ተገቢ አይደለም።
በአመራር ችግር ምክንያት የተስተጓጎለው ልማት በልጆቿ ይስተካከላል የሚል አቋም ልንይዝ ይገባል።
ሌላው የአመራር ችግር ያለበት ወግዲ ወረዳ ብቻ እንደሆነ አድርጎ ማሰቡ ተገቢ አይደለም። እንደ አጠቃላይ በክልል ደረጃ የአመራር ችግር እንዳለ ግንዛቤ ውስጥ ልናስገባ ግድ ይለናል።
ይህንንም የአመራር ችግር ተቋቁመው ማህበራት የመሰረቱ ወረዳዎች ብዙ ናቸው።ለምሳሌ በቅርቡ የመቅደላ ወረዳ ተወላጆች ማህበር መስርተዋል ።
ስለዚህ እኛ ማድረግ የማንችልበት ምንም ምክንያት የለም።
ደስ የሚለው ደግሞ እጅግ አበረታችና ሞራል የሚሰጡ አስተያየቶች አሉ። እየወደቅን እየተነሳንም ቢሆን ወደተግባር እንግባ የሚሉ አስተያየቶች አሉ ይህ ይበረታታል።
ከላይ የፃፍኩት የኔ የግሌ ሀሳብ ነው።ማንኛውንም አስተያየት መስጠት ይቻላል።ስጋቶች መነሳታቸው ለጥንቃቄ ጠቃሚ ስለሚሆኑ የሚነሱ ስጋቶች በግልፅ ቢነሱ መልካም ነው።
አመሰግናለሁ!
You can view and join right away.