04/04/2023
የክስታኔ ጉራጌ ህዝብ የልማት ማህበር መጋቢት 24 ቀን 2015 ዓ.ም ቀጣይ 5 ዓመት የልማት ስራ ዕቅዱን (ፍኖተ ካርታ) በሆቴል ዲአፍሪክ ለህዝብ ይፋ አደረገ። በዕለቱ የመንግስት ባለስልጣናትን ጨምሮ ከተለያየ የህብረተሰብ ክፍል የተወጣጣ በርካታ ሰው የተገኘ ሲሆን የክስታኔ የአገር እድሮችና ከአዲስ አበባ ውጪ የመጡ የሌላ የልማት ማህበር ተወካዮችም በመድረኩ ተሳትፈዋል።
ከዚህ ባለፈም ሁሉም እንደ ጉዳዩ ባለቤት የልማቱን ስራ ከማህበሩ ጋር በተቀናጀ መልኩ በጋራ ለማካሄድ ዝግጁነቱን አሳውቆ የዕለቱ መርሃ ግብር በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።