Ethiopia Scout Association

Ethiopia Scout Association ዝግጁ - Zigiju

የሐዘን መግለጫ በሐረር ስካውት ካውንስል ታሪክ አንጋፋና ቀደምት ከሚባሉ የስካውት አባሎች እና አመራሮች ስማቸው የሚጠቀሰው አቶ አያሌው ዘውዴ ቀዳሚ ናቸው አቶ አያሌው ዘውዴ በስካውት ትልቅ ...
06/11/2025

የሐዘን መግለጫ

በሐረር ስካውት ካውንስል ታሪክ አንጋፋና ቀደምት ከሚባሉ የስካውት አባሎች እና አመራሮች ስማቸው የሚጠቀሰው አቶ አያሌው ዘውዴ ቀዳሚ ናቸው

አቶ አያሌው ዘውዴ በስካውት ትልቅ ቦታ ያለውን የ አመራርነት ስልጠና በስካውት wood badge የተሰኘውን ስልጠና በቀዳሚነት የወሰዱና ለሐረር ስካውት ካውንስል ትልቅ አስተዋፅኦ እያበረከቱ ያሉ አመራር እንደነበሩም ይታወቃል አቶ አያሌው የ ሐረር ስካውት ካውንስል በሚፈልጋቸው ወቅት ሁሉ ከጎን በመሆን በሙሉ አቅማቸው ሲያግዙ እንደነበርና ክልላችን 8ኛውን የኢትዮጵያ ስካውት ጃምቡሬ ሲያዘጋጅ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ትልልቅ ኃላፊነቶችን ወስደው ካውንስሉ ፕሮግራሙን በተሳካ ሁኔታም እንዲያልቅ ያደረጉና በካውንስሉ ውስጥ የአዋቂ ስካውት አመራር በመሆንና በመከታተል ላይ የሚገኙ ለካውንስሉ ትልቅ አቅም እና ብርታት የሚሰጡ አባታችን ነበሩ ቢሆንም ግን የፈጣሪ ትዕዛዝ ነውና አቶ አያሌው ዘውዴን ትላንት ጥቅምት 26/2018 ዓ.ም ምሽት በድንገተኛ ህመም አጥተናቸዋልና ለመላው የካውንስሉ አመራርና አባላት ለሚያውቋቸውና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ሁሉ መፅናናትን እየተመኘን የአባታችንን ነብስ በአፀደ ገነት እንዲያሳርፍልን እንመኛለን ::

ጥቅምት 27/2018 ዓ.ም
ምንጭ:- ሐረር ስካውት ካውንስል

የኢትዮጵያ ስካውት ማህበር
ለመላው የካውንስሉ አመራርና አባላት፣ ለመላው ስካውት፣ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ሁሉ መፅናናትን እየተመኘን የአባታችንን ነብስ በአፀደ ገነት እንዲያሳርፍልን እንመኛለን።

የኢትዮጵያ ስካውት ማህበር
27/02/2018 ዓ.ም

በመላው ኢትዮጵያ ለምትገኙ ስካውቶች በሙሉ ጆታ ጆቲ 2025 ኢንተርኔት ጃምቡሬ ላይ የተሳተፋችሁ ስካውቶች እና የስካውት መሪዎች ለፕሮግራሙ መሳካት ላደረጋችሁት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ከልብ እያመ...
20/10/2025

በመላው ኢትዮጵያ ለምትገኙ ስካውቶች በሙሉ ጆታ ጆቲ 2025 ኢንተርኔት ጃምቡሬ ላይ የተሳተፋችሁ ስካውቶች እና የስካውት መሪዎች ለፕሮግራሙ መሳካት ላደረጋችሁት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ከልብ እያመሰገንን የተሳትፎና የ Challenge Badge Award አሸናፊነት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ጥቅምት 13/2018 ዓ.ም በኢሜል አድራሻችሁ የሚድርሳችሁ መሆኑን እንገልፃለን ።

ተከታታይ መረጃ እንዲደርስዎ ከቀረቡ አማራጮች ሊንኩን በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ

"- - - - - - ለሕይወት ዝግጁ - - - - - -"

Ethiopia Scout Association
⚜️
ⒻⒶⒸⒺⒷⓄⓄⓀ;👉 https://www.facebook.com/EthiopiaScouts
ⓉⒺⓁⒺⒼⓇⒶⓂ;👉 https://linktr.ee/EthiopiaScouts
LINKEDIN;-
https://www.linkedin.com/company/ethiopiascouts/

Email;- [email protected]
more info about Scouting 👉 Scout.org

ጥቅምት 10/2018
የኢትዮጵያ ስካውት ማሕበር

ጆታ ጆቲ 2025 ኢንተርኔት ጃምቡሬ ተጠናቀቅጆታ ጆቲ 2025 ከጥቅምት 7- 9/2018 ዓ.ም በመላው ዓለም የሚገኙ ስካውቶች ባሉበት ሆነው በበይነ መረብ ሲሳተፉ የነበረው የጆታ ጆቲ 2025 ...
20/10/2025

ጆታ ጆቲ 2025 ኢንተርኔት ጃምቡሬ ተጠናቀቅ

ጆታ ጆቲ 2025 ከጥቅምት 7- 9/2018 ዓ.ም በመላው ዓለም የሚገኙ ስካውቶች ባሉበት ሆነው በበይነ መረብ ሲሳተፉ የነበረው የጆታ ጆቲ 2025 ኢንተርኔት ጃምቡሬ በትላንትናው እለት ተጠናቋል ፡፡

JOTA-JOTI ኢንተርኔት ጃምቡሬ በዓለም ዙሪያ ያሉ ስካውቶች አዳዲስ ክህሎቶችን የሚማሩበት፣ ሃሳቦችን የሚለዋወጡበት፣ እና ዓለም አቀፍ ጓደኝነትን የሚገነቡበት ስካውታዊ ፕሮግራም ሲሆን ባለፉት ሶስት ቀናት የድሬዳዋ ስካውት ካውንስል አባላት በመድረኩ በንቃት ሲሳተፉ ቆይተዋል ፡፡

በትላንትናው በነበረው የመዝጊያ ፕሮግራም በሶሰት ቀናት ቆይታ በነበረው ስልጠናዎች ከፍተኛ ውጤት ያመጡ /Challenge Awarded/ አሸናፊ ስካውቶች እንዲሁም ፕሮግራሙ የተሳካ እንዲሆን ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ ስካውት መሪዎች የእውቅና የምስጋና የስካውት ባጅ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል ፡፡

ጥቅምት 10/2018 ዓ.ም
ምንጭ:-ድሬዳዋ ስካውት ካውንስል
የኢትዮጵያ ስካውት ማህበር

ለመላው ኢትዮጵያዊያን ኩራት ለሆነው እና የሁሉም ኢትዮጵያዊ አሻራ ላረፈበት ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ምረቃ እንኳን አደረሳችሁ ! እንኳን አደረሰን !🇪🇹🇪🇹ጳጉሜ 04/2017 ዓ.ምየኢት...
09/09/2025

ለመላው ኢትዮጵያዊያን ኩራት ለሆነው እና የሁሉም ኢትዮጵያዊ አሻራ ላረፈበት ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ምረቃ እንኳን አደረሳችሁ ! እንኳን አደረሰን !🇪🇹🇪🇹

ጳጉሜ 04/2017 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ስካውት ማሕበር

የኢትዮጵያ ስካውት ማሕበር ከመላው አገሪቱ ለተውጣጡ ወጣት ስካውት አባላት እና ተጽዕኖ ፈጣሪ ወጣቶች በቢሾፍቱ ከተማ ለሶስት ቀናት ሲሰጥ የነበረው የዲጃታላይዝ ዩዝ  ስልጠና ተጠናቀቀ ፡፡ሰኔ...
21/06/2025

የኢትዮጵያ ስካውት ማሕበር ከመላው አገሪቱ ለተውጣጡ ወጣት ስካውት አባላት እና ተጽዕኖ ፈጣሪ ወጣቶች በቢሾፍቱ ከተማ ለሶስት ቀናት ሲሰጥ የነበረው የዲጃታላይዝ ዩዝ ስልጠና ተጠናቀቀ ፡፡
ሰኔ 14/2017 ዓ.ም ቢሾፍቱ/ኢትዮጵያ
================================================================
የኢትዮጵያ ስካውት ማሕበር ከአፍሪካ ስካውት ሪጂን ቢሮ በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ወጣቶች በዲጂታል ዓለም በጎ ተፅዕኖ ፈጣሪ መሆን የሚያስችል የዲጂታላይዝ ዩዝ ኢትዮጵያ (Digitalis Youth Ethiopia ) ፕሮጀክት ለመተግበር የሚያስችል የመጀመሪያ ዙር ስልጠና ከመላው አገሪቱ ለተውጣጡ ስካውቶችና ተፅዕኖ ፈጣሪ ወጣቶች በቢሾፍቱ ከተማ ከሰኔ 12 – 14/2017 ዓ.ም ሲሰጥ የነበረው ስልጠና በዛሬው ዕለት ተጠናቋል ።

በሰልጠናው ወጣቶች የዲጂታል ዓለም እንቅስቃሴን በሚገባ በመረዳት በጎ ተፅዕኖ ፈጣሪ እንዲሆኑ እና አዎንታዊ ለውጥ እንዲያመጡ የሚያስችል ስልጠና ኬንያ ከሚገኘው የአፍሪካ ስካውት ቢሮ የመጡ አሰልጣኝና በቶጎ የአሰልጣኞች አሰልጣኝ ስልጠና የተከታተሉ የማሕበሩ ወጣት ስካውቶች ስልጠናውን ሰጥተዋል ፡፡

በስልጠናውም ማጠናቀቂያ ላይ የኢትዮጵያ ስካውት ማሕበር ቺፍ ኮሚሽነር ተገኝተው መልዕክትና የስራ መመሪያ ያስተላለፉ ሲሆን ለተሳታፊዎች እና ለአስተባባሪዎች ሰርተፍኬት አበርክተዋል ፡፡

ሰኔ 14/2017 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ስካውት ማሕበር

የሐረር ስካውት ካውንስል በአቡነ-ኢንድሪያስ ት/ቤት ካፕ ስካውቶችን አስመረቀ ⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️===========================================በዛ...
14/06/2025

የሐረር ስካውት ካውንስል በአቡነ-ኢንድሪያስ ት/ቤት ካፕ ስካውቶችን አስመረቀ ⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️
===========================================
በዛሬው እለት በአቡነ ኢንድሪያስ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የስካውትን ስልጠና ለ3ወር ያክል በማስተማርና ተማሪዎቹን ብቁ ሆነው አምሮአቸው ዳብሮ ለትምህርት ቤታቸውና ለጓደኞቻቸው አርአያ ሊሆኑ የሚችሉ እንዲሁም ለቤተሰቦቻቸው ታዛዥና አጋዥ እንዲሆኑ በማድረግና በማሰልጠን በዛሬው እለት በቀን 07/10/2017 ዓ.ም ላይ አስመርቋል።⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️
ምንጭ:- የሐረር ስካውት ካውንስል

የኢትዮጵያ ስካውት ማሕበር አዲስ አበባና ድሬዳዋን ጨምሮ  ከሁሉም ክልል ስካውት ካውንስሎች ለተውጣጡ የስካውት አመራሮች እና አስተባባሪዎች ሲሰጥ የነበረው ምግብ ለሕይወት ፕሮጀክት (Food ...
01/06/2025

የኢትዮጵያ ስካውት ማሕበር አዲስ አበባና ድሬዳዋን ጨምሮ ከሁሉም ክልል ስካውት ካውንስሎች ለተውጣጡ የስካውት አመራሮች እና አስተባባሪዎች ሲሰጥ የነበረው ምግብ ለሕይወት ፕሮጀክት (Food for Life) ስልጠና ተጠናቀቀ ፡፡

ግንቦት 24/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ

የኢትዮጵያ ስካውት ማሕበር ከአለም ስካውት ፋውንዴሽን በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ምግብ ለሕይወት ( Food For Life ) ፕሮጀክት ለመተግበር ለሶስት ቀናት ከመላው አገሪቱ ለተውጣጡ ስካውቶች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና በትላንትናው እለት ተጠናቋል ፡፡

በስልጠናው ማጠናቀቂያ ላይ ተገኝተው መልዕክትና የስራ መመሪያ የሰጡት የኢትዮጵያ ስካውት ማሕበር ቺፍ ስካውት ዶ/ር ቆስጠንጢኒዮስ በርህተስፋ ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለፁት ስካውት ትውልዱን በመልካም ስነ-ምግባር እና በአገር ፍቅር ስሜት ከመቅረፅ ባሻገር በዘላቂ ልማት ተግባራት ውስጥ ታዳጊዎችን እና ወጣቶችን ለማሳተፍ እንዲሁም ለአከባቢ ጥበቃ የበኩላችን አስተዋፅዎ ለማበርከት ምግብ ለሕይወት (Food for Life) ፕሮጀክት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው መሆኑን በመረዳት ከስልጠና ያገኙትን ልምድና እውቀት ወደ መጡበት አካባቢ ሲመለሱ ትኩረት ሰጥተው እንዲተገብሩት አሳስበዋል ፡፡

በተጨማሪ መልዕክት ያስተላለፉት የኢትዮጵያ ስካውት ማሕበር ዋና ኮሚሽነር ነብዩ መርዕድ እንደገለፁት ምግብ ለሕይወት (Food for Life) ፕሮጀክት ታዳጊዎችና ወጣቶች መሰረታዊ የግብርና እውቀት ኖሯቸው በትምህርት ቤታቸው እንዲሁም በአካባቢያቸው የጓሮ አታክልቶችን በቀላሉ በመትከል እና በማብቀል መጠቀም የሚችሉበትን ክህሎት እንዲያገኙ የሚያስችል እንዲሁም ዘላቂነት ያለው የምግብ ፍላጎትን በሟሟላት ስካውቶች የግብርና መር የስራ ፈጣሪነት እንዲያጎለብቱ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው እና ለዚህም ከፕሮጀክቱ አስፈላጊውን የስልጠና እና የግብዓት ድጋፍ እንደሚያደረግ ገልፀዋል፡፡

ምግብ ለሕይወት ፕሮጀክት በሁሉም ክልሎች እና በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች በሚገኙ ስካውት ካውንስሎች አማካኝነት ከመጪው ሰኔ ወር ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል ፡፡

የኢትዮጵያ ስካውት ማሕበር ግንቦት 24/2017 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ስካውት ማሕበር በመላው አገሪቱ ተግባራዊ የሚደረግ (Food for Life) ምግብ ለሕይወት ፕሮጀክት ስልጠና ለስካውት መሪዎች እና አስተባባሪዎች መስጠት ተጀመረ ፡፡ግንቦት 21/2...
29/05/2025

የኢትዮጵያ ስካውት ማሕበር በመላው አገሪቱ ተግባራዊ የሚደረግ (Food for Life) ምግብ ለሕይወት ፕሮጀክት ስልጠና ለስካውት መሪዎች እና አስተባባሪዎች መስጠት ተጀመረ ፡፡

ግንቦት 21/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ

ምግብ ለሕይወት (Food for Life) ፕሮጀክት በአለም ስካውት ፋውዴሽን ድጋፍ በኢትዮጵያ ፣ በማላዊ እና በሩዋንዳ ተግባራዊ የሚደረግ ፕሮጀክት ሲሆን ዋንኛ ዓለማው ታዳጊዎች መሰረታዊ የግብርና እውቀት ኖራቸው በትምህርት ቤታቸው እንዲሁም በአካባቢያቸው የጓሮ አታክልቶችን በቀላሉ በመትከል እና በማብቀል መጠቀም የሚችሉበትን ክህሎት እንዲያገኙ የሚያስችል እንዲሁም ዘላቂነት ያለው የምግብ ፍላጎትን በሟሟላት ለአካባቢ ጥበቃ የበኩላቸውን አስተዋፆኦ እንዲወጡ የሚያስችል ነው ፡፡

በዛሬው እለተም በአዲስ አበባ እየተሰጠ በሚገኘው ስልጠና ለሚቀጥሉት ሶስት ቀናት የሚቀጥል ሲሆን ከቤንሻንጉል ክልል በስተቀር ከሁሉም ክልሎች እና ከሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ የስካውት መሪዎች ፣ መምህራን እና አስተባባሪዎች ስልጠናውን እየተከታተሉ የሚገኙ ሲሆን ኬኒያ ከሚገኘው የአፍሪካ ስካውት ቢሮ የመጡት አሰልጣኝ ስልጠናውን እየሰጡ ይገኛል ፡፡

ግንቦት 21/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ
የኢትዮጵያ ስካውት ማሕበር

በኦሮሚያ ስካዉት ካዉንስል የመቂ ዲስትሪክት ላለፉት ተከታታይ ሶስት ወራት ያሰለጠኗቸዉን እጩ ስካዉቶች ግንቦት 2/2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ ስካዉት ማህበር አመራሮች በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ ...
12/05/2025

በኦሮሚያ ስካዉት ካዉንስል የመቂ ዲስትሪክት ላለፉት ተከታታይ ሶስት ወራት ያሰለጠኗቸዉን እጩ ስካዉቶች ግንቦት 2/2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ ስካዉት ማህበር አመራሮች በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ አስመርቀዋል።

Address

Addis Ababa
Ababa
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopia Scout Association posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share