06/11/2025
የሐዘን መግለጫ
በሐረር ስካውት ካውንስል ታሪክ አንጋፋና ቀደምት ከሚባሉ የስካውት አባሎች እና አመራሮች ስማቸው የሚጠቀሰው አቶ አያሌው ዘውዴ ቀዳሚ ናቸው
አቶ አያሌው ዘውዴ በስካውት ትልቅ ቦታ ያለውን የ አመራርነት ስልጠና በስካውት wood badge የተሰኘውን ስልጠና በቀዳሚነት የወሰዱና ለሐረር ስካውት ካውንስል ትልቅ አስተዋፅኦ እያበረከቱ ያሉ አመራር እንደነበሩም ይታወቃል አቶ አያሌው የ ሐረር ስካውት ካውንስል በሚፈልጋቸው ወቅት ሁሉ ከጎን በመሆን በሙሉ አቅማቸው ሲያግዙ እንደነበርና ክልላችን 8ኛውን የኢትዮጵያ ስካውት ጃምቡሬ ሲያዘጋጅ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ትልልቅ ኃላፊነቶችን ወስደው ካውንስሉ ፕሮግራሙን በተሳካ ሁኔታም እንዲያልቅ ያደረጉና በካውንስሉ ውስጥ የአዋቂ ስካውት አመራር በመሆንና በመከታተል ላይ የሚገኙ ለካውንስሉ ትልቅ አቅም እና ብርታት የሚሰጡ አባታችን ነበሩ ቢሆንም ግን የፈጣሪ ትዕዛዝ ነውና አቶ አያሌው ዘውዴን ትላንት ጥቅምት 26/2018 ዓ.ም ምሽት በድንገተኛ ህመም አጥተናቸዋልና ለመላው የካውንስሉ አመራርና አባላት ለሚያውቋቸውና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ሁሉ መፅናናትን እየተመኘን የአባታችንን ነብስ በአፀደ ገነት እንዲያሳርፍልን እንመኛለን ::
ጥቅምት 27/2018 ዓ.ም
ምንጭ:- ሐረር ስካውት ካውንስል
የኢትዮጵያ ስካውት ማህበር
ለመላው የካውንስሉ አመራርና አባላት፣ ለመላው ስካውት፣ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ሁሉ መፅናናትን እየተመኘን የአባታችንን ነብስ በአፀደ ገነት እንዲያሳርፍልን እንመኛለን።
የኢትዮጵያ ስካውት ማህበር
27/02/2018 ዓ.ም