10/11/2022
ዜና
የሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን የምስጋና ፕሮግራም አደረገ፤ በፕሮግራሙ ላይ የኢትዮጵያ አየር ትራሪክ ተቆጣጣሪዎች ማህበር በተጋባዥነት ተወክሏል። የዓለም አቀፉ የሲቪል አቪዬሽን ድርጅት (ICAO) 41ኛው ዓለም አቀፍ ጉባዔውን በካናዳ ሞንትሪያል ከተማ ከመስከረም 17 - 27 2015 ዓ.ም. ማካሄዱ ይታወቃል። በጉባኤው ኢትዮጵያ የድርጅቱ የካውንስል አባል ሆና በከፍተኛ ድምጽ ተመርጣልች፤ ሲቪል አቪዬሽን ሁለንተናዊ ደህንነት አጠባበቅና ቁጥጥር ልዩ ሽልማትና እውቅና አግኝቷል። የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ለተገኘው ውጤት ከፍተኛ አስተዋጽዎ አበርክተዋል ያላቸውን ተቋማትና ሰራተኞች የምስጋናና የዕውቅና ፕሮግራም አዘጋጅቷል፣ የምስክር ወርቀት አበርክቷል ።
በስካይ ላይት ሆቴል ከ 05፡00 ሰዓት ጀምሮ በተካሄደው ፕሮግራም ላይ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የትራንስፖርና ሎጅስቲክ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቤ ወ/ሮ ሸዊት ሻንካ የትራንስፖርና ሎጅስቲክስ ሚንቴስር ምኒስር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ እና ምኒስትር ዲኤታ አቶ ዳንጌ ቦሩ ተገኝተዋል። ማህበራችን በተደረገለት ግብዣ መሰርት ፕሬዝዳቱና ምክትል ፕሬዝዳንቷ በፕሮግራሙ ተካፍለዋል።